በ«ተቃዋሚዎች» መካከል ስለ አማራ ማንነት አይነቱ ክርር ያለ ጭቅጭቅ ሲነሳ «መጀመሪያ የሁላችንም ጠላት የሆነውን ህወሓትን ከስልጣን መፈንቀል ላይ ተባብረን እናተኩር ፤ ከዛ በኋላ ስለ ሌሎች ጉዳዮች መነጋገር ይቻላል» ይባላል። ለ27 ዓመት በተደጋጋሚ የሰማነው አሁንም የምንሰማው አባባል ነው።
አዎ ግባችን ህወሓትን ከስልጣን ማውረድ ከሆነ ከማንም ጋር ተባብረን ሌሎች ጉዳዮችንን በሙሉ ዘርግፈን ግባችን ላይ ማተኮር ነው ያለብን። ነገር ግን ይህን ማድረግ አልተቻለም። ለ27 ረዥም ዓመታት አልተቻለም! ተስማምተን ለአላማችን ብለን ተማምነንና ተባብረን አንድ ሆነን መስራት አልቻልንም።
ለምን? ለምን ግባችንን ለመምታት ግድ የሆነውን አንድነት መመስረት አልቻልንም? ያልቻልንበት ምክንያት እኛ «ተቃዋሚዎች» በርካታ የማንስማማባቸው የአገራችን የፖለቲካ ጉዳዮች ስላሉ ነው። በነዚህ ጉዳዮች ስለማንስማማ ተማምነን አብረን መስራት አልቻልንም።
ስለዚህ ይህን ችግር ለመፍታት ቁጭ ብለን መወያየት፣ ጉዳዮቹን ማብሰልሰል፣ መከራከር፤ መስማማት አለብን። ይህን የውይይት ስራችንን እስካሁን በጭራሽ አልሰራንም ማለት ይቻላል። እስካሁን ጊዜአችንን አቅማችንን 95% በኢህአዴግ ማልቀስ 5% በራሳችንን ማጎልበት ነው ያዋልነው! አንድ ላይ መስራት የምንችለው በኢትዮጵያ ያለንን ራዕይ ዙርያ በቂ ውይይታዊ ስራ ካደረግን በኋላ ነው።
ስለዚህ ቀደም ተከተሉ እንደዚህ መሆን አለበት፤ 1ኛ) እርስ በርስ ያለንን ጉዳዮች ተወያይተን ጨምቀን ወደ የምንተመመንበት የምንስማማበት መድረስ። ይህ ስራ ዓመታት ሊፈጅ ይችላል። 2ኛ) ከዚያ በኋላ የመሰረትነውን መተማመን፣ ስምምነትና አንድነት ተጠቅመን ህወሓትን መፎካከር።
ለማጠቃለል ትኩረታችን ህውሓትን ከስልጣን ማውረድ ከሆነ በመጀመሪያ በመካከላችን አንድነት መፍጠር አለብን። አንድነት ለመፍጠር እርስ በርስ በሁሉም መልኩ እንዳንተማመን፤ እንዳንስማማ እና አንድነት እንዳንፈጥር የሚያደርጉንን ጉዳዮች በደንብ መወያየት አለብን። ከዚያም የገነባነውን አንድነት በመጠቀም ህወሓትን ለማሸነፍ እንችላለን።
ስለዚህ ስለ አማራ ማንነት፤ የጎሳ አስተዳደር፤ የትግል ስልት፤ እና ሌሎች በርካታ የማያስማሙን ወይም ማሻሻል የሚኖሩብን ጉዳዮችን መወያየት ህወሓትን ለማሸነፍ የግድ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ቅድመ ሁኔታ ነው።
እዚህ ላይ ለመጨመር ያህል በኔ እይታ ህወሓትን ከስልጣን ማስወገድ አንደኛ ላማችን ሊሆን አይገባም። አላማችን ሰላም፤ ፍትሕ፤ ፍቅር፤ መልካም አስተዳደር ማምጣት ነው። ሀውሓትንም ማስወገድ የምንፈልገው የነዚህ ተቃራኒ ስለሆነ ነው። ግን ህወሓትን ከስልጣን አባረን የሱን ቢጤ የሆነ መንግስት አንፈልግም። ከላይ የዘረዘርኩት አካሄድ ግን እንደዚህ እንዳይሆን የሚከላከል ነው! ስለ አገራችን ያለንን ራዕይ ላይ ቀድሞ በደምብ ተወያይተን ከተስማማን ከተማመንን አምባገነን ከመካከላችን አምባገነን ሊፈጠር አይችልም አምባገነን የአለመግባባት የአለመስማማት ውጤት ስለሆነ። ስለዚህ ካሁን ወድያ ይህ ዋና ስራችን ላይ እናቶኩር።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Monday, 26 March 2018
Sunday, 25 March 2018
ስለ «አማራ» ያከው ውይይት
ስለ አማራ ማንነት ይሆን ወይም በሌላም አርእስት ስነወያይ ነገሮችን በጥራት እንድናይ ለመወያየት ለመከራከር ለመተቻቸት ብቻ ሳይሆን ግብ ለመምታት ከሆነ ከውይይታችን ከአስተሳሰባችን በስተ ጀርባ ዙርያውን ያለውን ሁኔታ አስተሳሰባችን መመልከት አለብን። ይህን ለማድረግ ዘንድ እስቲ እነዚህን ነጥቦች በደምብ እንመልከታቸው።
1. ሁሉም ውይይት "context" (ዐውደ ሁኔታ?) አለው። ዛሬ ያለው ሁኔታ ምንድነው? 60 ዓመት በፉት ይህ ውይይት ይኖር ነበር ቢኖርስ ምን ይመስል ነበር። 2. ለውይይቱ ምን አይነት አመለካከት ርዕዮት ዓለም እምነት ወዘተ ይዘን ነው የምንከራከረው? በጎሰኝነት ("identity") ፒለቱካ እናምናለን? ወይም የአገር ብሄርተኖች ("nationalist") ነን? 3. የምንጠቀምበት ቋንቋ ቃላቶች ምን ትርጉም አላቸው? «ጎሳ» ምንድንደው? «ህዝብ» ምንድነው? «አማራ» ምንድነው? «ማንንነት» ምንድነው?
4. የውይይታችን አላማ ምንድነው? ውይይቱን ማሸነፍ ነው? መስማማት ነው? እውነት ላይ መድረስ ነው?
5. የጠቅላላ አላማችን ምንድነው? ከአገራችን ሽኩቻ አድሎ ኢፍትሃዊነት እንዲጠፋ ሰላምና ፍትህ እንዲኖር ነው? ህወሓትን ከስልጣን ማውረድ ነው? ስልጣን መያዝ ነው? ጥሩ የሚመስለንን ሥርዓትን ማስፈን ነው?
6. ውይይታችን አቋማችን ከህዝቡ ዝንባሌ ጋር በተወሰነ ድረጃ ብቻ ቢሆንም ይሄዳል ወይ? ይህ ታላቅ ጥያቄ ነው። የ«ፌስቡክ» ብቻ ውይይት ነው? የልሂቃን ብቻ ውይይት ነው? የአዲስ አበባ ብቻ ውይይት ነው? የተማሪዎች? ወይም ከብዙኃኑ ምካከል ይህ ጉዳይ እንደ ቁም ነገር ይቆጠር ይሆን?
ሁላችንም እራሳችንን እነዚህን ጥያቄዎች ጠይቀን በአግባቡ መልሰን ነው ፍሬአማ ውይይት ሊኖርን ይሚችለው።
እስቲ የኔን መልሶች ልስጣችሁ፤
1. ዛሬ የምዕራባዊ የማርክሲዝም የጎሳ ወይም ብሄሮች አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ በደምብ ሰክኗል። በ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ተማሪዎቻችን ወደ ውጭ አገር ትምሕርትቤት ሄድው ያመጡት ርዕዮት ዓለም አገር ውስጥ መሰረት ጥሎ ጭርሽ ህገ መንግስታችንን በክሎታል የፖለቲካ መዋቀራችንን በይኗል። በመሀበረሰብ ደረጀ በፊት ከ«ልሂቃን» ያልወጣ አስተሳሰብ አሁን አማራ ኦሮሞ ሲዳማ ትግሬ ብዙኃኑም ያውቀዋል። ግን በትክክሉ ምንድነው የሚያውቀው? ቋንቋ ነው? «ዘር» ነው? «ቦታ» ነው? ማንነት ነው? የፖለቲካ ክፍል ነው? ብዚህ ዙርያ የተለያዩ አመለካከቶች ቢኖሩም አብዛኞቻችን «አማራ» የሚለውን ቃል ድሮ የማንጠቀምበት ዛሬ እንጠቀምበታለን። ድሮ የፖለቲካ ትርጉም ያልነበረው ዛሬ አለው። ዛሬ ሰዎች በአማርነት ይከሰሱበታል። ይወነጀሉበታል። አንዳንዱ አማራ በመሆኔ ተጎጂ ነኝ ብሎ ያስባል። እጨቆናለሁ መብት የለኝም የሚል አለ። ባጭሩ ይህ ሁኔታ ላይ ነው ዛሬ የምንገኘው።
2. ማንነት የሰው ተፈጥሮ ባህሪ ነው ብዬ አምናለው። በመንደር ካልሆነ በጠቅላይ ግዛት ካልሆነ በጎሳ ካልሆነ በአገር ሁላችንም አንዱ የማንነታችንን ክፍል ይህ ነው። እስቲ አንድ ምሳሌ እናስብ። አንድ ኢትዮጵያዊ አሜሪካ ለ20 ዓመት ኖሮ ዜግነት ተቀብሎ አሜሪካው ነኝ ይላል። ኢትዮጵያዊ ነኝም ይላል። ለምን ኢትዮጵያዊነቱን አይተወውም። ልም ልጆቹን የኢትዮጵያ ቋንቋ ያስተምራል ቢችልም የኢትዮጵያ ትምሕርትቤት ይልካል? ለመሆኑ አሜሪካና ኢትዮጵያ በሆነ ጉዳይ ቢቃረኑ ማንን ይሆን የሚደግፈው? ኢትዮጵያን ቢደፍግ ሌላው አሜሪካዊ ከሃዲ አይለውም ይሆን? ለሌላው አሜሪካዊ «ኢትዮጵያዊ-አመሪካዊ» ማለት ጎሳ ነው። አያችሁ የጎሳ ስሜት እንዴት የተፈጥሮ እንደሆነ። የተፈጥሮ ቢሆንም ብዙ ጎሳዎች ያሉበት አገር ውስት የጎሰኝነት ስሜት ከአገር ብሄርተኝነት ስሜት ከበለጠ የጎሳ ፉክክር ("ethnic competition") በፖለቲካ ምድር ውስጥ ያበዛና ለአገሪቷ ህልውና ለሰላም ለፍትህ አደገኛ ነው ይሚሆነው። ይህን ነው ዛሬ በኢትዮጵያ የምናየው። ይህ ምክነያት የአገር ብሄርተኛ ነኝ። ማለት ለሁላችን ሰላምና ለአገሪቷ ብልጽግና የጎሰኘት ስሜት ከአገር ስሜት በታች መሆን አለበት ብዬ ነው የማምነው። «ኢትዮጵያዊ ነኝ ቀጥሎ ኦሮሞ» ትሩ ነው። «ትግሬ ነኝ ቀጥሎ ኢትዮጵያዊ» ወደ ችግር ይመራል።
3. «ጎሳ» «ህዝብ» «ማንንነት» «አማራ» ለሁላችንም የተለያዩ ትርጉሞች አላቸው። ከላይ እንዳልኩት ለኔ የሰው ልጅ ማንነት ውስጥ አንድ የአገር ወይ ጎሳ ወይ መንደር ወዘተ ክፍል አለ። ስለዚህ ለኔ ይህ የማንነት ክፍል በ«ኢትዮጵያዊነት» ወይም «ኦሮሞነት» ወይም «ኦሮሞ-ኢትዮጵያዊነት» ወይም «ኢትዮጵያ-አማራነት» ወይም «ጎጃምነት» ወይም «አፍሪካነት» ሊሞላ ይችላል። ግን ሰውው «ጎሳ» እና «ህዝብ» እና «አገር» ሲለይ የፖለቲካ አቋምን ነው የሚገልጸው። ለምሳሌ አውሮፓ ከትናንሽ የንጉስ ግዛቶች «ጎሳዎች» ወደ አገሮች ("nation state") ሲቀየር «ጎሳ» የኋላ ቀር ነው ብለው ሰየሙ። ግን በጎስኝነት ዘመን የሚያራምዱት ጥላቻን ጦርነትን አሁን በ«አገር» ደረጃ በከፍ ያለ አቀም አራመዱት! ወደ «አማራ» የምንለው ቃል እንምጣ። የቃላቱ ትርጉም በመቶዎች ዓመታት እነደተቀየሩ ግልጽ ነው። የታሪቅ መጽሐፍቶች የድሮ አጠቃቀም ካሁኑ እንደሚለው ያሳያሉ። በቅርብ ዓመታት እራሱ ለምሳሌ ከሃረር እስከ ሸዋ መካከል «ነባር» ሙስሊም ኦሮሞዎች በቀር ሌላው «ክርስትያን» ነበር የሚባለው። ግን ነገሮች ይቀየራሉ። አሁን ከላይ እንደጠቀስኩት የማርክሲዝም ፖለቲካ ሰፍኖ ሁላችንም አማራ እንላለን ወይም ታግለን እራሳችንን እንቆጥባለን።
4. ስወያይ በተቻለ ቁጥር እውነት ላይ ለመድረስ ነው የምወያየው። አዎን አንድ አንድ ጊዜ ፍተናው ያሸንፈኛልና ትቢት ተሞልቼ ማሸነፍ ፈልጋለው አቋሜ ትክክል ቢሆንም ባይሆንም። ውይም ፈርቼ ወይም ለይሉኝታ መስማማት እፈልጋለሁ ስምምነት በውሸት የተመሰረተ ቢሆንም። ግን ደካማ ወገኔን ትቻ አላማየ እውነት ነው። ባልወደውም። ለምን እውነንት? እውነት ነው ለሁሉም የሚበጀው። አላማ እውነት ነው ማለት ለታክቲክ ወይም ለጊዜያዊ ሰላም ቁስል እስኪድን ወዘተ ተብሎው ዝም አይባልም ወይም አይዋሽም ማለት አይደለም። ገን የመጨረሻ ግቡ እውነት ነው።
5. እኔ ሰላምና ፍትህ ነው የምወደው። (አድሎ ሙስና አይኖር ማለት ፍትህ ይኑር ነው።) ሰው እንዳይጎዳ። ሰው ሌላውን ጉዳ እንዳይባል መጉዳት ከመጎዳት ይበልጥ ጎጂ ነውና። ከዛ ውጭ ማን ይግዛ ምን ሥርዓት ይኖር ግድ የለኝም። እንደ ኦርቶዶክስ ክርስትያንነቴ ወደ ንጉሳዊ አገዛዝ አደላለው ከሰው ወይም ሰዎች ይልቅ እግዚአብሔር መሪ ቢሾም ይሻላል ስለሚመስለኝ። ግን ይህ ሀሳብ ለ«ዘመናዊ» ሰው አይገባውም እንተወው። ለማንኛውም ሰላም ፍቅር ፍትህን የሚያበዛ ትልና ሽኩጫን የሚያሳንስ ሥርዓት ከተባለ ከሞላ ጎደል ምን መምሰል እንዳለበት እናውቃለን።
6. እውነቱን ለመናገር ይህ ሀአማራ ማንነት ጉዳይ ከዲያስፖራና ፌስቡክ ውች ያን ያህል ትኩረት ያለው አይመስለኝም። በኔ እይታ (በኢህአዴግም ይመስለኛል!) ያለፉት ሶስት አራት ዓመት የህዝብ ተቃውሞ በመጀመርያ ደረጃ አድሎን በተለይ የ«ትግሬ አድሎን» ተመስርቶ ነው። ይህ በአማራ ክልል የተካሄደውን ተቃውሞንም ያካትታል። መፈከሩ ትግሬ አይግዛን ነው እንጂ አማራ ይከበር አይመስለኝም። በግሌ ያየሁት የሰማሁት እንደዚህ ነው። እንደሚመስለኝ ዛሬ አማራ የምንለው ህዝብ አሁንም በጣም ወደ ኢትዮጵያዊነት ያመዝናል ከአማራነት ይልቅ። ነገ አማራ ክልል በንዚን ቢገኝ ለአማራ ክልል ብቻ ይውል የሚል ጥቂት መሰለኝ። ትግሬ ምንም አያገኝ የሚሉ ብዙ ይኖራሉ ያሳዝናል እንጂ። ጥቃት ያመታው ችግር ነው። ግን አብዛኛው አማራ በለጸገች ከማለት ኢትዮጵያ በለጸገች ነው የሚለው።
እሺ በመጨረሻ ለ«ትግሉ» ተብሎ በአማራነት መታገሉ አይሻልም ወይ የሚለው ከመምህር ሐዚም አስራት ወልደየስ ዘመን ጀምሮ ያለ ጥያቄ አለ። ያኔ አልሰራም ከላይ እንደጠቀስኩት «አማራ» የሚባለው ስሜቱ ከአማራነት ይልቅ ኢትዮጵያዊነት እጅግ ስለሚበልት። አናሳ ብሄርም ስላልሆነ። የተጭቋኝ ስሜትም ስላልነበረው። ዛሬ ሁኔታው ጠቀይሯል በተወሰነ ደረጃ ግን አሁን ስኬታማ የ«አማራ የጎሳ» ትግል ለማካሄድ የህዝቡ ሁኔታ የሚፈቅድ አይመስለኝም።
እውነት ነው እንደዚህ አይነቱ ትግል ያስጎመዣል። እነ ሻዕብያ ህወሓት ኦነግ እንዳረጉት ስኬታማ ትግል ማድረግ ነው። የጎሳን የተፈጥሮ የማሰባሰብ ኃይል መጠቀም ነው። ግን ሁኔታው ካልፈቀደ ህዝቡ ማንነቱ ከዚ አይነት አስተሳሰብ ጋር የማይሄድ ከሆነ አሁንም አይሳካም። ሰከን ብሎ ማሰብ ነው።
በመጨረሻ ላስታውሳችሁ የምወደው ምሳሌዎቹ ወይም "template" የሆኑት እነ ሻዕብያ ህወሓት እጅግ አናሳ ስለሆኑ ለማሸነፍ ጎሰኝነትን ግድ መጠቀም አለብን ብለው ያምኑ ነበር። ግን እስካማውቀው ኢ-ህወሓት የሆንነው ወይም «ተቃዋሚ» የሆንነው የአገሪቷ 90% ወይም 80% ወይም 70% ነን። የጎሰኝነት የፖለቲካ ኃይል መሰብሰብያ "ethnic leverage" አስፈላጊ ነው ልንል አይገባም። ትንሽ የፖልቲካ ብስለት ትብብር አብሮ መስራት መተማመን ጉዳዩን ትላንት ይጨርሰው ነበር።
Thursday, 22 March 2018
የመሬት ፖሊሲ በጸንፈኛ ፖለቲከኞቻችን እጅ
English version: https://asfawdarguemeshal.blogspot.ca/2017/05/our-radical-politicians-land-to-ruler.html
በቅርብ ጊዜ ከዚህ ዓለም የተለዩት የኃይለ ሥላሴ የህግ አማካሪ የነበሩት ተሾመ ገብረማርያም በቃለ ምልልስ እነዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፤ «መሬት ለአራሹ» ነበር ያልነው፤ «መሬት ለመንግስት» ሆኖ ቀረ። የ«መሬት ለአራሹ» የሚባለው ፖሊሲ አላማው ከባላባት «ተከራይቶ» የሚያርሰውን መሬት ለጪሰኛው መስጠትና የመረቱ ባለቤት ማድረግ ነበር። የኃይለ ሥላሴ መንግስት ይህን ፖሊሲ ለማጽደቅ ቢሞክር በፖለቲካ በፍትህ በአፈጻጸም ደረጃ ችግሮች ያጋጥሙት ነበር። ሆኖም ለነበረው ኢፍትሃዊ ሥርዓትና ከነበረው የገበሬውችግር አንጻር ይህ «መሬት ለአራሹ» ፖሊሲ ትክክል ተገቢ አስተዋይና መጠነኛ እርምጃ ይሆን ነበር። በተቃራኒው ከደርግ ጀምሮ የዋለው «መሬት ለመንግስት» ፖሊሲ የመሬት ባለቤትነት ሙሉ በሙሉ ለመንግስት ማስተላለፉ ለነበረው የመሬትችግር የከረረና ጸንፈኛ መልሰ ነበር። የፖለቲካ ልሂቃኖቻችን ተገቢውን መጠነኛውን እርምጃ ከመውሰድ አክራሪና ጸንፈኛውን እርምጃ ወሰዱ።
የሚያሳዝነው ነገር በኢትዮጵያ የቅርብ ዘመን ታሪቅ ልሂቃኖቻችን በቁልፍ ጊዜዎች በተደጋጋሚ ወደ ጸንፍ ማድላታቸው ነው። በተለይ የኃይለ ሥላሴ «ልጆች» የሆኑት በሳቸው ጊዜ ከ1950 ወዲህ የቀለም ትምሕርት የተማሩት ልሂቃን በተደጋጋሚ ጸንፈኛ የፖለቲካ ውሳኔዎች በመወሰን አገራችንን ወደ ከባድ ያልተጠበቁ አደጎች መርተዋታል። ኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ ለነዚህ አጉል ውሳኔዎች ዋጋ እየከፈለች ነው።
ከዚህ ጽሁፍ የኢትዮጵያን ህዝብ የጎዳው እስካሁንም እያሰቃየው ያለው የመሬት ባለቤትን መንግስት ያደረገው የፖሊሲ ውሳኔን እንመልከት። ይህ ፖሊሲ ባጭሩ ስድስት ችግሮች ፈጥሯል አባብሷል፡
1. የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር
2. አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት
3. ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች
4. ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን
5. ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት
6. የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ
እነዚህ ችግሮች እንዴት ተፈጠሩ? በመጀመርያ መሬት የመንግስት መደረጉ ገበሬዎች መሬታቸውን መሸጥ መለወጥ ስለከለከላቸው የገጥር ህዝብን ከሞላ ጎደል እስረኛ አድርጓቸዋል። ገበሬዎችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ከተማ መዘዋወር እንዳይችሉ ከልክሏቸዋል። ይህ እንዴት እንደሆነ በምሳሌ ላስረዳ።
ዐምዴ የሚባል አንድ ገበሬ በ1968 በቂ የሆነ ወደ ሰባት ሄክታር የሚሆን እርሻ ነበረው። ዐምዴ ቤተሰቡን ይዞ ወደ ከተማ መዘዋወር ይፈልጋል። ግን ይህን ለማድረግ የመቋቋምያና ስራ መጀመርያ ገንዘብ ያስፈልገዋል። ይህን ገንዘብ ለማግኘት መሬቱን በሙሉ ወይም በከፊል መሸጥ አለበት መሬቱ ዋና ንብረቱ ስለሆነ። ያኔም አሁንም የኢትዮጵያ ገበሬዎች ከመሬታቸው ሌላ ብዙ ዋጋ ያለው ንብረቶች የላቸውም።
ግን የዐምዴ መሬት የመንግስት ነው ተብሎ ስለተሰየመ መሸጥ መለወጥ በሱ መበደርም አይችልም። ስለዚህ ለከተማ ኑሮ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ማግኘት አልቻለም። በተጨማሪ መሬቱን ትቶ ቢሄድ ደግሞ ይወሰድበታል። ስለዚህ በተዘዋዋሪ ዐምዴ ወደ ከተመ መዘዋወር እንዳይችል ተከለከለ ማለት ነው። 1) መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ ለመሄድ ገንዘብ ማግኘት አይችልም። 2) እንደምንም አድርጎ ገንዘብ አግኝቶ ቢሄድም ሀሳቡን ቀይሮ ልመለስ ቢል ምሬቱ ተወስዶበት ነው የሚያገኘው! ይህን ሁሉ ስለሚያውቅ ዐምዴ ወደ ከተማ መሄድን አያስበውም። ሌሎቹም የኢትዮጵያ ገበሬዎች እንደ ዐምዴ ከተማ መሄድ ቢፈልጉም ገጠር ቁች ብለዋል። በዚህ የመሬት ፖሊሲ ምክነያት ከ1975 እስከ ቅርቡ ጊዜ ገበሬዎች በሚገባው ቁጥር ወደ ከተማ አልፈለሱም።
በዐምዴ ታሪክ እንቀጥልና የለት ኑሮው እንዴት ነበር ብለን እንጠይቅ። እንደ አብዛኛው የገጠር ነዋሪ ዐምዴ ብዙ ልጆች ወልዷል። ሰባት ልጆች ወልዷል። በ2000ዓ.ም. በገጠር የሚኖሩ ሴቶች በአማካኝ 6.5 ልጆች ነበር የሚወልዱት በአዲስ አበባ 2.2 ነበር። ይህ በከተማና በገጠር ያለው የልጅ መውለድ መጠን ልዩነት ዓለም አቀፍ ያለ ነው፤ የገጠር በአንጻሩ ብዙ ይወልዳል የከተማ አይወልድም። ደሃ ባንጻሩ ብዙ ይወልዳል ሃብታም አይወልድም። ይህ ዓለም በሙሉ የሚታይ ሁኔታ ነው።
የዐምዴ ልጆች ሲያድጉ መሬቱን ከፋፍሎ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሄክታር አወረሰ። ከብዙ ዓመታት በኋላ ልጆቹም እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወለዱና አንድ ሄክታር መሬቶቻቸው ጠበቡ። ይህ ችግር በአገር አቀፍ ደረጃ እየባሰ ሄዷል። ዛሬ በኢትዮጵያ የአማካኝ የእርሻ ይዞታ ከአንድ ሄክታር በታች ነው። የገጠር መሬት ተጨናንቋል።
በ1968 የመሬት አዋጁ ሲታወጅ ከ28 ሚሊዮን የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ወደ 85% የገጠር ነዋሪ ነበር። 40 ዓመት በኋላ በ2008 ከ97 ሚሊዮን ጠቅላላ የህዝብ ቁጥር 80% በገጠር ይኖራል። በ40 ዓመት በገጠር የሚኖረው የህዝብ መጠን ከ85% ወደ 80% በአምስት ብቻ ነው የቀነሰው። ግን የገጠር ነዋሪዎች ከላይ እንደጠቀስኩት በአማካኝ 6.5 ልጅ ስለሚወልዱ ጠቅላላ የገጠር የህዝብ ቁጥር ናረ። ለምን? ለ40 ዓመት ገበሬዎች ሲፈልጉ መሬታቸውን ሽጠው ወደ ከተማ መዘዋወር ስላልቻሉ ከሚገባው በታች ቁጥር ነው ወደ ከተማ የፈለሰው። የመሬቱ ፖሊሲ ባይኖር ኖሮ የገጠሩ ሰው ዓለም ዙርያ እንደሚታየው በራሱ በተፈጥሮና በነፃነት መንገድ ቀስ በቀስ ውደ ከተማ ይፈልስ ነበር። ይህ የተፈጥሮ መጠነኛ ፍልሰት በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ባይታገድ ኖሮ የገጥር የህዝብ ቁጥር ዛሬ ከ80% ፋንታ ምናልባት ወደ 65% ወይም ከዛም ዝቅ ብሎ ይወርድ ነበር።
በዚህ መልክ የገጠሩ የህዝብ ቁጥር ቅስ በቅስ እየወረደ ቢሄድ የከተማ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ የአገሪቷ የጠቅላላ የህዝብ ቁጥር እንዳሁኑ አይንርም ነበር። ምክነያቱ የከተማ ሰው እንደ ገጠሬው ያህል አይወልድም። በዐምዴ ምሳሌ ከቀጠልን ወደ ከተመ ቢዘዋወር ኖሮ ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ከሚወልዱ ከተማ ስለሚኖሩ እንደሌሎች የከተማ ነዋሪዎች ሁለት ይወልዱ ነበር። ግን ወደ ከተማ እንዳይመጣ «ተከልክሎ» ዐምዴ ከገጠር ታስሮ ቆየ። በዐምዴ ምሳሌ እንደምናየው ይህ «የገጠር እስርቤት» መተንፈስ ስላልቻለ የህዝብ ቁጥሩ በ40 ዓመት ከ24 ሚሊዮን ወደ 77 ሚሊዮን ገባ። ይህ የገጠር/ከተማ የህዝብ መጠን አላግባብ ከፍ ያለ በመሆኑ ነው የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር በኢተፈጥሮ መንገድ የናረው እስካሁን የሚንረው።
ወደ ዐምዴ ቤተሰብ እንመለስ። ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወልደው የአንድ ሄክታር መሬታቸውን ለሰባቱ መከፋፈል አይችሉም አንድ ሰባተኛ ሄክታር ለአንድ ቤተሰብን በቂ ስላልሆነ። ስለዚህ መሬታቸውን ለአንድ ልጃቸው ያወርሱትና ሌሎቹ ስድስት ልጆቻቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን ጨርሰው ግድ ወደ ከተመ መዘዋወር ይኖርባቸዋል። አሁን በአገራችን የምናየው ሁኔታ ይህ ነው። የጠበቅነው ግን መንግስቶቻችን ችላ ያሉት የመሬት መጥበብ ደርሷል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ገበሬዎች ለአንድ ወራሽ ብቻ የሚበቃ መሬት ነው ያላቸውና ሌሎች ልጆቻቸው ወደ ከተማ እየፈለሱ ነው። አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ይህ ነው ምክነያቱ። ለ40 ዓመት የተጠራቀመ ፍልሰት ነው አሁን ባንዴ የሚታየው። ግና ይቀጥላል።
ከዐምዴ ጋር እንቀጥል። ዐምዴ እግዚአብሔር ይባርከው እንጂ ጎበዝ ገበሬ አይደለም። ሙያውም ፍላጎቱም የለውም ግን ቤተሰቡን ለማስተዳደር ብሎ ያርሳል። ጎረቤቱ ገመቹ ግን እጅግ ጎበዝ ገበሬ ነው። የግብርና ንግዱን ማስፋፋት ይፈልጋል። ግን በመሬት ፖሊሲው ምክነያት እንዴት አድርጎ ተጨማሪ መሬት ይግዛ። ዐምዴ በደስታ መሬቱን ይሸጥለት ነበር ገመቹም ችሎታውን ተማምኖ ጥሩ ዋጋ ይሰጠው ነበር ግን አይፈቀድም። ስለዚህ የሚፈቀደውን አደረጉ ገመቹ ከዐምዴ የተወሰነ መሬት በየዓመቱ እየተከራየ ማረስ ጀመረ። ገመቹ ጉድጓድ መቆፈር ዛፍ መትከልና ተመሳሳይ የረዥም እቅድ ስራዎችና ኢንቬስትሜንቶች ማድረግ ይፈልጋል ግን መሬቱ የሱ ስላልሆነ ኪራዩም በየዓመቱ የሚታደስ ስለሆነ ስለረዥም እቅዶች ማሰብ አይችልም። ገመቹ ከሌሎች ጎረቤቶቹ ተጨማሪ መሬት ገዝቶ ስራውን አስፋፍቶ ምናልባት በትራክተር ማረስ፤ ሙያውንም ማዳበር፤ ስለ ፍራፍሬ ማምረት መማር፤ ወዘተ ያልማል። ግን ችሎታ ቢኖረውም በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ምኞቶቹን በተግባር መዋል አልቻለም።
ገመቹ ከዐምዴ በተከራየው መሬት 20 ኪንታል በሄክታር ጠፍ ያመርታል። ዐምዴ 10 ነበር የሚያመርተው። ገመቹ የዐምዴ መሬት ሙሉ በሙሉ ሰባቱንም ሄክታር ገዝቶ ጠፍ ቢተክልበት ኖሮ በዐምዴ 70 ኪንታል የሚያበቅለው መሬት በገመቹ እጅ 140 ኪንታል ያበቅል ነበር። የአካባቢው የምርት መጠን ይጨምር ነበር። ገመቹ ደግሞ የሚያገኘውን ትርፍ ተጠቅሞ መሬቱ ላይ ኢንቬስት አድርጎ የግብርና ንግዱን የምርት መጠኑን ይበልጥ ያሻሽል ነበር። የአካባቢው የጠፍ ምርት ይጨምር ነበር የጤፍ ዋጋ ደግሞ ይቀንስ ነበር። ዐምዴ ከተማ ገብቶ ጠፍ በመጠነኛ ዋጋ ያገኝ ነበር።
ገመቹ ላይ የደረሰው የስራ ክለላ ወይም የማስፋፈትና ማደግ ክለላ የኢትዮጵያ መንግስታት በአገሪቷ ገበሬዎች ላይ ያሳደሩት አሳዛኝ ድርጊት ነው። ገበሬዎች ስራቸውን እርሻቸውን ንግዳቸውን እንዳያሰፋፉ በማገድ መንግስት የገበሬዎቻችን «የሰው አቅም» (human capital) አፍነዋል። ይህ የኤኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሥነ ልቦና የፖለቲካ የማኅበራዊ ተጽዕኖ ገበሬዎች ላይ አሳድሯል። ከሁሉም የግል ነጋዲዎች ተለይተው ገበሬዎች ነፃነት እንዳይኖራቸው ንግዳቸውን ማስፋፋት እንዳይችሉ ተደርገዋል። በዚህ ምክነያት በሙያ ችሎታም በሙያ ትምሕርትም እንዳይሻሻሉ ተደርገዋል። እንደነበሩት እንዲቆዩ ተደርገዋል። እስቲ አንድ ሜካኒክ ስራውን ንግዱን ከማስፋፋት በህግ ቢከልከል እናስበው። ከአንድ መኪና በላይ የሚችል ቦታ ሊኖርህ አይችልም ቢባል። ይህ ሜካኒክ መቼም የችሎታውን አቅም ሳያሟላ ይቆያል። ወይም አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር ስራ መቀየር አትችልም ከአንድ ርዕስ ውጪ ጥናት ማካሄድ አትችልም ቢባል። ይህ መምህር በሙያው የተም አይደርስምና እራሱን ለማሻሻል አይጥርም። ስራውም እየሰለቸው ይሄዳል። ስለዚህ የመሬት ፖሊሲው ለገበሬዎች ኮምዩኒዝም ለሌሎች ካፒታሊዝም ነው ያደነገገው።
ይባስ ተብሎ መንግስቶቻችን የመንግስት ያልሆኑት ድርጅቶችም (ንጂኦ) ገበሬዎችን ወደታች አድርገው በንቀት ይመለከታሉ። እንደ ሞግዚት የሚያስፈልጋቸው ደንቆሮች ያይዋቸዋል። ከላይ እንዳልኩት ይህ የሆነው ገበሬዎች አቅማቸውን እውቀታቸውን ከማሻሻል ስለተገደቡ ነው። መንግስት እራሱ በነፃነት እንዳይሰሩ ስለከለከላቸው ነው። እንደ ጥሩ ኮምዩኒስቶች መንግስት ዋናውን የምርት ግበዓት የሆነውን መሬት አፍኖ ሌሎችን ግብአቶች እንደ ምርጥ ዘር ማዳበርያ ተባይና አረም ምጥፍያ የ«ኤክስቴንሽን» ትምሕርት ወዘተ በመጨመር የአገሪቷ የምርት መጠንን መጨመር ሞከረ። ግን አልሰራም።
ዛሬም በኢትዮጵያ የሰብል መርት በሄክታር ዝቅተኛ ነው። የምግብ ዋጋ ከሌሎች ታዳጊ ዓገሮች ውድ ነው። ወተት እንቁላል ቂቤ ሥጋ ማር ከአደጉ አገሮች ይልቅ ኢትዮጵያ ይወደዳሉ። የሰብል ዋጋ ውድ ቢሆንም የግብርና የንግድ ክፍል ተስፋፍቶ ያለውን ፍላጎት በአግባብ ማስተናገድ አልቻለም። ፈላጊ እየበዛ ሲሄድ አቅራቢ በቂ ማቅረብ አቅቶታል። ገበሬው ኢንቬስት ማድረግ አልቻለም። ለዚህ ነው የእህል የምግባ የዋጋ ግሽበቱ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሆነውና መንግስትን የሚያስጨንቀው።
ወደ ዐምዴ እንመለስ… ኢትዮጵያ በ10 ዓመት አንዴ የሚደርስባት ድርቅ መጥቶ የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታሮቻቸው በጣም አነስተኛ መርት ያገኛሉ። ዐምዴ ሰባቱን ሄክታር በሚያአርስበት ጊዜ ድርቅ ቢኖርም የሰባት ሄክታሩ ምርት ብዙ ስለነበር ለድርቅ ጊዜ በቂ የተከማቸ እህል ነበረው። አሁን ግን የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታር እጅ ወደ አፍ ስለሚኖሩ የአንድ ዓመት ምርታቸው ከቀነሰ በቂ አይኖራቸውም። ስለዚህ ሰባቱም የዐምዴ ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ምግብ እርዳታ ተሸጋሸጉ።
ታሪኩ በዚ ይጠቃለላል፤ የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ። ሁሉም ችግሮች ብያንስ በከፊሉ የ1968 የመሬት አዋጁ ውጤቶች።
የዚህ ፖሊሲ ጎጂ ውጤቶች ያልበሰሉ ጸንፈኛ የፖለቲካ ልሂቃን በችኩልነታቸው አገሪቷ ላይ ሊያመጡ የሚችሉትን ጉዳት ያሳያል። ከጽንፈኝነት መካከለኛውን መንገድ መያዝ ይሻላል። የዛሬም ግዥዎቻችን ከዚህና ሌሎች ታሪኮች ተምረው ሌላውን ጸንፈኛ የአገራችን ፖሊሲ የጎሳ አስተዳደርን እንደገና ቢያስቡበት ይሻላል።
በቅርብ ጊዜ ከዚህ ዓለም የተለዩት የኃይለ ሥላሴ የህግ አማካሪ የነበሩት ተሾመ ገብረማርያም በቃለ ምልልስ እነዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፤ «መሬት ለአራሹ» ነበር ያልነው፤ «መሬት ለመንግስት» ሆኖ ቀረ። የ«መሬት ለአራሹ» የሚባለው ፖሊሲ አላማው ከባላባት «ተከራይቶ» የሚያርሰውን መሬት ለጪሰኛው መስጠትና የመረቱ ባለቤት ማድረግ ነበር። የኃይለ ሥላሴ መንግስት ይህን ፖሊሲ ለማጽደቅ ቢሞክር በፖለቲካ በፍትህ በአፈጻጸም ደረጃ ችግሮች ያጋጥሙት ነበር። ሆኖም ለነበረው ኢፍትሃዊ ሥርዓትና ከነበረው የገበሬውችግር አንጻር ይህ «መሬት ለአራሹ» ፖሊሲ ትክክል ተገቢ አስተዋይና መጠነኛ እርምጃ ይሆን ነበር። በተቃራኒው ከደርግ ጀምሮ የዋለው «መሬት ለመንግስት» ፖሊሲ የመሬት ባለቤትነት ሙሉ በሙሉ ለመንግስት ማስተላለፉ ለነበረው የመሬትችግር የከረረና ጸንፈኛ መልሰ ነበር። የፖለቲካ ልሂቃኖቻችን ተገቢውን መጠነኛውን እርምጃ ከመውሰድ አክራሪና ጸንፈኛውን እርምጃ ወሰዱ።
የሚያሳዝነው ነገር በኢትዮጵያ የቅርብ ዘመን ታሪቅ ልሂቃኖቻችን በቁልፍ ጊዜዎች በተደጋጋሚ ወደ ጸንፍ ማድላታቸው ነው። በተለይ የኃይለ ሥላሴ «ልጆች» የሆኑት በሳቸው ጊዜ ከ1950 ወዲህ የቀለም ትምሕርት የተማሩት ልሂቃን በተደጋጋሚ ጸንፈኛ የፖለቲካ ውሳኔዎች በመወሰን አገራችንን ወደ ከባድ ያልተጠበቁ አደጎች መርተዋታል። ኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ ለነዚህ አጉል ውሳኔዎች ዋጋ እየከፈለች ነው።
ከዚህ ጽሁፍ የኢትዮጵያን ህዝብ የጎዳው እስካሁንም እያሰቃየው ያለው የመሬት ባለቤትን መንግስት ያደረገው የፖሊሲ ውሳኔን እንመልከት። ይህ ፖሊሲ ባጭሩ ስድስት ችግሮች ፈጥሯል አባብሷል፡
1. የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር
2. አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት
3. ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች
4. ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን
5. ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት
6. የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ
እነዚህ ችግሮች እንዴት ተፈጠሩ? በመጀመርያ መሬት የመንግስት መደረጉ ገበሬዎች መሬታቸውን መሸጥ መለወጥ ስለከለከላቸው የገጥር ህዝብን ከሞላ ጎደል እስረኛ አድርጓቸዋል። ገበሬዎችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ከተማ መዘዋወር እንዳይችሉ ከልክሏቸዋል። ይህ እንዴት እንደሆነ በምሳሌ ላስረዳ።
ዐምዴ የሚባል አንድ ገበሬ በ1968 በቂ የሆነ ወደ ሰባት ሄክታር የሚሆን እርሻ ነበረው። ዐምዴ ቤተሰቡን ይዞ ወደ ከተማ መዘዋወር ይፈልጋል። ግን ይህን ለማድረግ የመቋቋምያና ስራ መጀመርያ ገንዘብ ያስፈልገዋል። ይህን ገንዘብ ለማግኘት መሬቱን በሙሉ ወይም በከፊል መሸጥ አለበት መሬቱ ዋና ንብረቱ ስለሆነ። ያኔም አሁንም የኢትዮጵያ ገበሬዎች ከመሬታቸው ሌላ ብዙ ዋጋ ያለው ንብረቶች የላቸውም።
ግን የዐምዴ መሬት የመንግስት ነው ተብሎ ስለተሰየመ መሸጥ መለወጥ በሱ መበደርም አይችልም። ስለዚህ ለከተማ ኑሮ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ማግኘት አልቻለም። በተጨማሪ መሬቱን ትቶ ቢሄድ ደግሞ ይወሰድበታል። ስለዚህ በተዘዋዋሪ ዐምዴ ወደ ከተመ መዘዋወር እንዳይችል ተከለከለ ማለት ነው። 1) መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ ለመሄድ ገንዘብ ማግኘት አይችልም። 2) እንደምንም አድርጎ ገንዘብ አግኝቶ ቢሄድም ሀሳቡን ቀይሮ ልመለስ ቢል ምሬቱ ተወስዶበት ነው የሚያገኘው! ይህን ሁሉ ስለሚያውቅ ዐምዴ ወደ ከተማ መሄድን አያስበውም። ሌሎቹም የኢትዮጵያ ገበሬዎች እንደ ዐምዴ ከተማ መሄድ ቢፈልጉም ገጠር ቁች ብለዋል። በዚህ የመሬት ፖሊሲ ምክነያት ከ1975 እስከ ቅርቡ ጊዜ ገበሬዎች በሚገባው ቁጥር ወደ ከተማ አልፈለሱም።
በዐምዴ ታሪክ እንቀጥልና የለት ኑሮው እንዴት ነበር ብለን እንጠይቅ። እንደ አብዛኛው የገጠር ነዋሪ ዐምዴ ብዙ ልጆች ወልዷል። ሰባት ልጆች ወልዷል። በ2000ዓ.ም. በገጠር የሚኖሩ ሴቶች በአማካኝ 6.5 ልጆች ነበር የሚወልዱት በአዲስ አበባ 2.2 ነበር። ይህ በከተማና በገጠር ያለው የልጅ መውለድ መጠን ልዩነት ዓለም አቀፍ ያለ ነው፤ የገጠር በአንጻሩ ብዙ ይወልዳል የከተማ አይወልድም። ደሃ ባንጻሩ ብዙ ይወልዳል ሃብታም አይወልድም። ይህ ዓለም በሙሉ የሚታይ ሁኔታ ነው።
የዐምዴ ልጆች ሲያድጉ መሬቱን ከፋፍሎ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሄክታር አወረሰ። ከብዙ ዓመታት በኋላ ልጆቹም እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወለዱና አንድ ሄክታር መሬቶቻቸው ጠበቡ። ይህ ችግር በአገር አቀፍ ደረጃ እየባሰ ሄዷል። ዛሬ በኢትዮጵያ የአማካኝ የእርሻ ይዞታ ከአንድ ሄክታር በታች ነው። የገጠር መሬት ተጨናንቋል።
በ1968 የመሬት አዋጁ ሲታወጅ ከ28 ሚሊዮን የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ወደ 85% የገጠር ነዋሪ ነበር። 40 ዓመት በኋላ በ2008 ከ97 ሚሊዮን ጠቅላላ የህዝብ ቁጥር 80% በገጠር ይኖራል። በ40 ዓመት በገጠር የሚኖረው የህዝብ መጠን ከ85% ወደ 80% በአምስት ብቻ ነው የቀነሰው። ግን የገጠር ነዋሪዎች ከላይ እንደጠቀስኩት በአማካኝ 6.5 ልጅ ስለሚወልዱ ጠቅላላ የገጠር የህዝብ ቁጥር ናረ። ለምን? ለ40 ዓመት ገበሬዎች ሲፈልጉ መሬታቸውን ሽጠው ወደ ከተማ መዘዋወር ስላልቻሉ ከሚገባው በታች ቁጥር ነው ወደ ከተማ የፈለሰው። የመሬቱ ፖሊሲ ባይኖር ኖሮ የገጠሩ ሰው ዓለም ዙርያ እንደሚታየው በራሱ በተፈጥሮና በነፃነት መንገድ ቀስ በቀስ ውደ ከተማ ይፈልስ ነበር። ይህ የተፈጥሮ መጠነኛ ፍልሰት በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ባይታገድ ኖሮ የገጥር የህዝብ ቁጥር ዛሬ ከ80% ፋንታ ምናልባት ወደ 65% ወይም ከዛም ዝቅ ብሎ ይወርድ ነበር።
በዚህ መልክ የገጠሩ የህዝብ ቁጥር ቅስ በቅስ እየወረደ ቢሄድ የከተማ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ የአገሪቷ የጠቅላላ የህዝብ ቁጥር እንዳሁኑ አይንርም ነበር። ምክነያቱ የከተማ ሰው እንደ ገጠሬው ያህል አይወልድም። በዐምዴ ምሳሌ ከቀጠልን ወደ ከተመ ቢዘዋወር ኖሮ ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ከሚወልዱ ከተማ ስለሚኖሩ እንደሌሎች የከተማ ነዋሪዎች ሁለት ይወልዱ ነበር። ግን ወደ ከተማ እንዳይመጣ «ተከልክሎ» ዐምዴ ከገጠር ታስሮ ቆየ። በዐምዴ ምሳሌ እንደምናየው ይህ «የገጠር እስርቤት» መተንፈስ ስላልቻለ የህዝብ ቁጥሩ በ40 ዓመት ከ24 ሚሊዮን ወደ 77 ሚሊዮን ገባ። ይህ የገጠር/ከተማ የህዝብ መጠን አላግባብ ከፍ ያለ በመሆኑ ነው የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር በኢተፈጥሮ መንገድ የናረው እስካሁን የሚንረው።
ወደ ዐምዴ ቤተሰብ እንመለስ። ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወልደው የአንድ ሄክታር መሬታቸውን ለሰባቱ መከፋፈል አይችሉም አንድ ሰባተኛ ሄክታር ለአንድ ቤተሰብን በቂ ስላልሆነ። ስለዚህ መሬታቸውን ለአንድ ልጃቸው ያወርሱትና ሌሎቹ ስድስት ልጆቻቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን ጨርሰው ግድ ወደ ከተመ መዘዋወር ይኖርባቸዋል። አሁን በአገራችን የምናየው ሁኔታ ይህ ነው። የጠበቅነው ግን መንግስቶቻችን ችላ ያሉት የመሬት መጥበብ ደርሷል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ገበሬዎች ለአንድ ወራሽ ብቻ የሚበቃ መሬት ነው ያላቸውና ሌሎች ልጆቻቸው ወደ ከተማ እየፈለሱ ነው። አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ይህ ነው ምክነያቱ። ለ40 ዓመት የተጠራቀመ ፍልሰት ነው አሁን ባንዴ የሚታየው። ግና ይቀጥላል።
ከዐምዴ ጋር እንቀጥል። ዐምዴ እግዚአብሔር ይባርከው እንጂ ጎበዝ ገበሬ አይደለም። ሙያውም ፍላጎቱም የለውም ግን ቤተሰቡን ለማስተዳደር ብሎ ያርሳል። ጎረቤቱ ገመቹ ግን እጅግ ጎበዝ ገበሬ ነው። የግብርና ንግዱን ማስፋፋት ይፈልጋል። ግን በመሬት ፖሊሲው ምክነያት እንዴት አድርጎ ተጨማሪ መሬት ይግዛ። ዐምዴ በደስታ መሬቱን ይሸጥለት ነበር ገመቹም ችሎታውን ተማምኖ ጥሩ ዋጋ ይሰጠው ነበር ግን አይፈቀድም። ስለዚህ የሚፈቀደውን አደረጉ ገመቹ ከዐምዴ የተወሰነ መሬት በየዓመቱ እየተከራየ ማረስ ጀመረ። ገመቹ ጉድጓድ መቆፈር ዛፍ መትከልና ተመሳሳይ የረዥም እቅድ ስራዎችና ኢንቬስትሜንቶች ማድረግ ይፈልጋል ግን መሬቱ የሱ ስላልሆነ ኪራዩም በየዓመቱ የሚታደስ ስለሆነ ስለረዥም እቅዶች ማሰብ አይችልም። ገመቹ ከሌሎች ጎረቤቶቹ ተጨማሪ መሬት ገዝቶ ስራውን አስፋፍቶ ምናልባት በትራክተር ማረስ፤ ሙያውንም ማዳበር፤ ስለ ፍራፍሬ ማምረት መማር፤ ወዘተ ያልማል። ግን ችሎታ ቢኖረውም በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ምኞቶቹን በተግባር መዋል አልቻለም።
ገመቹ ከዐምዴ በተከራየው መሬት 20 ኪንታል በሄክታር ጠፍ ያመርታል። ዐምዴ 10 ነበር የሚያመርተው። ገመቹ የዐምዴ መሬት ሙሉ በሙሉ ሰባቱንም ሄክታር ገዝቶ ጠፍ ቢተክልበት ኖሮ በዐምዴ 70 ኪንታል የሚያበቅለው መሬት በገመቹ እጅ 140 ኪንታል ያበቅል ነበር። የአካባቢው የምርት መጠን ይጨምር ነበር። ገመቹ ደግሞ የሚያገኘውን ትርፍ ተጠቅሞ መሬቱ ላይ ኢንቬስት አድርጎ የግብርና ንግዱን የምርት መጠኑን ይበልጥ ያሻሽል ነበር። የአካባቢው የጠፍ ምርት ይጨምር ነበር የጤፍ ዋጋ ደግሞ ይቀንስ ነበር። ዐምዴ ከተማ ገብቶ ጠፍ በመጠነኛ ዋጋ ያገኝ ነበር።
ገመቹ ላይ የደረሰው የስራ ክለላ ወይም የማስፋፈትና ማደግ ክለላ የኢትዮጵያ መንግስታት በአገሪቷ ገበሬዎች ላይ ያሳደሩት አሳዛኝ ድርጊት ነው። ገበሬዎች ስራቸውን እርሻቸውን ንግዳቸውን እንዳያሰፋፉ በማገድ መንግስት የገበሬዎቻችን «የሰው አቅም» (human capital) አፍነዋል። ይህ የኤኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሥነ ልቦና የፖለቲካ የማኅበራዊ ተጽዕኖ ገበሬዎች ላይ አሳድሯል። ከሁሉም የግል ነጋዲዎች ተለይተው ገበሬዎች ነፃነት እንዳይኖራቸው ንግዳቸውን ማስፋፋት እንዳይችሉ ተደርገዋል። በዚህ ምክነያት በሙያ ችሎታም በሙያ ትምሕርትም እንዳይሻሻሉ ተደርገዋል። እንደነበሩት እንዲቆዩ ተደርገዋል። እስቲ አንድ ሜካኒክ ስራውን ንግዱን ከማስፋፋት በህግ ቢከልከል እናስበው። ከአንድ መኪና በላይ የሚችል ቦታ ሊኖርህ አይችልም ቢባል። ይህ ሜካኒክ መቼም የችሎታውን አቅም ሳያሟላ ይቆያል። ወይም አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር ስራ መቀየር አትችልም ከአንድ ርዕስ ውጪ ጥናት ማካሄድ አትችልም ቢባል። ይህ መምህር በሙያው የተም አይደርስምና እራሱን ለማሻሻል አይጥርም። ስራውም እየሰለቸው ይሄዳል። ስለዚህ የመሬት ፖሊሲው ለገበሬዎች ኮምዩኒዝም ለሌሎች ካፒታሊዝም ነው ያደነገገው።
ይባስ ተብሎ መንግስቶቻችን የመንግስት ያልሆኑት ድርጅቶችም (ንጂኦ) ገበሬዎችን ወደታች አድርገው በንቀት ይመለከታሉ። እንደ ሞግዚት የሚያስፈልጋቸው ደንቆሮች ያይዋቸዋል። ከላይ እንዳልኩት ይህ የሆነው ገበሬዎች አቅማቸውን እውቀታቸውን ከማሻሻል ስለተገደቡ ነው። መንግስት እራሱ በነፃነት እንዳይሰሩ ስለከለከላቸው ነው። እንደ ጥሩ ኮምዩኒስቶች መንግስት ዋናውን የምርት ግበዓት የሆነውን መሬት አፍኖ ሌሎችን ግብአቶች እንደ ምርጥ ዘር ማዳበርያ ተባይና አረም ምጥፍያ የ«ኤክስቴንሽን» ትምሕርት ወዘተ በመጨመር የአገሪቷ የምርት መጠንን መጨመር ሞከረ። ግን አልሰራም።
ዛሬም በኢትዮጵያ የሰብል መርት በሄክታር ዝቅተኛ ነው። የምግብ ዋጋ ከሌሎች ታዳጊ ዓገሮች ውድ ነው። ወተት እንቁላል ቂቤ ሥጋ ማር ከአደጉ አገሮች ይልቅ ኢትዮጵያ ይወደዳሉ። የሰብል ዋጋ ውድ ቢሆንም የግብርና የንግድ ክፍል ተስፋፍቶ ያለውን ፍላጎት በአግባብ ማስተናገድ አልቻለም። ፈላጊ እየበዛ ሲሄድ አቅራቢ በቂ ማቅረብ አቅቶታል። ገበሬው ኢንቬስት ማድረግ አልቻለም። ለዚህ ነው የእህል የምግባ የዋጋ ግሽበቱ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሆነውና መንግስትን የሚያስጨንቀው።
ወደ ዐምዴ እንመለስ… ኢትዮጵያ በ10 ዓመት አንዴ የሚደርስባት ድርቅ መጥቶ የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታሮቻቸው በጣም አነስተኛ መርት ያገኛሉ። ዐምዴ ሰባቱን ሄክታር በሚያአርስበት ጊዜ ድርቅ ቢኖርም የሰባት ሄክታሩ ምርት ብዙ ስለነበር ለድርቅ ጊዜ በቂ የተከማቸ እህል ነበረው። አሁን ግን የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታር እጅ ወደ አፍ ስለሚኖሩ የአንድ ዓመት ምርታቸው ከቀነሰ በቂ አይኖራቸውም። ስለዚህ ሰባቱም የዐምዴ ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ምግብ እርዳታ ተሸጋሸጉ።
ታሪኩ በዚ ይጠቃለላል፤ የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ። ሁሉም ችግሮች ብያንስ በከፊሉ የ1968 የመሬት አዋጁ ውጤቶች።
የዚህ ፖሊሲ ጎጂ ውጤቶች ያልበሰሉ ጸንፈኛ የፖለቲካ ልሂቃን በችኩልነታቸው አገሪቷ ላይ ሊያመጡ የሚችሉትን ጉዳት ያሳያል። ከጽንፈኝነት መካከለኛውን መንገድ መያዝ ይሻላል። የዛሬም ግዥዎቻችን ከዚህና ሌሎች ታሪኮች ተምረው ሌላውን ጸንፈኛ የአገራችን ፖሊሲ የጎሳ አስተዳደርን እንደገና ቢያስቡበት ይሻላል።
Wednesday, 21 March 2018
«ሴኩላሪዝም»
ትንሽ አመታት በፊት አንድ የመንግስት ስራተኛ የሆነ ዘመዴ የኦርቶዶክስ መዝሙር ከመስሪያቤት ኮምፕዩተሩ ላይ ማዳመጥ ክልክል እንደተደረገ ነገረኝ። ለምን ብዬ ስጠይቀው ክርስትያኑም ሙስሊሙም የሚፈልገውን መዝሙር፤ ስብከት፤ ትምሕርት እያዳመጠ እና ኮምፕዩተሩ ላይ ሥዕል እየለጠፈ የሰራተኞች እርስ በርስ ግጭት ሊፈጥር ይችላል ተብሎ ተከለከለ አለኝ። የሚገርመው ነገር ግን 1) ከመስሪያቤቱ እንደዚህ አይነት ግጭቶች አልነበሩም እና 2) ክልከላው በተራ ትዛዝ ሳይሆን ከከፍ ያለ የአስተዳደር ደረጃ በመመርያ ምልክ የተላለፈ ነበር። የመመርያው ርዕስ ደግሞ «ሴኩላሪዝም» ነበር።
ይህን ታሪክ ስሰማ እጅግ አዘንኩኝ። መቼ ነው መንግስቶቻችን፤ ምሁሮቻችን እና ልሂቆቻችን የምዕራብ ዓለም ርዕዮት ዓለምና ፍልስፍና ይዘው አገራችን ላይ መጫን የሚያቆሙት? ካለፉት የ100 ዓመታት ታሪካችን አይማሩምን?
እስቲ «ሴኩላሪዝም» ባጭሩ ምን እንደሆነ እንመልከት። «ሴኩላሪዝም በዓለማችን እግዚአብሔር የለም/አይሳተፍም ብሎ ማሰብ ነው»። ሴኩላሪዝም እግዚህብሔር ሊኖር ላይኖርም ይችላል ግን ከዓለማችን ከሕይወታችን ከለት ኑሮአችንም አይሳተፍም የሚለው አመለካከት ነው። እግዚአብሔር ካለ እዛው ከዙፋኑ ወይንም ገነቱ ተቀምጦ ይመለከተናል። በሃይማኖት እና በእግዚአብሔር በግል ምርጫችን ልናምንባቸው የምንችል የእምነት ሥርዓቶች ናቸው። በሀሳብ ደረጃ ነው የምናምንባቸው ካላሰኘን ደግሞ ከሀሳባችን እናስወግዳቸዋለን!
ይህ አስተሳሰብ በተለያየ መንገድ ወደ ክርስትያን የሆነውን አስተሳሰብ ገብቷል። «ዓለማዊ» እና «መንፋሳዊ» የምንላቸው ቃላት በተሳሳተ መንገድ እንጠቀማለን። ዓለማዊ ስንል ስራችን፤ ትምሕርታችን፤ ገበያችን፤ ንግዳችን ወዘተ ነው። እግዚአብሔር እነዚ ነገሮች ውስጥ እንዳለ አናምንም። ስለዚህም ነው በነዚህ የህይወት ዘርፎቻችን ኢ-ክርስትያናዊ ነገሮች እያደረግን እያለን አማኞች ነን የምንለው። እሁድ እሁድ ግን ቤተ ክርስትያን ሄደን ወደ መንፈሳዊስ ዓለም እንሸጋገራለን። እዛ ጨዋ ነን፤ ጥሩ ስነ መግባር አለን፤ ጭንቀቶቻችንን አስተንፍሰን ወደ ዓለማችን እንመለሳለን።
ይህ ግን የውሸት ክርስትና ነው። በእምነታችን እግዚአብሔር በሁሉም ቦታ በሁሉም ነገር አለ። «እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።» ኤር 23:23-24።
ስለዚህ ትምሕርት ቤት ብሄድ፤ መስሪያ ቦታ ብሄድ፤ እርሻዬ ላይ ብሆን፤ ትራንስፖርት ላይ ብሆን፤ መጠጥ ቤት ብሄድ፤ በሁሉም ቦታ እግዚአብሔር አለ። ሕይወታችንን እግዚአብሔር ያለበትና የሌለበት ብለን ልንከፋፍለው አንችልም። በሁሉም ቦታ በሁሉ ደቂቃ ከኛ ጋር ነውና።
ይህ የሚያሳየን የሰው ልጅ ክርስትያንም ሴኩላሪስትም አብሮ ሊሆን አይችልም። ብዙዎቻችን ወደዚህ ስህተት ብንገባም ሊሆን የማይችል ነገር ነው። ለክርስትያኖች እግዚአብሔር ልኬት የለውምና። በተጨማሪ ሴኩላሪዝም እግዚአብሔርን ከለት ኑሮአችን ማጥፋት ስለሚፈልግ የክርስትና ተቃራኒ ብቻ ሳይሆን ጠላት እንደሆነ ግልጽ ነው።
«እናንተ ኦርቶዶክሶች፤ ሙስሊሞች፤ ፕሮቴስታንቶች አብሮ መኖር አትችሉም። ስለዚህም (እግዚአብሔራን ተክቼ!) ከላያችሁ ሆኜ አስተዳድራችኋለሁ» ይላል ሴኩላሪዝም / ሴኩላሪስቱ። «እኔ ነኝ ስልጡኑ፤ ከማንም ጋር የማልጋጨው፤ ከሁሉም ጋር የምግባባው፤ ሁሉንም የማከብረው» ይላል። እውነቱ ግን ሴኩላሪስቱ እንደዚህ ሲል ሁሉንም በሰላም ለመጠበቅ ሳይሆን አላማው ይህን አስመስሎ «እግዚአብሔር የለም» የሚባለውን ሃይማኖትን ለማስፋፋት ነው። እግዚአብሔር ከአዕምሮአችን ብቻ ነው ያለው እንጂ ከስራ ቦታችን፤ ገበያ ቦታችን፤ መንገዶቻችን፤ ሚዲያዎቻችን፤ ከለት ኑሮአችን የለም ብለን ካመንን ቀጥሎ እግዚአብሔር የትም የለም ማለት የሚቀጥለው ቀላል እርምጃ ነውና!
በተጨማሪ እግዚአብሔር ከለት ኑሮአችን ከሌለ የማህበረሰብ የአገራችን ድንጋጌዎች ከየት ሊመጡ ነው? ከሴኩላሪዝም ርዕዮት ዓለም ከ«እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖት ሊመጡ ነው! አያችሁ ሴኩላሪዝም እራሱን ገለልተኛ አድርጎ እንዴት «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ሰተት ብሎ እንደሚያሰፍን።
ኢትዮጵያ የሃይማኖት አገር ናት። ታሪካችን ትውፊታችን ከዚህ የተያያዘ ነው። ማንነታችን ይህ ነው። ሴኩላሪዝም ደግሞ የህን አፍርሶ «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ነው ማስፈን የሚፈልገው። ይህ ሂደት እንዴት እንደሚሰራ ለማወቅ የምዕራብ ዓለሙን ያለፈውን 400 መቶ ዓመት ታሪክ መመልከት ነው። ስለዚህ ሴኩላሪዝም ኢ-ኢትይጵያዊ እንደሆነ ተረድተን ወደ አገራችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን። በተለይ ደግሞ ወደ ልባችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን።
ይህን ታሪክ ስሰማ እጅግ አዘንኩኝ። መቼ ነው መንግስቶቻችን፤ ምሁሮቻችን እና ልሂቆቻችን የምዕራብ ዓለም ርዕዮት ዓለምና ፍልስፍና ይዘው አገራችን ላይ መጫን የሚያቆሙት? ካለፉት የ100 ዓመታት ታሪካችን አይማሩምን?
እስቲ «ሴኩላሪዝም» ባጭሩ ምን እንደሆነ እንመልከት። «ሴኩላሪዝም በዓለማችን እግዚአብሔር የለም/አይሳተፍም ብሎ ማሰብ ነው»። ሴኩላሪዝም እግዚህብሔር ሊኖር ላይኖርም ይችላል ግን ከዓለማችን ከሕይወታችን ከለት ኑሮአችንም አይሳተፍም የሚለው አመለካከት ነው። እግዚአብሔር ካለ እዛው ከዙፋኑ ወይንም ገነቱ ተቀምጦ ይመለከተናል። በሃይማኖት እና በእግዚአብሔር በግል ምርጫችን ልናምንባቸው የምንችል የእምነት ሥርዓቶች ናቸው። በሀሳብ ደረጃ ነው የምናምንባቸው ካላሰኘን ደግሞ ከሀሳባችን እናስወግዳቸዋለን!
ይህ አስተሳሰብ በተለያየ መንገድ ወደ ክርስትያን የሆነውን አስተሳሰብ ገብቷል። «ዓለማዊ» እና «መንፋሳዊ» የምንላቸው ቃላት በተሳሳተ መንገድ እንጠቀማለን። ዓለማዊ ስንል ስራችን፤ ትምሕርታችን፤ ገበያችን፤ ንግዳችን ወዘተ ነው። እግዚአብሔር እነዚ ነገሮች ውስጥ እንዳለ አናምንም። ስለዚህም ነው በነዚህ የህይወት ዘርፎቻችን ኢ-ክርስትያናዊ ነገሮች እያደረግን እያለን አማኞች ነን የምንለው። እሁድ እሁድ ግን ቤተ ክርስትያን ሄደን ወደ መንፈሳዊስ ዓለም እንሸጋገራለን። እዛ ጨዋ ነን፤ ጥሩ ስነ መግባር አለን፤ ጭንቀቶቻችንን አስተንፍሰን ወደ ዓለማችን እንመለሳለን።
ይህ ግን የውሸት ክርስትና ነው። በእምነታችን እግዚአብሔር በሁሉም ቦታ በሁሉም ነገር አለ። «እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።» ኤር 23:23-24።
ስለዚህ ትምሕርት ቤት ብሄድ፤ መስሪያ ቦታ ብሄድ፤ እርሻዬ ላይ ብሆን፤ ትራንስፖርት ላይ ብሆን፤ መጠጥ ቤት ብሄድ፤ በሁሉም ቦታ እግዚአብሔር አለ። ሕይወታችንን እግዚአብሔር ያለበትና የሌለበት ብለን ልንከፋፍለው አንችልም። በሁሉም ቦታ በሁሉ ደቂቃ ከኛ ጋር ነውና።
ይህ የሚያሳየን የሰው ልጅ ክርስትያንም ሴኩላሪስትም አብሮ ሊሆን አይችልም። ብዙዎቻችን ወደዚህ ስህተት ብንገባም ሊሆን የማይችል ነገር ነው። ለክርስትያኖች እግዚአብሔር ልኬት የለውምና። በተጨማሪ ሴኩላሪዝም እግዚአብሔርን ከለት ኑሮአችን ማጥፋት ስለሚፈልግ የክርስትና ተቃራኒ ብቻ ሳይሆን ጠላት እንደሆነ ግልጽ ነው።
«እናንተ ኦርቶዶክሶች፤ ሙስሊሞች፤ ፕሮቴስታንቶች አብሮ መኖር አትችሉም። ስለዚህም (እግዚአብሔራን ተክቼ!) ከላያችሁ ሆኜ አስተዳድራችኋለሁ» ይላል ሴኩላሪዝም / ሴኩላሪስቱ። «እኔ ነኝ ስልጡኑ፤ ከማንም ጋር የማልጋጨው፤ ከሁሉም ጋር የምግባባው፤ ሁሉንም የማከብረው» ይላል። እውነቱ ግን ሴኩላሪስቱ እንደዚህ ሲል ሁሉንም በሰላም ለመጠበቅ ሳይሆን አላማው ይህን አስመስሎ «እግዚአብሔር የለም» የሚባለውን ሃይማኖትን ለማስፋፋት ነው። እግዚአብሔር ከአዕምሮአችን ብቻ ነው ያለው እንጂ ከስራ ቦታችን፤ ገበያ ቦታችን፤ መንገዶቻችን፤ ሚዲያዎቻችን፤ ከለት ኑሮአችን የለም ብለን ካመንን ቀጥሎ እግዚአብሔር የትም የለም ማለት የሚቀጥለው ቀላል እርምጃ ነውና!
በተጨማሪ እግዚአብሔር ከለት ኑሮአችን ከሌለ የማህበረሰብ የአገራችን ድንጋጌዎች ከየት ሊመጡ ነው? ከሴኩላሪዝም ርዕዮት ዓለም ከ«እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖት ሊመጡ ነው! አያችሁ ሴኩላሪዝም እራሱን ገለልተኛ አድርጎ እንዴት «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ሰተት ብሎ እንደሚያሰፍን።
ኢትዮጵያ የሃይማኖት አገር ናት። ታሪካችን ትውፊታችን ከዚህ የተያያዘ ነው። ማንነታችን ይህ ነው። ሴኩላሪዝም ደግሞ የህን አፍርሶ «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ነው ማስፈን የሚፈልገው። ይህ ሂደት እንዴት እንደሚሰራ ለማወቅ የምዕራብ ዓለሙን ያለፈውን 400 መቶ ዓመት ታሪክ መመልከት ነው። ስለዚህ ሴኩላሪዝም ኢ-ኢትይጵያዊ እንደሆነ ተረድተን ወደ አገራችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን። በተለይ ደግሞ ወደ ልባችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን።
የፖለቲካ ውይይት ስልት፤ «ከጠንካራ ወገኑ ተሟገት»
የኛ የ«ተቃዋሚዎች» የፖለቲካ ችሎታችን፤ ብስለታችን፤ አቅማችን ምን ያህል ደካማ መሆኑን የቅንጅት ታሪክ አጉልቶ ካሳየን 12 ዓመት አልፎታል። አሁንም ደካማ ነን። ብዙኃኑ ንሯል ልሂቃኑ ኋላ ቀርቷል። ምክንያቱ ፖለቲካችንን ለማጠናከር የሚያስፈልጉን ባህሪዎች እንደ መወያየት፤ መተባበር፤ መተማመን፤ መስማማት፤ አብሮ መስራት፤ ቅራኔን መፍታት ወዘተ አሁንም ይጎሉናል። ይህ ጉድለት ነው ለሰላምና ፍትህ ትግላችን ዋና እንቅፋት የሆነው።
ዛሬ በነዚህ ዙርያ አንድ ነጥብ ላይ ማተኮር እወዳለው። ውይይት ሙግት ክርክር የፖለቲካም የማንኛውም የህብረት ስራም መሰረት ነው። የውይይት አንዱ አላማ ሀሳቦችን መፈተንና ማጣራት ነው። የትኛው ትክክል እንደሆነ፤ የትኛው የተሳሳተ እንደሆነ፤ የትኛው ጠቃሚ እንደሆነ፤ የትኛው ተጨማሪ መጠናት እንዳለበት፤ ወዘተ።
ስንወያይ የራሳችን ሀሳብ መናገር ብቻ ከሆነ የምናደርገው እና የሌሎችን ሀሳብ በትክክል የማናዳምጥ ከሆነ ውይይቱ ግቡን እንደማይመታ ግልጽ ነው። እያንዳንዳችን የራሳችን ሀሳብ ብቻ ነው ተቀባይነት የሚገባው ከሆነ ሀሳባችን ሊገመገምና ሊጣራ አይችልም ልንስማማም አንችልም። ሀሳቦቻችን ስላልተገመገሙ ደካማ ይሆናሉ ስላልተስማማን አብረን ደካማ ሆነን እንቀራለን። ስለዚህ ተጠንቅቀን የሌሎችን ሀሳብ ብቻ ሳይሆን አመለካከታቸውንም መረዳት አለብን።
እንደዚህ ለማድረግ የተሟጋቾቻችን ወይም የተቃራኒዎቻችን ሀሳቦች «ጠንካራ ወገንን» መመልከት አለብን። የውይይታችን ዓላማ ማሸነፍ ሳይሆን መገምገምና ማጣራት ስለሆነ። አልፎ ተርፎ የተቃራኒአችን ወይም ተሟጋችን አመለካከትና ሀሳብ ልክ እንደሱ አውቀን መከራከር መቻል አለብን። ከጥንት ዘመን እንደሚባለው ተቃራኒውን ወይም ጠላቱን ያላወቀ ይሸነፋል። ማወቅ ማለት ላይ ላዩን አባባሉን ድርጊቱን ማወቅ ሳይሆን ልከንደሱ ማሰብ ምቻል። ይህን የቻለ ሰው የተቃራኒውን ሀሳብና አቋም ከሱ በተሻለ መንገድ ማሳመን ይችላል! ተቃራኒን በደምብ ማወቅ ማለት ይህ ነው። ከዚህ ብኋላ የተቃራኒውን ሀሳብ በትክክል ሊሟገት ሊያሸንፍ ወይም ሊጠቀምበት ይችላል።
ስለዚህ ጉዳይ ከራሴ አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ። ለረዥም ዓመታት ከ«ጎሰኞች» ጋር ስሟገት የራሴ አቋም እውነት ነው ስነ መግባርና ፍትህ የተሞላ ብቸኛ ሀሳብ ነው ብዬ እነሱን አላዳምጥም ነበር። «ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው» እያልኩኝ ከዚህ ሳላልፍ እንደመድም ነበር። ለኔ የሙግቴ አላማ እነሱን የራሴን ሀሳብ ማሳመን ብቻ ነበር። አልሰራም።
አንድ ወቅት ማዳመጥ ጀመኩኝ። እስቲ በነሱ ቦታ ሆኜ ላስበው አልኩኝ። እንደነሱ ሆኜ ከራሴ ጋር መሟገት ጀመርኩኝ። እንደዚህ ሳረግ የነሱ አስተሳሰብ አመጣጥና ሀሳብ እይገባኝ ሄደ። የነሱን አቋም ይዤ መከራከር ቻልኩኝ። ይህ የራሴን አቋም እንዳጠራው ጠቀመኝ። እነሱም እንደማዳምጣቸው ሲረዱ እኔንም ማዳመጥ ጀመሩ። መተማመን ጀመርን እንደ ጥላት መተያየት አቆምን። ብዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን አሁን ከድሮ ይልቅ በደምብ እረዳለሁ ማለት እችላለሁ። የጎሰኝነትንም አጉል ወገን እንዴት ማስወገድና ማጥፋት እንደሚቻል ይበልጥ የገባኝ ይመስለኛል።
በተዘዋዋሪ ይህን «ማዳመጥ» ወይም ለሰው መቆርቆርና ራስን በሌላው ቦታ ማድረግ የደረስኩበት ከክርስትና ተልእኮአችን ነው። «አትፍረዱ» «ማሩ» «ራሩ» መሰረታዊ የክርስትና ትምሕርቶች ናቸው። አንዱ ታላቅ ቅዱስ ዮሐንስ «ዘመሰላል» እንደዚህ ብለዋል፤
ዛሬ በነዚህ ዙርያ አንድ ነጥብ ላይ ማተኮር እወዳለው። ውይይት ሙግት ክርክር የፖለቲካም የማንኛውም የህብረት ስራም መሰረት ነው። የውይይት አንዱ አላማ ሀሳቦችን መፈተንና ማጣራት ነው። የትኛው ትክክል እንደሆነ፤ የትኛው የተሳሳተ እንደሆነ፤ የትኛው ጠቃሚ እንደሆነ፤ የትኛው ተጨማሪ መጠናት እንዳለበት፤ ወዘተ።
ስንወያይ የራሳችን ሀሳብ መናገር ብቻ ከሆነ የምናደርገው እና የሌሎችን ሀሳብ በትክክል የማናዳምጥ ከሆነ ውይይቱ ግቡን እንደማይመታ ግልጽ ነው። እያንዳንዳችን የራሳችን ሀሳብ ብቻ ነው ተቀባይነት የሚገባው ከሆነ ሀሳባችን ሊገመገምና ሊጣራ አይችልም ልንስማማም አንችልም። ሀሳቦቻችን ስላልተገመገሙ ደካማ ይሆናሉ ስላልተስማማን አብረን ደካማ ሆነን እንቀራለን። ስለዚህ ተጠንቅቀን የሌሎችን ሀሳብ ብቻ ሳይሆን አመለካከታቸውንም መረዳት አለብን።
እንደዚህ ለማድረግ የተሟጋቾቻችን ወይም የተቃራኒዎቻችን ሀሳቦች «ጠንካራ ወገንን» መመልከት አለብን። የውይይታችን ዓላማ ማሸነፍ ሳይሆን መገምገምና ማጣራት ስለሆነ። አልፎ ተርፎ የተቃራኒአችን ወይም ተሟጋችን አመለካከትና ሀሳብ ልክ እንደሱ አውቀን መከራከር መቻል አለብን። ከጥንት ዘመን እንደሚባለው ተቃራኒውን ወይም ጠላቱን ያላወቀ ይሸነፋል። ማወቅ ማለት ላይ ላዩን አባባሉን ድርጊቱን ማወቅ ሳይሆን ልከንደሱ ማሰብ ምቻል። ይህን የቻለ ሰው የተቃራኒውን ሀሳብና አቋም ከሱ በተሻለ መንገድ ማሳመን ይችላል! ተቃራኒን በደምብ ማወቅ ማለት ይህ ነው። ከዚህ ብኋላ የተቃራኒውን ሀሳብ በትክክል ሊሟገት ሊያሸንፍ ወይም ሊጠቀምበት ይችላል።
ስለዚህ ጉዳይ ከራሴ አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ። ለረዥም ዓመታት ከ«ጎሰኞች» ጋር ስሟገት የራሴ አቋም እውነት ነው ስነ መግባርና ፍትህ የተሞላ ብቸኛ ሀሳብ ነው ብዬ እነሱን አላዳምጥም ነበር። «ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው» እያልኩኝ ከዚህ ሳላልፍ እንደመድም ነበር። ለኔ የሙግቴ አላማ እነሱን የራሴን ሀሳብ ማሳመን ብቻ ነበር። አልሰራም።
አንድ ወቅት ማዳመጥ ጀመኩኝ። እስቲ በነሱ ቦታ ሆኜ ላስበው አልኩኝ። እንደነሱ ሆኜ ከራሴ ጋር መሟገት ጀመርኩኝ። እንደዚህ ሳረግ የነሱ አስተሳሰብ አመጣጥና ሀሳብ እይገባኝ ሄደ። የነሱን አቋም ይዤ መከራከር ቻልኩኝ። ይህ የራሴን አቋም እንዳጠራው ጠቀመኝ። እነሱም እንደማዳምጣቸው ሲረዱ እኔንም ማዳመጥ ጀመሩ። መተማመን ጀመርን እንደ ጥላት መተያየት አቆምን። ብዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን አሁን ከድሮ ይልቅ በደምብ እረዳለሁ ማለት እችላለሁ። የጎሰኝነትንም አጉል ወገን እንዴት ማስወገድና ማጥፋት እንደሚቻል ይበልጥ የገባኝ ይመስለኛል።
በተዘዋዋሪ ይህን «ማዳመጥ» ወይም ለሰው መቆርቆርና ራስን በሌላው ቦታ ማድረግ የደረስኩበት ከክርስትና ተልእኮአችን ነው። «አትፍረዱ» «ማሩ» «ራሩ» መሰረታዊ የክርስትና ትምሕርቶች ናቸው። አንዱ ታላቅ ቅዱስ ዮሐንስ «ዘመሰላል» እንደዚህ ብለዋል፤
«አስተዋይ ሰው ወይን ሲበላ የበሰሱትን ይበላል ያልበሰሉትን የሚጎመዝዙትን ይተዋል። እንዲሁም አስተዋይ አዕምሮ በማንድ ሰው የሚያየው (ትንሽም) ጥሩነት ተጠንቅቆ ይመዘግባል። አዕምሮ ቢስ የሆነ ድክመትና መጥፎ ባህሪያትን ይፈልግበታል… ሰው ኃጢአት ሲፈጽም በአይንህም ብታይ አትፍረድ፤ አይኖቻችንም ሊታለሉ ይችላሉና።»ይህን መንገድ የሚከተል የሌሎችን አስተያየትና አመለካከትን አክብሮ በነሱ ቦቶ እራሱን አስቀምጦ ሁኔታውን ይገመግማል። «አትፍረዱ» «ማሩ» «ራሩ» ማለት እራስን በሌላው ቦታ አድርጎ ማሰብ መቻል ነው!
Monday, 19 March 2018
ሊዩ ሺያዎቦ፤ የቻይና ህሊና
ሊዩ ሺያዎቦ (Liu Xiaobo) በቅርብ ከዚህ ዓለም የተለዩ የቻይና ምሁር የሰላምና ፍትህ ተቀናቃኝ የመንግስት ተቃዋሚ ነበሩ። ታሪካቸው ለሁላችንም ኢትዮጵያዊያን እጅግ አስተማሪ ነው። ይህ ጽሑፍ ጠቅለል አድርጎ የሊዩን የፖለቲካ ማንነትን በደምብ የሚገልጽ ይመስለኛል።
ከሊዩ ሺያዎቦ ግንዛቤዎች መካከል አንዱ አትኩረን ማየት ያለብን የሚመስለኝ ስለ ምዕራቡ ዓለምና ምዕራባዊነት የነበራቸው አመለካከት ነው። ሊዩ በመጀመርያ ምዕራባዊነትንና የምዕራብ አገሮችን አጉል ያደንቁ ነበር። የአገራቸውን የፖለቲካ ችግር ከምዕራብ አገሮች «ዴሞክራሲ» «ፍትህ» «ሰላም» እና ጠቅላላ «ስልጣኔ» ሲያነጻጽሩ የምዕራብ አገሮች ገነት የሆኑ ይመስላቸው ነበር።
ግን እንደ ታላቁ ሩሲያዊ አሌክሳንደር ሶልዠኒትሲን ሊዩ አሜሪካን ሲጎበኙ ይህ አመለካከታቸው የተሳሳተ እንደሆነ ተገነዘቡ። የአሜሪካን ችግር ሲያዩ የምዕራብ አገሮች ገነት አለመሆናቸው ብቻ ሳይሆን ግነት በምድር መኖር እንደማይቻልም ተገነዘቡ! ምዕራባዊነትንም እንደ ጣዖት ማየት አቆሙ። አገሬ ቻይና እንደ ምዕራብ አገሮች መሆን አለበት ብለው ማሰብ አቆሙ። የራስችንን ችግር በራሳችን መንገድ ማስተካከል አለበን ብለው አሰቡ።
የምዕራብ ስልጣኔን ፍፁም አድርጌ የማየው የነበረው ምክንያት በአገር ወዳድ ስሜቴ ምዕራቡን ዓለም ለቻይና ተሃድሶ አራአያ ትህናለች ብዬ ነው። ግን ይህ አመለካከቴ የምዕራብ ዓለሙን ግድፈቶችን እንዳላይ አድርጎኛል። የምዕራብ ስልጣኔን አጉል አመልክ ነበር መልካምነቱን አጋንኜ ነበር። የራሴን አስተሳሰብን ትክክልነትም አጋንኜ ነበር። ምዕራብ ዓለሙ ቻይናን የሚያድን ብቻ ሳይሆን የዓለም በሙሉ የሰው ልጅ የመጨረሻ ግብ ይመስለኝ ነበር። የዓለም አገሮች በሙሉ እያደጉ ሲሄዱ እንደ ምዕራብ አገሮች እየመሰሉ ይሄዳሉ ብዬ አስብ ነበር። በተጨማሪ ይህን ቅዠታማ አስተያየቴን ይዤ አገሬን አድናለው ቢየ አስብ ነበር።
አሁን ግን የገባኝ ይህ ነው፤ የምዕራብ ስልጣኔ ቻይና አሁን ባለችበት ሁኔታ ለማደስ ጥሩ ምሳሌዎች ይኖሩታል ግን ዓለምን የሰው ልጅን ሊያድን አይችልም።
የምዕራብ ስልጣኔን ራቅ ብለን ሰከን ብለን ከተመለከትነው የሰው ልጅ ቀጥንት እስካሁን ያሉትን ችግሮች አሉት።
ለ30 ዓመት በላይ በቻይና አምባገነናዊ ሥርዓት የኖርኩኝ ሆኜ ስለ የሰው ልጅ ማንነትና ዕጣ ማሰብ ከፈለግኩኝና እውነተኛ መሆን ከፈለግኩኝ ሁለት ትንተኖች ማድረግ ይኖርብኛል፤
1. የምዕራብ ስልጣኔን ቻይናን ለመተንተን መጠቀም አለብኝሊዩ ሺያዎቦ ከጻፉት መጸሐፎች የታወቀው «ጠላት የለኝም ጥላቻም የለኝም» ነው። ሊዩ ለቻይና መሪዎች የኮምዩኒስት ፓርቲ አባሎች እና ሌሎች ገዞች ጥላቻውን አስወገደ። የሃገሩ ሥርዓት ምክንያት እነሱ ብቻ ሳይሆኑ እያንዳንዱ ቻይናዊ ሃላፊነት እንዳለበት ተገንዝበው ሁላችንም መቀየር አለብን ንለው ያምኑ ነበር። ስሜትን የሚያስተስት ለፖለቲካ ምቹ ሃሳብ ባይሆንም ትክክለኛው እውነት የሆነ ሃሳብ ነው።
2. የራሴን የፈጠራ ሃሳቦችን የምዕራብ ዓለምን ለመተቸት መጠቀም አለብኝ
ለዚህ መሰለኝ ሌሎች ይበልጥ የሚጮሁ (የሚለፈልፉ) መንግስትን የሚተቹ የመንግስት ተቃዋሚዎች ሳይታሰሩ ሊዩ ሺያዎቦ እስኪሞቱ የታሰሩት። ሊዩ ሺያዎቦ እውነቱን ደረሱበት። መንስግትን ብቻ ሳይሆን ላለው ሥርዓት ህዝቡንም ሃላፊነት አለው አሉ። ህዝቡ ቢያዳምጣቸው ደግሞ የእውነት ለውጥ እንደሚመጣ መንግስት ያውቃል።
ሊዩ ሺያዎቦ የምዕራብ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለውጥ ለማምጣት አያስፈልጉንም አሉ። የራሳችን ማንነት ስነ መግባር ፍትህ ህሊና ይበቃናል። ሊዩ በየ ምዕራብ መገናኛ ብዙኃን እየዞረ ቃለ ምልልስ አይሰጥም ነበር። ሌሎች ይህን የሚያደርጉ ሳይታሰሩ ታሰረ። የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ምን እውነት እንደሆነና ምን አይነት አስተሳሰብ ከስልጣን እንደሚያወርዱ በደምብ ያውቃል። ስለዚህ ሰላማዊው ሊዩ ሺያዎቦ ታሰረና ሞተ። ታላቅ ምሳሌ ናቸው።
Subscribe to:
Posts (Atom)