በ«ተቃዋሚዎች» መካከል ስለ አማራ ማንነት አይነቱ ክርር ያለ ጭቅጭቅ ሲነሳ «መጀመሪያ የሁላችንም ጠላት የሆነውን ህወሓትን ከስልጣን መፈንቀል ላይ ተባብረን እናተኩር ፤ ከዛ በኋላ ስለ ሌሎች ጉዳዮች መነጋገር ይቻላል» ይባላል። ለ27 ዓመት በተደጋጋሚ የሰማነው አሁንም የምንሰማው አባባል ነው።
አዎ ግባችን ህወሓትን ከስልጣን ማውረድ ከሆነ ከማንም ጋር ተባብረን ሌሎች ጉዳዮችንን በሙሉ ዘርግፈን ግባችን ላይ ማተኮር ነው ያለብን። ነገር ግን ይህን ማድረግ አልተቻለም። ለ27 ረዥም ዓመታት አልተቻለም! ተስማምተን ለአላማችን ብለን ተማምነንና ተባብረን አንድ ሆነን መስራት አልቻልንም።
ለምን? ለምን ግባችንን ለመምታት ግድ የሆነውን አንድነት መመስረት አልቻልንም? ያልቻልንበት ምክንያት እኛ «ተቃዋሚዎች» በርካታ የማንስማማባቸው የአገራችን የፖለቲካ ጉዳዮች ስላሉ ነው። በነዚህ ጉዳዮች ስለማንስማማ ተማምነን አብረን መስራት አልቻልንም።
ስለዚህ ይህን ችግር ለመፍታት ቁጭ ብለን መወያየት፣ ጉዳዮቹን ማብሰልሰል፣ መከራከር፤ መስማማት አለብን። ይህን የውይይት ስራችንን እስካሁን በጭራሽ አልሰራንም ማለት ይቻላል። እስካሁን ጊዜአችንን አቅማችንን 95% በኢህአዴግ ማልቀስ 5% በራሳችንን ማጎልበት ነው ያዋልነው! አንድ ላይ መስራት የምንችለው በኢትዮጵያ ያለንን ራዕይ ዙርያ በቂ ውይይታዊ ስራ ካደረግን በኋላ ነው።
ስለዚህ ቀደም ተከተሉ እንደዚህ መሆን አለበት፤ 1ኛ) እርስ በርስ ያለንን ጉዳዮች ተወያይተን ጨምቀን ወደ የምንተመመንበት የምንስማማበት መድረስ። ይህ ስራ ዓመታት ሊፈጅ ይችላል። 2ኛ) ከዚያ በኋላ የመሰረትነውን መተማመን፣ ስምምነትና አንድነት ተጠቅመን ህወሓትን መፎካከር።
ለማጠቃለል ትኩረታችን ህውሓትን ከስልጣን ማውረድ ከሆነ በመጀመሪያ በመካከላችን አንድነት መፍጠር አለብን። አንድነት ለመፍጠር እርስ በርስ በሁሉም መልኩ እንዳንተማመን፤ እንዳንስማማ እና አንድነት እንዳንፈጥር የሚያደርጉንን ጉዳዮች በደንብ መወያየት አለብን። ከዚያም የገነባነውን አንድነት በመጠቀም ህወሓትን ለማሸነፍ እንችላለን።
ስለዚህ ስለ አማራ ማንነት፤ የጎሳ አስተዳደር፤ የትግል ስልት፤ እና ሌሎች በርካታ የማያስማሙን ወይም ማሻሻል የሚኖሩብን ጉዳዮችን መወያየት ህወሓትን ለማሸነፍ የግድ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ቅድመ ሁኔታ ነው።
እዚህ ላይ ለመጨመር ያህል በኔ እይታ ህወሓትን ከስልጣን ማስወገድ አንደኛ ላማችን ሊሆን አይገባም። አላማችን ሰላም፤ ፍትሕ፤ ፍቅር፤ መልካም አስተዳደር ማምጣት ነው። ሀውሓትንም ማስወገድ የምንፈልገው የነዚህ ተቃራኒ ስለሆነ ነው። ግን ህወሓትን ከስልጣን አባረን የሱን ቢጤ የሆነ መንግስት አንፈልግም። ከላይ የዘረዘርኩት አካሄድ ግን እንደዚህ እንዳይሆን የሚከላከል ነው! ስለ አገራችን ያለንን ራዕይ ላይ ቀድሞ በደምብ ተወያይተን ከተስማማን ከተማመንን አምባገነን ከመካከላችን አምባገነን ሊፈጠር አይችልም አምባገነን የአለመግባባት የአለመስማማት ውጤት ስለሆነ። ስለዚህ ካሁን ወድያ ይህ ዋና ስራችን ላይ እናቶኩር።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ውይይት. Show all posts
Showing posts with label ውይይት. Show all posts
Monday, 26 March 2018
Sunday, 25 March 2018
ስለ «አማራ» ያከው ውይይት
ስለ አማራ ማንነት ይሆን ወይም በሌላም አርእስት ስነወያይ ነገሮችን በጥራት እንድናይ ለመወያየት ለመከራከር ለመተቻቸት ብቻ ሳይሆን ግብ ለመምታት ከሆነ ከውይይታችን ከአስተሳሰባችን በስተ ጀርባ ዙርያውን ያለውን ሁኔታ አስተሳሰባችን መመልከት አለብን። ይህን ለማድረግ ዘንድ እስቲ እነዚህን ነጥቦች በደምብ እንመልከታቸው።
1. ሁሉም ውይይት "context" (ዐውደ ሁኔታ?) አለው። ዛሬ ያለው ሁኔታ ምንድነው? 60 ዓመት በፉት ይህ ውይይት ይኖር ነበር ቢኖርስ ምን ይመስል ነበር። 2. ለውይይቱ ምን አይነት አመለካከት ርዕዮት ዓለም እምነት ወዘተ ይዘን ነው የምንከራከረው? በጎሰኝነት ("identity") ፒለቱካ እናምናለን? ወይም የአገር ብሄርተኖች ("nationalist") ነን? 3. የምንጠቀምበት ቋንቋ ቃላቶች ምን ትርጉም አላቸው? «ጎሳ» ምንድንደው? «ህዝብ» ምንድነው? «አማራ» ምንድነው? «ማንንነት» ምንድነው?
4. የውይይታችን አላማ ምንድነው? ውይይቱን ማሸነፍ ነው? መስማማት ነው? እውነት ላይ መድረስ ነው?
5. የጠቅላላ አላማችን ምንድነው? ከአገራችን ሽኩቻ አድሎ ኢፍትሃዊነት እንዲጠፋ ሰላምና ፍትህ እንዲኖር ነው? ህወሓትን ከስልጣን ማውረድ ነው? ስልጣን መያዝ ነው? ጥሩ የሚመስለንን ሥርዓትን ማስፈን ነው?
6. ውይይታችን አቋማችን ከህዝቡ ዝንባሌ ጋር በተወሰነ ድረጃ ብቻ ቢሆንም ይሄዳል ወይ? ይህ ታላቅ ጥያቄ ነው። የ«ፌስቡክ» ብቻ ውይይት ነው? የልሂቃን ብቻ ውይይት ነው? የአዲስ አበባ ብቻ ውይይት ነው? የተማሪዎች? ወይም ከብዙኃኑ ምካከል ይህ ጉዳይ እንደ ቁም ነገር ይቆጠር ይሆን?
ሁላችንም እራሳችንን እነዚህን ጥያቄዎች ጠይቀን በአግባቡ መልሰን ነው ፍሬአማ ውይይት ሊኖርን ይሚችለው።
እስቲ የኔን መልሶች ልስጣችሁ፤
1. ዛሬ የምዕራባዊ የማርክሲዝም የጎሳ ወይም ብሄሮች አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ በደምብ ሰክኗል። በ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ተማሪዎቻችን ወደ ውጭ አገር ትምሕርትቤት ሄድው ያመጡት ርዕዮት ዓለም አገር ውስጥ መሰረት ጥሎ ጭርሽ ህገ መንግስታችንን በክሎታል የፖለቲካ መዋቀራችንን በይኗል። በመሀበረሰብ ደረጀ በፊት ከ«ልሂቃን» ያልወጣ አስተሳሰብ አሁን አማራ ኦሮሞ ሲዳማ ትግሬ ብዙኃኑም ያውቀዋል። ግን በትክክሉ ምንድነው የሚያውቀው? ቋንቋ ነው? «ዘር» ነው? «ቦታ» ነው? ማንነት ነው? የፖለቲካ ክፍል ነው? ብዚህ ዙርያ የተለያዩ አመለካከቶች ቢኖሩም አብዛኞቻችን «አማራ» የሚለውን ቃል ድሮ የማንጠቀምበት ዛሬ እንጠቀምበታለን። ድሮ የፖለቲካ ትርጉም ያልነበረው ዛሬ አለው። ዛሬ ሰዎች በአማርነት ይከሰሱበታል። ይወነጀሉበታል። አንዳንዱ አማራ በመሆኔ ተጎጂ ነኝ ብሎ ያስባል። እጨቆናለሁ መብት የለኝም የሚል አለ። ባጭሩ ይህ ሁኔታ ላይ ነው ዛሬ የምንገኘው።
2. ማንነት የሰው ተፈጥሮ ባህሪ ነው ብዬ አምናለው። በመንደር ካልሆነ በጠቅላይ ግዛት ካልሆነ በጎሳ ካልሆነ በአገር ሁላችንም አንዱ የማንነታችንን ክፍል ይህ ነው። እስቲ አንድ ምሳሌ እናስብ። አንድ ኢትዮጵያዊ አሜሪካ ለ20 ዓመት ኖሮ ዜግነት ተቀብሎ አሜሪካው ነኝ ይላል። ኢትዮጵያዊ ነኝም ይላል። ለምን ኢትዮጵያዊነቱን አይተወውም። ልም ልጆቹን የኢትዮጵያ ቋንቋ ያስተምራል ቢችልም የኢትዮጵያ ትምሕርትቤት ይልካል? ለመሆኑ አሜሪካና ኢትዮጵያ በሆነ ጉዳይ ቢቃረኑ ማንን ይሆን የሚደግፈው? ኢትዮጵያን ቢደፍግ ሌላው አሜሪካዊ ከሃዲ አይለውም ይሆን? ለሌላው አሜሪካዊ «ኢትዮጵያዊ-አመሪካዊ» ማለት ጎሳ ነው። አያችሁ የጎሳ ስሜት እንዴት የተፈጥሮ እንደሆነ። የተፈጥሮ ቢሆንም ብዙ ጎሳዎች ያሉበት አገር ውስት የጎሰኝነት ስሜት ከአገር ብሄርተኝነት ስሜት ከበለጠ የጎሳ ፉክክር ("ethnic competition") በፖለቲካ ምድር ውስጥ ያበዛና ለአገሪቷ ህልውና ለሰላም ለፍትህ አደገኛ ነው ይሚሆነው። ይህን ነው ዛሬ በኢትዮጵያ የምናየው። ይህ ምክነያት የአገር ብሄርተኛ ነኝ። ማለት ለሁላችን ሰላምና ለአገሪቷ ብልጽግና የጎሰኘት ስሜት ከአገር ስሜት በታች መሆን አለበት ብዬ ነው የማምነው። «ኢትዮጵያዊ ነኝ ቀጥሎ ኦሮሞ» ትሩ ነው። «ትግሬ ነኝ ቀጥሎ ኢትዮጵያዊ» ወደ ችግር ይመራል።
3. «ጎሳ» «ህዝብ» «ማንንነት» «አማራ» ለሁላችንም የተለያዩ ትርጉሞች አላቸው። ከላይ እንዳልኩት ለኔ የሰው ልጅ ማንነት ውስጥ አንድ የአገር ወይ ጎሳ ወይ መንደር ወዘተ ክፍል አለ። ስለዚህ ለኔ ይህ የማንነት ክፍል በ«ኢትዮጵያዊነት» ወይም «ኦሮሞነት» ወይም «ኦሮሞ-ኢትዮጵያዊነት» ወይም «ኢትዮጵያ-አማራነት» ወይም «ጎጃምነት» ወይም «አፍሪካነት» ሊሞላ ይችላል። ግን ሰውው «ጎሳ» እና «ህዝብ» እና «አገር» ሲለይ የፖለቲካ አቋምን ነው የሚገልጸው። ለምሳሌ አውሮፓ ከትናንሽ የንጉስ ግዛቶች «ጎሳዎች» ወደ አገሮች ("nation state") ሲቀየር «ጎሳ» የኋላ ቀር ነው ብለው ሰየሙ። ግን በጎስኝነት ዘመን የሚያራምዱት ጥላቻን ጦርነትን አሁን በ«አገር» ደረጃ በከፍ ያለ አቀም አራመዱት! ወደ «አማራ» የምንለው ቃል እንምጣ። የቃላቱ ትርጉም በመቶዎች ዓመታት እነደተቀየሩ ግልጽ ነው። የታሪቅ መጽሐፍቶች የድሮ አጠቃቀም ካሁኑ እንደሚለው ያሳያሉ። በቅርብ ዓመታት እራሱ ለምሳሌ ከሃረር እስከ ሸዋ መካከል «ነባር» ሙስሊም ኦሮሞዎች በቀር ሌላው «ክርስትያን» ነበር የሚባለው። ግን ነገሮች ይቀየራሉ። አሁን ከላይ እንደጠቀስኩት የማርክሲዝም ፖለቲካ ሰፍኖ ሁላችንም አማራ እንላለን ወይም ታግለን እራሳችንን እንቆጥባለን።
4. ስወያይ በተቻለ ቁጥር እውነት ላይ ለመድረስ ነው የምወያየው። አዎን አንድ አንድ ጊዜ ፍተናው ያሸንፈኛልና ትቢት ተሞልቼ ማሸነፍ ፈልጋለው አቋሜ ትክክል ቢሆንም ባይሆንም። ውይም ፈርቼ ወይም ለይሉኝታ መስማማት እፈልጋለሁ ስምምነት በውሸት የተመሰረተ ቢሆንም። ግን ደካማ ወገኔን ትቻ አላማየ እውነት ነው። ባልወደውም። ለምን እውነንት? እውነት ነው ለሁሉም የሚበጀው። አላማ እውነት ነው ማለት ለታክቲክ ወይም ለጊዜያዊ ሰላም ቁስል እስኪድን ወዘተ ተብሎው ዝም አይባልም ወይም አይዋሽም ማለት አይደለም። ገን የመጨረሻ ግቡ እውነት ነው።
5. እኔ ሰላምና ፍትህ ነው የምወደው። (አድሎ ሙስና አይኖር ማለት ፍትህ ይኑር ነው።) ሰው እንዳይጎዳ። ሰው ሌላውን ጉዳ እንዳይባል መጉዳት ከመጎዳት ይበልጥ ጎጂ ነውና። ከዛ ውጭ ማን ይግዛ ምን ሥርዓት ይኖር ግድ የለኝም። እንደ ኦርቶዶክስ ክርስትያንነቴ ወደ ንጉሳዊ አገዛዝ አደላለው ከሰው ወይም ሰዎች ይልቅ እግዚአብሔር መሪ ቢሾም ይሻላል ስለሚመስለኝ። ግን ይህ ሀሳብ ለ«ዘመናዊ» ሰው አይገባውም እንተወው። ለማንኛውም ሰላም ፍቅር ፍትህን የሚያበዛ ትልና ሽኩጫን የሚያሳንስ ሥርዓት ከተባለ ከሞላ ጎደል ምን መምሰል እንዳለበት እናውቃለን።
6. እውነቱን ለመናገር ይህ ሀአማራ ማንነት ጉዳይ ከዲያስፖራና ፌስቡክ ውች ያን ያህል ትኩረት ያለው አይመስለኝም። በኔ እይታ (በኢህአዴግም ይመስለኛል!) ያለፉት ሶስት አራት ዓመት የህዝብ ተቃውሞ በመጀመርያ ደረጃ አድሎን በተለይ የ«ትግሬ አድሎን» ተመስርቶ ነው። ይህ በአማራ ክልል የተካሄደውን ተቃውሞንም ያካትታል። መፈከሩ ትግሬ አይግዛን ነው እንጂ አማራ ይከበር አይመስለኝም። በግሌ ያየሁት የሰማሁት እንደዚህ ነው። እንደሚመስለኝ ዛሬ አማራ የምንለው ህዝብ አሁንም በጣም ወደ ኢትዮጵያዊነት ያመዝናል ከአማራነት ይልቅ። ነገ አማራ ክልል በንዚን ቢገኝ ለአማራ ክልል ብቻ ይውል የሚል ጥቂት መሰለኝ። ትግሬ ምንም አያገኝ የሚሉ ብዙ ይኖራሉ ያሳዝናል እንጂ። ጥቃት ያመታው ችግር ነው። ግን አብዛኛው አማራ በለጸገች ከማለት ኢትዮጵያ በለጸገች ነው የሚለው።
እሺ በመጨረሻ ለ«ትግሉ» ተብሎ በአማራነት መታገሉ አይሻልም ወይ የሚለው ከመምህር ሐዚም አስራት ወልደየስ ዘመን ጀምሮ ያለ ጥያቄ አለ። ያኔ አልሰራም ከላይ እንደጠቀስኩት «አማራ» የሚባለው ስሜቱ ከአማራነት ይልቅ ኢትዮጵያዊነት እጅግ ስለሚበልት። አናሳ ብሄርም ስላልሆነ። የተጭቋኝ ስሜትም ስላልነበረው። ዛሬ ሁኔታው ጠቀይሯል በተወሰነ ደረጃ ግን አሁን ስኬታማ የ«አማራ የጎሳ» ትግል ለማካሄድ የህዝቡ ሁኔታ የሚፈቅድ አይመስለኝም።
እውነት ነው እንደዚህ አይነቱ ትግል ያስጎመዣል። እነ ሻዕብያ ህወሓት ኦነግ እንዳረጉት ስኬታማ ትግል ማድረግ ነው። የጎሳን የተፈጥሮ የማሰባሰብ ኃይል መጠቀም ነው። ግን ሁኔታው ካልፈቀደ ህዝቡ ማንነቱ ከዚ አይነት አስተሳሰብ ጋር የማይሄድ ከሆነ አሁንም አይሳካም። ሰከን ብሎ ማሰብ ነው።
በመጨረሻ ላስታውሳችሁ የምወደው ምሳሌዎቹ ወይም "template" የሆኑት እነ ሻዕብያ ህወሓት እጅግ አናሳ ስለሆኑ ለማሸነፍ ጎሰኝነትን ግድ መጠቀም አለብን ብለው ያምኑ ነበር። ግን እስካማውቀው ኢ-ህወሓት የሆንነው ወይም «ተቃዋሚ» የሆንነው የአገሪቷ 90% ወይም 80% ወይም 70% ነን። የጎሰኝነት የፖለቲካ ኃይል መሰብሰብያ "ethnic leverage" አስፈላጊ ነው ልንል አይገባም። ትንሽ የፖልቲካ ብስለት ትብብር አብሮ መስራት መተማመን ጉዳዩን ትላንት ይጨርሰው ነበር።
Wednesday, 21 March 2018
የፖለቲካ ውይይት ስልት፤ «ከጠንካራ ወገኑ ተሟገት»
የኛ የ«ተቃዋሚዎች» የፖለቲካ ችሎታችን፤ ብስለታችን፤ አቅማችን ምን ያህል ደካማ መሆኑን የቅንጅት ታሪክ አጉልቶ ካሳየን 12 ዓመት አልፎታል። አሁንም ደካማ ነን። ብዙኃኑ ንሯል ልሂቃኑ ኋላ ቀርቷል። ምክንያቱ ፖለቲካችንን ለማጠናከር የሚያስፈልጉን ባህሪዎች እንደ መወያየት፤ መተባበር፤ መተማመን፤ መስማማት፤ አብሮ መስራት፤ ቅራኔን መፍታት ወዘተ አሁንም ይጎሉናል። ይህ ጉድለት ነው ለሰላምና ፍትህ ትግላችን ዋና እንቅፋት የሆነው።
ዛሬ በነዚህ ዙርያ አንድ ነጥብ ላይ ማተኮር እወዳለው። ውይይት ሙግት ክርክር የፖለቲካም የማንኛውም የህብረት ስራም መሰረት ነው። የውይይት አንዱ አላማ ሀሳቦችን መፈተንና ማጣራት ነው። የትኛው ትክክል እንደሆነ፤ የትኛው የተሳሳተ እንደሆነ፤ የትኛው ጠቃሚ እንደሆነ፤ የትኛው ተጨማሪ መጠናት እንዳለበት፤ ወዘተ።
ስንወያይ የራሳችን ሀሳብ መናገር ብቻ ከሆነ የምናደርገው እና የሌሎችን ሀሳብ በትክክል የማናዳምጥ ከሆነ ውይይቱ ግቡን እንደማይመታ ግልጽ ነው። እያንዳንዳችን የራሳችን ሀሳብ ብቻ ነው ተቀባይነት የሚገባው ከሆነ ሀሳባችን ሊገመገምና ሊጣራ አይችልም ልንስማማም አንችልም። ሀሳቦቻችን ስላልተገመገሙ ደካማ ይሆናሉ ስላልተስማማን አብረን ደካማ ሆነን እንቀራለን። ስለዚህ ተጠንቅቀን የሌሎችን ሀሳብ ብቻ ሳይሆን አመለካከታቸውንም መረዳት አለብን።
እንደዚህ ለማድረግ የተሟጋቾቻችን ወይም የተቃራኒዎቻችን ሀሳቦች «ጠንካራ ወገንን» መመልከት አለብን። የውይይታችን ዓላማ ማሸነፍ ሳይሆን መገምገምና ማጣራት ስለሆነ። አልፎ ተርፎ የተቃራኒአችን ወይም ተሟጋችን አመለካከትና ሀሳብ ልክ እንደሱ አውቀን መከራከር መቻል አለብን። ከጥንት ዘመን እንደሚባለው ተቃራኒውን ወይም ጠላቱን ያላወቀ ይሸነፋል። ማወቅ ማለት ላይ ላዩን አባባሉን ድርጊቱን ማወቅ ሳይሆን ልከንደሱ ማሰብ ምቻል። ይህን የቻለ ሰው የተቃራኒውን ሀሳብና አቋም ከሱ በተሻለ መንገድ ማሳመን ይችላል! ተቃራኒን በደምብ ማወቅ ማለት ይህ ነው። ከዚህ ብኋላ የተቃራኒውን ሀሳብ በትክክል ሊሟገት ሊያሸንፍ ወይም ሊጠቀምበት ይችላል።
ስለዚህ ጉዳይ ከራሴ አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ። ለረዥም ዓመታት ከ«ጎሰኞች» ጋር ስሟገት የራሴ አቋም እውነት ነው ስነ መግባርና ፍትህ የተሞላ ብቸኛ ሀሳብ ነው ብዬ እነሱን አላዳምጥም ነበር። «ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው» እያልኩኝ ከዚህ ሳላልፍ እንደመድም ነበር። ለኔ የሙግቴ አላማ እነሱን የራሴን ሀሳብ ማሳመን ብቻ ነበር። አልሰራም።
አንድ ወቅት ማዳመጥ ጀመኩኝ። እስቲ በነሱ ቦታ ሆኜ ላስበው አልኩኝ። እንደነሱ ሆኜ ከራሴ ጋር መሟገት ጀመርኩኝ። እንደዚህ ሳረግ የነሱ አስተሳሰብ አመጣጥና ሀሳብ እይገባኝ ሄደ። የነሱን አቋም ይዤ መከራከር ቻልኩኝ። ይህ የራሴን አቋም እንዳጠራው ጠቀመኝ። እነሱም እንደማዳምጣቸው ሲረዱ እኔንም ማዳመጥ ጀመሩ። መተማመን ጀመርን እንደ ጥላት መተያየት አቆምን። ብዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን አሁን ከድሮ ይልቅ በደምብ እረዳለሁ ማለት እችላለሁ። የጎሰኝነትንም አጉል ወገን እንዴት ማስወገድና ማጥፋት እንደሚቻል ይበልጥ የገባኝ ይመስለኛል።
በተዘዋዋሪ ይህን «ማዳመጥ» ወይም ለሰው መቆርቆርና ራስን በሌላው ቦታ ማድረግ የደረስኩበት ከክርስትና ተልእኮአችን ነው። «አትፍረዱ» «ማሩ» «ራሩ» መሰረታዊ የክርስትና ትምሕርቶች ናቸው። አንዱ ታላቅ ቅዱስ ዮሐንስ «ዘመሰላል» እንደዚህ ብለዋል፤
ዛሬ በነዚህ ዙርያ አንድ ነጥብ ላይ ማተኮር እወዳለው። ውይይት ሙግት ክርክር የፖለቲካም የማንኛውም የህብረት ስራም መሰረት ነው። የውይይት አንዱ አላማ ሀሳቦችን መፈተንና ማጣራት ነው። የትኛው ትክክል እንደሆነ፤ የትኛው የተሳሳተ እንደሆነ፤ የትኛው ጠቃሚ እንደሆነ፤ የትኛው ተጨማሪ መጠናት እንዳለበት፤ ወዘተ።
ስንወያይ የራሳችን ሀሳብ መናገር ብቻ ከሆነ የምናደርገው እና የሌሎችን ሀሳብ በትክክል የማናዳምጥ ከሆነ ውይይቱ ግቡን እንደማይመታ ግልጽ ነው። እያንዳንዳችን የራሳችን ሀሳብ ብቻ ነው ተቀባይነት የሚገባው ከሆነ ሀሳባችን ሊገመገምና ሊጣራ አይችልም ልንስማማም አንችልም። ሀሳቦቻችን ስላልተገመገሙ ደካማ ይሆናሉ ስላልተስማማን አብረን ደካማ ሆነን እንቀራለን። ስለዚህ ተጠንቅቀን የሌሎችን ሀሳብ ብቻ ሳይሆን አመለካከታቸውንም መረዳት አለብን።
እንደዚህ ለማድረግ የተሟጋቾቻችን ወይም የተቃራኒዎቻችን ሀሳቦች «ጠንካራ ወገንን» መመልከት አለብን። የውይይታችን ዓላማ ማሸነፍ ሳይሆን መገምገምና ማጣራት ስለሆነ። አልፎ ተርፎ የተቃራኒአችን ወይም ተሟጋችን አመለካከትና ሀሳብ ልክ እንደሱ አውቀን መከራከር መቻል አለብን። ከጥንት ዘመን እንደሚባለው ተቃራኒውን ወይም ጠላቱን ያላወቀ ይሸነፋል። ማወቅ ማለት ላይ ላዩን አባባሉን ድርጊቱን ማወቅ ሳይሆን ልከንደሱ ማሰብ ምቻል። ይህን የቻለ ሰው የተቃራኒውን ሀሳብና አቋም ከሱ በተሻለ መንገድ ማሳመን ይችላል! ተቃራኒን በደምብ ማወቅ ማለት ይህ ነው። ከዚህ ብኋላ የተቃራኒውን ሀሳብ በትክክል ሊሟገት ሊያሸንፍ ወይም ሊጠቀምበት ይችላል።
ስለዚህ ጉዳይ ከራሴ አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ። ለረዥም ዓመታት ከ«ጎሰኞች» ጋር ስሟገት የራሴ አቋም እውነት ነው ስነ መግባርና ፍትህ የተሞላ ብቸኛ ሀሳብ ነው ብዬ እነሱን አላዳምጥም ነበር። «ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው» እያልኩኝ ከዚህ ሳላልፍ እንደመድም ነበር። ለኔ የሙግቴ አላማ እነሱን የራሴን ሀሳብ ማሳመን ብቻ ነበር። አልሰራም።
አንድ ወቅት ማዳመጥ ጀመኩኝ። እስቲ በነሱ ቦታ ሆኜ ላስበው አልኩኝ። እንደነሱ ሆኜ ከራሴ ጋር መሟገት ጀመርኩኝ። እንደዚህ ሳረግ የነሱ አስተሳሰብ አመጣጥና ሀሳብ እይገባኝ ሄደ። የነሱን አቋም ይዤ መከራከር ቻልኩኝ። ይህ የራሴን አቋም እንዳጠራው ጠቀመኝ። እነሱም እንደማዳምጣቸው ሲረዱ እኔንም ማዳመጥ ጀመሩ። መተማመን ጀመርን እንደ ጥላት መተያየት አቆምን። ብዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን አሁን ከድሮ ይልቅ በደምብ እረዳለሁ ማለት እችላለሁ። የጎሰኝነትንም አጉል ወገን እንዴት ማስወገድና ማጥፋት እንደሚቻል ይበልጥ የገባኝ ይመስለኛል።
በተዘዋዋሪ ይህን «ማዳመጥ» ወይም ለሰው መቆርቆርና ራስን በሌላው ቦታ ማድረግ የደረስኩበት ከክርስትና ተልእኮአችን ነው። «አትፍረዱ» «ማሩ» «ራሩ» መሰረታዊ የክርስትና ትምሕርቶች ናቸው። አንዱ ታላቅ ቅዱስ ዮሐንስ «ዘመሰላል» እንደዚህ ብለዋል፤
«አስተዋይ ሰው ወይን ሲበላ የበሰሱትን ይበላል ያልበሰሉትን የሚጎመዝዙትን ይተዋል። እንዲሁም አስተዋይ አዕምሮ በማንድ ሰው የሚያየው (ትንሽም) ጥሩነት ተጠንቅቆ ይመዘግባል። አዕምሮ ቢስ የሆነ ድክመትና መጥፎ ባህሪያትን ይፈልግበታል… ሰው ኃጢአት ሲፈጽም በአይንህም ብታይ አትፍረድ፤ አይኖቻችንም ሊታለሉ ይችላሉና።»ይህን መንገድ የሚከተል የሌሎችን አስተያየትና አመለካከትን አክብሮ በነሱ ቦቶ እራሱን አስቀምጦ ሁኔታውን ይገመግማል። «አትፍረዱ» «ማሩ» «ራሩ» ማለት እራስን በሌላው ቦታ አድርጎ ማሰብ መቻል ነው!
Friday, 2 March 2018
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ
ይህንን የምጽፈው ሊህቃኖቻችንም እኛ ብዙሃንም አሁን ባለው የፖለቲካ ሁኔታ ትክክለኛ የሚመስለኝን ግንዛቤ እንዲኖረን ነው። በዛ ግንዛቤ ተመስርቶ ትክክለኛውን ሃሳብና ስራ በተግባር እንዲያውል ነው።
ዛሬ የፀደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በርካቶች ከሚያስቡት ተቃራኒ አስተዋሶ ነው የሚኖረው። የነጻነትን እንቅስቃሴውን ይጠቅማል እንጂ አይጎዶም።
ለማስታወስ ያህል ባለፉት ዓመታት ያየነው የህዝብ ተቃውሞና የኢህአዴግ የስልጣን መገለባበጥ በአንድ ጊዜ የምነጣ አይደለም። ለረዥም ዓመታት እየተንከባለለ የመጣ አዝማሚያ ነው። የህዝብ ብሶትና የአስተዳደሩ መሰረታዊ ችግር ያመታው ተቃውሞ ነው። የጎሳ አስተዳደርና የአውራ ፓርቲ የልማታዊ መንግስት አስተዳደር እንደ እሳትና ጭድ የሆኑ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለሞች በመሆናቸው ኤኮኖሚው ምንም ቢያድግም የህዝብ ቁታ እንዲንር አድርጓል። ይህ አገዛዝ ያመጣው በህዝቡ መካከል ያለው የአድሎ ግንዛቤ ህዝቡን እጅግ አምሮት ለዓመታት የማያቋረት ሰላማዊም አመጻዊም ሰልፍ እንዲካሄድ አድርጓል።
ይህን አዝማሚያ እንኳን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምንም ሊያቆመው አይችልም። ያለፈው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጀ እንዳላቆመው እናስታውስ! ትልቅ የፖለቲካ ለውጥ ብቻ ነው የህዝቡን ቅሬታ መመለስ የሚችለውና መሰረታዊ የፖለቲካ ብልሽቶችን ማስተካከል የሚችለው።
ምናልባት አንዳንድ ተቃዋሚዎች ስለኢህአዴግ ያላቸው ግንዛቤ የተጋነነ ስለሆነ በቀላሉ የተስፋ ምቁረጥ ባህሪ አላቸው። ይህ አዋጅ የህዝቡን ተቃውሞ ያቆመዋል ያከሽፈዋልና ከምርጫ 97 በኋላ እንደሆነው ለበርካታ ዓመታት የኢህአዴግ አገዛዝ ይቀጥላል ብለው ያምናሉ። ይህ ምን ያህል የተሳሰት እንደሆነ የሚያሳየው የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችንም ስለማያስቡት ነው! ስልጣናቸው እንደተነጋ ለሁሉም ግልጽ ነው። የሚሉትም ነገሮች፤ የሚወጣው ሚስጥሮች፤ የሚያደርጉት ድርጊቶች ሁሉ ይህንን ይመሰክራል። እስረኞችን የፈቱት ብርሀን ስላዩ አይደለም። ተሃድሶ እያሉ እርስ በርስ የሚፋጁት ከንቱ አይደለም። እነ ለማ መገርሳ እራሳቸውን ከፍ ያደረጉት አለ ምክንያት አይደለም። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያስፈለገውም ክንያት አለው! የህዝቡ ተቃውሞ ጋብ ይል ይሆናል ማለትም አለበት ግን ቀስ በቀስ ይቀጥላል ለውጥ እስኪመጣ።
ሌላው ማስተካከል የምወደው የተሳሳተ የሚመስለኝ አመለካከት ስለ ጦር ስራዊቱ ነው። የጦር መሪዎቹ ባብዛኛው የህወሓት አባሎች ቢሆኑም ጦሩ እራሱ ባብዛኛው አይደለም። ጠመንጃ የያዘው ኦሮሞ፤ አማራ፤ ሲዳማ ወዘተ ነው። ጦር ሰራዊት ውስጥ የታወቀ የፖለቲካ ክፍፍል አለ። በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወታደሩ ብዙ ቅራኔዎች ካላጋጠሙትና ባብዛኛው ሰላማዊ የፍተሻና የሚመሳሰል የማያስጨንቅ ስራ የሚሰራ ከሆነ ይህ ክፍፍል ብዙ ላይታይ ይችላል። ግን ኃይለኛ አመጽ ከተነሳና በርካታ ቅራኔና ግድያ ከተከሰተ የወታደሩ የውስጥ የፖለቲካ ክፍፍል - በዘር ምክንያት - መውጣት ይጀምራል። ጦር ሰራዊቱን ወደ መከፋፈል ይገፋዋል። የጦር ሰራዊት መሪዎች ደግሞ ይህንን "risk" እጅግ ይፈራሉና ይሸሻሉ። ግን የአቸኳ አዋጁ በቆየ ቁጥር ይህ የመከሰቱ እድል እየጨመረ ስለሚሄድ የጦር ሰራዊቱ መሪዎችም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቶሎ እንዲቋረጥ ነው የሚፈልጉት።
ስለዚህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ብዙ ሌከርም አይችልም። ጊዜ መግዣ ነው። የአገሪቷ መንገዶችና ንግዶች እንዲንቀሳቀሱና ሰውዉ ለተወሰነ ጊዜ ቢሆንም ወደ ዘውትር ኑሮ እንዲመለስ ነው። ፖለቲከኞቹ ማቀዳቸውንና ውይይታቸውን እንዲቀጥሉ ነው። አይከፋም። የአገሪቷ የፖለቲካ ጠቅላላ አዝማሚያውን አይቀይርም ሊቀይርም አይችልም። ኢህአዴግ ባለበት አወቃቀር ከስጣን መውረዱ አቀርም። ወይ ለጉድ ይቀየራል ወይም ከስልጣን ይወርዳል። ጉዳዩ አልቋል። አሁን የጭዋታው መጨረሻ ("end-game") ላይ ነን። ስለዚህ ስለ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከመጨነቅ ይልቁኑ እኛ ተቃዋሚዎች በርካታ የተጠራቀመ የቤት ስራችንን እንስራ። ጊዜውን እንጠቀምበት።
ዛሬ የፀደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በርካቶች ከሚያስቡት ተቃራኒ አስተዋሶ ነው የሚኖረው። የነጻነትን እንቅስቃሴውን ይጠቅማል እንጂ አይጎዶም።
ለማስታወስ ያህል ባለፉት ዓመታት ያየነው የህዝብ ተቃውሞና የኢህአዴግ የስልጣን መገለባበጥ በአንድ ጊዜ የምነጣ አይደለም። ለረዥም ዓመታት እየተንከባለለ የመጣ አዝማሚያ ነው። የህዝብ ብሶትና የአስተዳደሩ መሰረታዊ ችግር ያመታው ተቃውሞ ነው። የጎሳ አስተዳደርና የአውራ ፓርቲ የልማታዊ መንግስት አስተዳደር እንደ እሳትና ጭድ የሆኑ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለሞች በመሆናቸው ኤኮኖሚው ምንም ቢያድግም የህዝብ ቁታ እንዲንር አድርጓል። ይህ አገዛዝ ያመጣው በህዝቡ መካከል ያለው የአድሎ ግንዛቤ ህዝቡን እጅግ አምሮት ለዓመታት የማያቋረት ሰላማዊም አመጻዊም ሰልፍ እንዲካሄድ አድርጓል።
ይህን አዝማሚያ እንኳን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምንም ሊያቆመው አይችልም። ያለፈው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጀ እንዳላቆመው እናስታውስ! ትልቅ የፖለቲካ ለውጥ ብቻ ነው የህዝቡን ቅሬታ መመለስ የሚችለውና መሰረታዊ የፖለቲካ ብልሽቶችን ማስተካከል የሚችለው።
ምናልባት አንዳንድ ተቃዋሚዎች ስለኢህአዴግ ያላቸው ግንዛቤ የተጋነነ ስለሆነ በቀላሉ የተስፋ ምቁረጥ ባህሪ አላቸው። ይህ አዋጅ የህዝቡን ተቃውሞ ያቆመዋል ያከሽፈዋልና ከምርጫ 97 በኋላ እንደሆነው ለበርካታ ዓመታት የኢህአዴግ አገዛዝ ይቀጥላል ብለው ያምናሉ። ይህ ምን ያህል የተሳሰት እንደሆነ የሚያሳየው የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችንም ስለማያስቡት ነው! ስልጣናቸው እንደተነጋ ለሁሉም ግልጽ ነው። የሚሉትም ነገሮች፤ የሚወጣው ሚስጥሮች፤ የሚያደርጉት ድርጊቶች ሁሉ ይህንን ይመሰክራል። እስረኞችን የፈቱት ብርሀን ስላዩ አይደለም። ተሃድሶ እያሉ እርስ በርስ የሚፋጁት ከንቱ አይደለም። እነ ለማ መገርሳ እራሳቸውን ከፍ ያደረጉት አለ ምክንያት አይደለም። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያስፈለገውም ክንያት አለው! የህዝቡ ተቃውሞ ጋብ ይል ይሆናል ማለትም አለበት ግን ቀስ በቀስ ይቀጥላል ለውጥ እስኪመጣ።
ሌላው ማስተካከል የምወደው የተሳሳተ የሚመስለኝ አመለካከት ስለ ጦር ስራዊቱ ነው። የጦር መሪዎቹ ባብዛኛው የህወሓት አባሎች ቢሆኑም ጦሩ እራሱ ባብዛኛው አይደለም። ጠመንጃ የያዘው ኦሮሞ፤ አማራ፤ ሲዳማ ወዘተ ነው። ጦር ሰራዊት ውስጥ የታወቀ የፖለቲካ ክፍፍል አለ። በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወታደሩ ብዙ ቅራኔዎች ካላጋጠሙትና ባብዛኛው ሰላማዊ የፍተሻና የሚመሳሰል የማያስጨንቅ ስራ የሚሰራ ከሆነ ይህ ክፍፍል ብዙ ላይታይ ይችላል። ግን ኃይለኛ አመጽ ከተነሳና በርካታ ቅራኔና ግድያ ከተከሰተ የወታደሩ የውስጥ የፖለቲካ ክፍፍል - በዘር ምክንያት - መውጣት ይጀምራል። ጦር ሰራዊቱን ወደ መከፋፈል ይገፋዋል። የጦር ሰራዊት መሪዎች ደግሞ ይህንን "risk" እጅግ ይፈራሉና ይሸሻሉ። ግን የአቸኳ አዋጁ በቆየ ቁጥር ይህ የመከሰቱ እድል እየጨመረ ስለሚሄድ የጦር ሰራዊቱ መሪዎችም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቶሎ እንዲቋረጥ ነው የሚፈልጉት።
ስለዚህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ብዙ ሌከርም አይችልም። ጊዜ መግዣ ነው። የአገሪቷ መንገዶችና ንግዶች እንዲንቀሳቀሱና ሰውዉ ለተወሰነ ጊዜ ቢሆንም ወደ ዘውትር ኑሮ እንዲመለስ ነው። ፖለቲከኞቹ ማቀዳቸውንና ውይይታቸውን እንዲቀጥሉ ነው። አይከፋም። የአገሪቷ የፖለቲካ ጠቅላላ አዝማሚያውን አይቀይርም ሊቀይርም አይችልም። ኢህአዴግ ባለበት አወቃቀር ከስጣን መውረዱ አቀርም። ወይ ለጉድ ይቀየራል ወይም ከስልጣን ይወርዳል። ጉዳዩ አልቋል። አሁን የጭዋታው መጨረሻ ("end-game") ላይ ነን። ስለዚህ ስለ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከመጨነቅ ይልቁኑ እኛ ተቃዋሚዎች በርካታ የተጠራቀመ የቤት ስራችንን እንስራ። ጊዜውን እንጠቀምበት።
Subscribe to:
Posts (Atom)