እስካሁን በሰው ልጅ ታሪክ አንድ ሀገር በ«ልማት» ተመስርቶ ተገንብቶ አያውቅም። ሰዎች ከአንድ መንደር ሲሆኑ፤ የጋብቻ እና የደም ትሥስር ሲኖራቸው፤ ባህላቸው አንድ ሲሆን፤ ለመተባበር እና ለመረዳዳት ብለው በተፈጥሮአዊ በአዎንታዊ መንገድ «ሀገር» ይሆናሉ። ሃብት ፍለጋ፤ ጦርነት፤ ግጭት ወዘተም በአሉታዊ መንገድ በሀገር ምስረታ ሚና ይጫወታል። ግን «ልማት» ሀገር አይገነባም። ትሥሥር አይፈጥርም። ዝምድና አይፈጥርም። ፍቅር የለውም። ከልብ መረዳዳት አይጠይቅም። ሀገር አይገነባም።
ለማስታወስ ያህል የተወሰነ ዓመት በፊት ህዝብን የምርጫ 1997 ችግርን ለማስረሳት፤ «ጠባብ» የጎሳ ብሄርተኝነትን ለመዋጋት፤ መንግስትን ሊጥል የሚችል መሃበረሰባዊ ክፍፍልን ለማስወገድ ኢህአዴግ «ልማታዊ መንግስት» ብሎ አወጀ። ኦሮሞ፤ አማራ፤ ትግሬ፤ ሲዳማ ወዘተ ብሄር ብሄረሰቦች አንድ መሆን ባይችሉም በ«ልማት» ዙርያ አንድነት ይፈጥራሉ ወይንም ግጭት ይቀንሳሉ ተብሎ ነው «ልማት» የታወጀው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/ethnic-federalism-kills-meles.html)። የዚህ የልማት ዘመቻ ደግሞ ታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ነው ተብሎ የሳቸው ምስሎች ከነ ልማት ምስሎች ጋር በማርክሲስት አይነት ስዕሎች በየቦታው ተለጠፉ።
ልማቱ መጣ ኤኮኖሚው በፍጥነት አደገ። ግን ህዝቡ ይበልጥ ተከፋፈለ። ግጭቶች እየጨመሩ እየጠነከሩ ሄደ። ሰላም እና ፍቅር እየጠፋ ሄደ። የግብረ ገብ እጦቱ በአስፈሪ መልክ በዛ አገሩን አጠለቀለቀ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_31.html)። «ልማት» ወደ «ገንዘብ» ተተርጉሞ ለገንዘብ ብለን እናታችንን የምንሸጥ ስባዊነት-ቢስ ማህበረሰብ ሆንን። ይበልጥ ተከፋፈልን። «ልማት» የሚለው መፈከር አልሰራም።
ግን አሁንም ስለ «ልማት» እንሰማለን። «ለምን አንድ ሆነን ተፋቅረን ሁላችንም ወደ ልማት አንሄድም?» ይባላል። «ሀገራችንን በጋራ እናሳድጋት» ሲባል እንሰማለን። «አንድ ከሆነን ሀገራችን እንደ ሌሎች ሀገራት ትበለጽጋለች!» ይባላል።
አዎን ልማት እና እድገት አይከፋም። ግን ልማት ሀገር እና ህዝብ አያደርግም ወደፊትም ሊያደርግ አይችልም። ሀገር እና ህዝብ የሚያደርገን «ፍቅር» እና «ሰላም»፤ «እውነተኛ ዝምድና እና ትሥስር»፤ «መደጋገፍ» እና «መረዳዳት»፤ «አባቶችንና ተውፊትን በጋራ ማክበር» ወዘተ። እነዚህ ጊዜያዊ ሳይሆኑ ዘላቂያዊ ነገሮች ናቸው። ልክ እንደ ሃብት ቤተሰብን እንደማይፈጥር እንደማይገነባ ሀገርንም አይፈጥርም አይገነባም።
ይህን ስለተረዱ ነው ጠ/ሚ አብይ አህመድን ታላቅ የሚያረጋቸው። የሳቸው ትኩረት በጊዜያዊ አላፊ ትናንሽ ነገሮች ሳይሆን በከፍ ያሉት (higher) ነገሮች ነው። ህዝባችን ከልማት በላይ ደስታ እንዲኖረው ነው የምፈልገው ብለዋል። ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያው ትውፊታዊ አመለካከት ነው። ኢትዮጵያዊ ከገንዘብ፤ ምቾት፤ ሃባት ወዘተ ይልቅ ፍቅር፤ ሰላም፤ ፍትህ ወዘተን ያስቀድማል በሃይማኖትን እና ትውፊቱ ምክንያት። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ መልዕክት ምዕራቢያዊያንን በሚያስገርም ሁኔታ ህዝባችንን ያስደሰተው።
ስለዚህ የኛ መሪዎች እና ፖለቲከኞች እንዲሁም እኛ ብዙሃን «ልማት» የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ላሁን ብንተወው እና ትክክለኛ ቦታው ብንሰጠው ጥሩ ይመስለኛል። ፍቅር እና ሰላማችንን እናዳብር። ክፍፍሎቻችንን በግልጽ እና በትህትና እንወያይ። ይቅርታ እንባባል እርስ በርሳችን እንቆርቆር። ሀገርን እንገንባ። እዚህ ላይ እናተኩር። ከዛ በኋላ ልማት እንደ ሁለተኛ ምርት (byproduct) ይመጣል። ባይፈጥንም ፍቅራችን ያኖረናል።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ፍቅር. Show all posts
Showing posts with label ፍቅር. Show all posts
Wednesday, 5 September 2018
Friday, 3 August 2018
የበታችነት ስሜት
ሰላሳ አርባ ዓመታት በፊት ከሀገሩ የሚሰደድ ኢትዮጵያዊ ወደ ምዕራብ ሀገር ሲሄድ ከሀገሩ ይበልጥ «የሰለጠነ» እና «የበለጸገ» ሀገር አግኝቻለሁ ብሎ ያስቡ ነበር። የምዕራብ ሀገሮች በሀብት፤ በብልጽግና፤ በግብረ ገብነት፤ በቅልትፍና (efficiency)፤ በንፅህና ወዘተ ከኢትዮጵያ የላቁ መሆናቸው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ያምን ነበር።
ሆኖም ግን ስደተኛው ምዕራብ ሀገሮችን ቢያደንቅም የሚተችባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ለምሳሌ «ዘረኝነትን ያራምዳሉ» ይላል። በአዲስ ቅኝ ግዛት ታዳጊ ሀገራትን ያጠቃሉ ይዘርፋሉ። ኢትዮጵያ ለቅኝ ግዛት ስለማትመች እነ አሜሪካ ካዷት እና በደርግ አይነቱ አረመኔ መንግስት በማርክሲዝም እንድትገዛ አደረጉ። በተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ የሆኑ መንግስታትን ይገለብጣሉ። ወዘተ። ኢትዮጵያዊ ስደተኛው ልሂቃኑም የምዕራብ ሀገሮችን በዚህ መልኩ ይከሱ ነበር።
በርካታ ስደተኞች እንደዚህ በማለት የምዕራብ ሀገሮችን ተችተው ሀገራቸው ኢትዮጵያ ችግሮች ቢኖሯትም ከነዚህ ሀገሮች በማንነት ደረጃ አታንስም ብለው ያምኑ ነበር። በዚህ ምክንያት የሀገር የማንነት የበታችንነት ስሜት (inferiority complex) ገና ብዙ አላደረባቸውም። በኢትዮጵያዊነቱ ያለው ኩራት ብዙ አልተቦረቦረም ነበር።
ግን ጊዜው ባለፈ ቁጥር ኢትዮጵያ «አልሻሻል» ስትል ባንጻሩ የምዕራብ ሀገሮች በብልጽግና እይናሩ እና አንዳንድ ልውጦች ሲያደርጉ የፕሮፓጋንዳ ስልታቸውም እየዳበረ ሲሄድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛው በአሙሮው የምዕራቡን ዓለም እያበለጠ ሀገሩ ኢትዮጵያን እያሳነሰ ሄደ። ቀስ በቀስ የበታችነት ስሜት (inferiority complex) እያደረበት ሄደ። የህ የበታችነት ስሜት ወደ ሀገር ቤትም ገባ።
ወደ ምዕራብ ሀገር የተሰደደ ኢትዮጵያዊ ደህና ገቢ ማግኘት እና ሃብት ማከማቸት ቻለ። ስደተኛው ድሮ ቢገጥመውም ባይገጥመውም የሚያማርረው ዘረኝነቱ እየቀነሰ ሲሄድ አየ። ለነገሩ ዘረኝነቱ ድሮም ኑሮውን ከማሻሻል አልከለከለውም ነበር። አህን ግን ጭራሽ በጥቁርነቱ ስራ ከማጣት ማግኘት ጀመረ! ባሜሪካ ልጆቹ በጉብዝናቸው ብቻ ሳይሆን የጭቁን (ጥቅር) ዘር በመሆናቸው ስኮላርሺፕ ማግኘት ጀመሩ። የአሜሪካ ኑሮ ከድሮም ይበልጥ እየተመቸ ሄደ።
ይህ ስደተኛ ኑሮው «እየተሳካለት» በሄደ ቁጥር አሜሪካ በሱ አይን ይበልጥ እያማረች ሄደች። ፍትሐዊና መሐበራዊ ስነ ሥርዐቱን ከድሮም ይበልጥ ማደነቅ ጀመረ። ለሴቶች፤ ለልጆች፤ ለጥቁሮች ወዘተ ያለው «መብት» እና ጥንቃቄ ከኢትዮጵያ ጋር ሲያነጻጽረው ይገርመዋል። በፖለቲካ ደረጃ «ዴሞክራሲ» አምላኩ ሆነ «ሲኤንኤን» (CNN) መላዕክቱ ሆነ። በአንጻሩ ኢትዮጵያ በስደተኛው አይን እየቀነሰች እየወረደች ሄደች። አልሻሻል አለች እየባሰችም ሄደች። ስደተኛው ሀገሩን በጎበኛት ቁጥር ከአሜሪካ ጋር እያንጻጸረ ዘመዶቹን ያደነቁራል። በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ለማሳየት ያህል ዘመዱን ከ«ሀገር ቤት» ለመውጣት በርካታ አስር ሺዎች ዶላር ይከፍላል።
ዛሬ በኛ በኢትዮጵያውያን የዝቅተኘት መንፈስ በደምብ አድሮብናል ማለት ከእውነት የራቀ አይመስለኝም። ግን ይህ መንፈስ እውነትን ነው የሚያንጸባርቀው? እውነት ዝቅተኛ ህብረተሰብ ነን? ወይም ሀገራችን ዝቅተኛ ነው? ይበልጥ ታላቅ የሆነው ጥያቄ ሙሉ ሰው ለመሆን ወይንም በዘመኑ ቋንቋ «መሻሻል» ከፈለግን እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን ይኖርብናል? ምናልባት ዘፈናችን ጭፈራችን ምግባችንን ለትዝታ ብለን ጠብቀን በሌላው በሙሉ እንደነሱ እንደ ምዕራባዊያን መሆን ይኖርብን ይሆን?
እዚህ ላይ በቀለም ትምሕርት ከምንማረው በሚዲያ ከምንሰማው ፕሮፓጋንዳና ተራ «እውቀት» ወጥተን እናስብ። በአዲሱ ቅን ግዛት የተገዛውን አእምሮአችንን ነፃ እናውጣው የብዥታ መነጽራችንን እንጣል። በመጀመርያ እስቲ ምንድነው «ስልጣኔ» ብለን እንጀምር። ጥያቄውን በምሳሌ ኃይል ለመመርመር ታዋቂውን የሮሜን ስልጣኔን እንመልከት።
በክርስቶስ ዘመን በርካታ አይሁዶች ወደ ሀገራቸውን ወርሮ የገዛው ሮሜ ይፈልሱ ነበር። አንድ አይሁድ ወደ ሮሜ ሲሄደ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ከሀገሩ ወደ አሜሪካ እንደመሄድ እናመሳስለው። ሮሜ ሀብታም ነበረች። «ስደተኞችን» መጤዎችን ትቀበላለች ታስተናግዳለች ታበለጽጋለች። ውጣ ውረድ ቢኖረውም መጤዎች የሮሜ ዜጋ የመሆን እድል አላቸው። የሮሜ ዜግነት አንደ ይሁዳ ዜግነት በጎሳ በብሄር በደም የተወሰነ አይደለም ማንም የሮሜ ዜጋ መሆን ይችላል። የሮሜ ፍርድ ቤቶች በደምብ ይሰራሉ በተለይ ለሮሜ ዜጎች እውነተኛ ፍትሕ ይሰጣሉ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ችግር ባጋጠመው ቁጥር አይሁዶች ሲገሱት ሲሉ የሮሜ ዜግነቱን ተጠቅሞ ፍርድ ይጠይቃል! በሮሜ ፍርድ ቤት ትክክለኛ የፍርድ ሂደት እንደሚጠብቀው ስለሚያውቅ ነው። የሮሜ መንግስታዊ አስተዳደር ፍፁም ባይሆንም ከሌሎች አንጻር «የሰለጠነ» ነበር። «ዴሞክራሲ» አይነት ከነ ምክር ቤት አለው። በሮሜ የማሕበራዊ ብረ ገብ አለ። የሴቶች «መብቶች» ከሌሎች ሀገሮች ከይሁዳ ይልቅ የተከበሩ ናቸው። በስነ ሥርዓት በኩልም ሮሜ የስለጠነች ናት። መንገዶቿ ንፁ ናቸው። መንገደኛ ለመንገደኛ ጎረቤት ለጎረቤት አገልጋይ ለባለጉዳይ ያለው ግንኙነት በጥቅም የተሳሰረ ሰላማዊና የተቀላጠፈ (efficient) ነው። የድሮ «ሮሜ» ስልጣኔ እንደዚህ ይመስላል።
ለዚህም ነው አይሁዶችም ሌሎችም ወደ ሮሜ የሚፈልሱት ሃብቱን እና ስልጣኔውን ፈልገው። ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ወደ አሜሪካ እንደምንፈልሰው «ህይወትን ለማሻሻል» ወደ በአድ ሀገር ይሄዱ ነበር። ግን ሮሜ የይሁዳ ቅኝ ገዥ ነበረች! አይሁዶች ወደ የሚገዛቸው ሀገር ነበር የሚሄዱት። ወደ ዓለምን በሙሉ በጉልበቷ የተቆጣጠረቹ ሮሜ ነበር ለተሻለ ኑሮ ብለው የሚሄዱት። ግን አይሁዶቹንም ሌሎች መጤዎችንም የሮሜ ስልጣኔ ክፋነቷን እንዳያዩ አድርጓቸዋል አሳውራቸው። ለነሱ ሮሜ የብልጽግና ሀገር እንጂ የክፋት ሀገር አልነበረትም። ሮሜ ሀገራቸው ይሁዳ የሌላት ነገሮች ሁሉ አላት። በዚህ ምክንያት በራሳቸው ባህልና ማንነት ዝቅጠኝነት ተሰማቸው እንደ ሮሜዎች መሆነ ፈለጉ ወደ ሮሜ ህብረተሰብ ተቀላቀሉ።
ይህ ምሳሌ ስለ «ስልጣኔን» ምን ያስተምረናል? ለብዙዎቻችን ስልጣኔ ሀብት ማለት ነው። ሀብት ካለ ሌሎች ጉድለቶች አያታዩንም። ስልጣኔ «ቴክኖሎጂ» ይመስለናል። የሮሜ የከተማው ቧምቧ እና ፍሳሽ ስራ አይሁዶችን ይገርማቸው ነበር። ስልጣኔ ቅልጥፍና (efficiency) ይመስለናል። የሮሜ የመነግስት መዋቅሮች በተለይ ጦር ሰራዊቱ ግቡን በቀላሉ ያስፈጽም ነበር። ስልጣኔ ፍትሕ ነው። ስልጣኔ ግብረ ገብ እና ስነ መግባር ነው።
እነዚህን ሁሉ ስንመለከት ግን ባጭሩ ስልጣኔ ማለት ነግ በኔን በደምብ ማወቅ ነው። አካባቢዬን አላቆሽሽም ሌሎችን መንገደኞችን ውድጅያቸው ሳይሆን ንፁ አካባቢ ስለሚበጀኝ እኔ ካላቆሸሽኩኝ ሌሎችም ስለማያቆሽሹ ነው። እኔ መኪና የማሽከረክረው ሕግ አክብሬ ነው ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎችን ስለምወዳቸው ሳይሆን ሁላችንም በትክክል ካሽከረከርን ሁላችንም በፍጥነንት እና በሰላም የምንፈልግበት ቦታ ለመድረስ ስለሚያመችን ነው። መንግስቴ ለደሆች እርዳታ እንዲያደርግ እወዳለሁ ሰላምን ለመጠበቅ እኔም ነገ ብወድቅ እርዳታ እንዳገኝ። ወዘተ። ይህ ነው ስልጣኔ ባጭሩ። ሮሜም አሜሪካም የትም ህዝብ ሰላምና ሀብት እያገኘ ሲሄድ ለራሱ ለግል ምቾቱ የሚሆን አሰራሮች ስነ ምግባሮች እየገባው በተግባር መዋል ይጀምራል።
ግን ይህ ስልጣኔ ከጥሩነት፤ በጎነት፤ ሰላም ወዳድነት እና ከፍቅር ጋር አይገናኝም። ነግ በኔ በጎነትም ፍቅርም አይደለም። «የሰለጠነ» ራስ ወዳድነት ነው። ማንም ከጊዜ በሚያመጣው ልምድ በኋላ የሚደርስበት ነው። ማንም ደግሞ ችግሮች ሲያጋጥሙት ካልተመቸው የሚተወው ነው። ሮሜ ለራሷ የሰለጠነች ነበር ለሌሎች ሀገሮች ግን የክፋት መዓበል ነበረች። ዛሬ አሜሪካም አውሮፓም ሌሎችም ለራሳቸው የሰለጠኑ ናቸው ግን ከጠረፍ ውጭ አይደሉም።
ስለዚህ ይህ ሀገር የሰለጠነ ነው የኔ ሀገር አይደለም ብለን የበታችነት ስሜት ሊኖረን ይግባል? በፍፁም! ስልጣኔ ማንንነት አይደለም። ስልጣኔ ይመጣል ይሄዳል በዓለም ታሪክ በተለያዩ ቦታዎች ተገንብቷል ፈርሷል። ስልጣኔ ከፍቅርና በጎነት አይገናኝም። የሰው ማንነት ግን በጎነት፤ ፍቅር፤ ሰላም ወዘተ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ እነዚህን የሚሽህ እስከሆነ መቼም የበታችነት ሊሰማው አይገባም! ከፍቅር ይልቅ «ብልጭልጭን» ሲያመልክ ነው ችግሩ የሚመጣው።
ይህን ተክትሎ እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን አለብን ብሎ ማሰቡም ተገቢ አይደለም። ለምን ብትሉ የምዕራባዊያን ርዕዮት ዓለም ከኢትዮጵያዊነት ትውፊትና ማንነት 180 ዲግሪ የተቃረነ ነው። የምዕራባዊ አስተሳሰብ የሰው ልጅ የዓለም ቁንጮ አድርጎ ያስቀምጠዋል። እግዚአብሔር የለም ወይንም ምንም ሚና አይጫወትም ይላል። ኢትዮጵያዊ ግን በትውፊታችን ፈጣሪ ነው በአምሳሉ የፈጠረን ብለን እናምናለን ሁሉ ነገራችንም ከዛ ይከተላል። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ አህመድ የይቅርታ፤ ፍቅር እና ሰላም መልዕክቶችን በደስታ እና ጉጉት የምንቀበለው። እንደዚህ አይነቱ መልዕክት የተም ምዕራብ ሀገር እንደ ህፃንነት ነበር የሚታየው። ስለ ልማት፤ ነፃነት፤ መብት ነው የምዕራብ ሀገር ውይይት። እግዚአብሔር የለምና።
ታሪክ ረዥም ነው። 500 ዓመት በፊት ቻይና ከሁሉም «የሰለጠነች» ነበር። 60 ዓመት በፊት ቻይና ወደ 40 ሚሊዮን ህዝቦቿን ገደለች ግማሽ ሀገሪቷ በርሃብ እየተሰቃየ ነበር። 2000 ዓመት በፊት ስሜን አውሮፓ በሮሜዎች ዘንድ የያልሰለጠና የአረመኔ ስፍራ ነበር። ዛሬ ደግሞ ከዓለም በሙሉ የሰለጠው ጎራ ይባላል። 60 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ታላቅ ክብር ነበራት። ዛሬ እንደ ለማኝ ትታያለች። እኛ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ብናስታውስ ጥሩ ይመስለኛል።
እውነት ስልጣኔ ፍቅር እና ሰላም ነው። የኛ የኢትዮጵያዊያን በዚህ ረገድ ከማንም ልናንስም ልንበልጥም እንችላለን የኛ ፋንታ ነው። ግን የሰው ልጅ በመሆናችን ከማንም አናንስም አንበልጥምም። የዝቅተኛ ስሜታችንም በምንም መለክያ ተገቢ አይደለም። እጅግ ጎጂም ነው። ሌላውን ምዕራባዊያንም ለመገልበጥ መሻህ ዋጋ የለውም ጎጂ ነው። ማንነታች ከፈጣሪያችን የተሰጠን ነውና ምንም የምናፍርበት ሊሆን አይገባም። እርግጥም ለሌሎች ምሳሌ ሆነን መገኘት ነው ያለብን ድሮ ሆነን እናውቃለን አሁንም የማንሆንበት ምክንያት የለም።
ሆኖም ግን ስደተኛው ምዕራብ ሀገሮችን ቢያደንቅም የሚተችባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ለምሳሌ «ዘረኝነትን ያራምዳሉ» ይላል። በአዲስ ቅኝ ግዛት ታዳጊ ሀገራትን ያጠቃሉ ይዘርፋሉ። ኢትዮጵያ ለቅኝ ግዛት ስለማትመች እነ አሜሪካ ካዷት እና በደርግ አይነቱ አረመኔ መንግስት በማርክሲዝም እንድትገዛ አደረጉ። በተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ የሆኑ መንግስታትን ይገለብጣሉ። ወዘተ። ኢትዮጵያዊ ስደተኛው ልሂቃኑም የምዕራብ ሀገሮችን በዚህ መልኩ ይከሱ ነበር።
በርካታ ስደተኞች እንደዚህ በማለት የምዕራብ ሀገሮችን ተችተው ሀገራቸው ኢትዮጵያ ችግሮች ቢኖሯትም ከነዚህ ሀገሮች በማንነት ደረጃ አታንስም ብለው ያምኑ ነበር። በዚህ ምክንያት የሀገር የማንነት የበታችንነት ስሜት (inferiority complex) ገና ብዙ አላደረባቸውም። በኢትዮጵያዊነቱ ያለው ኩራት ብዙ አልተቦረቦረም ነበር።
ግን ጊዜው ባለፈ ቁጥር ኢትዮጵያ «አልሻሻል» ስትል ባንጻሩ የምዕራብ ሀገሮች በብልጽግና እይናሩ እና አንዳንድ ልውጦች ሲያደርጉ የፕሮፓጋንዳ ስልታቸውም እየዳበረ ሲሄድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛው በአሙሮው የምዕራቡን ዓለም እያበለጠ ሀገሩ ኢትዮጵያን እያሳነሰ ሄደ። ቀስ በቀስ የበታችነት ስሜት (inferiority complex) እያደረበት ሄደ። የህ የበታችነት ስሜት ወደ ሀገር ቤትም ገባ።
ወደ ምዕራብ ሀገር የተሰደደ ኢትዮጵያዊ ደህና ገቢ ማግኘት እና ሃብት ማከማቸት ቻለ። ስደተኛው ድሮ ቢገጥመውም ባይገጥመውም የሚያማርረው ዘረኝነቱ እየቀነሰ ሲሄድ አየ። ለነገሩ ዘረኝነቱ ድሮም ኑሮውን ከማሻሻል አልከለከለውም ነበር። አህን ግን ጭራሽ በጥቁርነቱ ስራ ከማጣት ማግኘት ጀመረ! ባሜሪካ ልጆቹ በጉብዝናቸው ብቻ ሳይሆን የጭቁን (ጥቅር) ዘር በመሆናቸው ስኮላርሺፕ ማግኘት ጀመሩ። የአሜሪካ ኑሮ ከድሮም ይበልጥ እየተመቸ ሄደ።
ይህ ስደተኛ ኑሮው «እየተሳካለት» በሄደ ቁጥር አሜሪካ በሱ አይን ይበልጥ እያማረች ሄደች። ፍትሐዊና መሐበራዊ ስነ ሥርዐቱን ከድሮም ይበልጥ ማደነቅ ጀመረ። ለሴቶች፤ ለልጆች፤ ለጥቁሮች ወዘተ ያለው «መብት» እና ጥንቃቄ ከኢትዮጵያ ጋር ሲያነጻጽረው ይገርመዋል። በፖለቲካ ደረጃ «ዴሞክራሲ» አምላኩ ሆነ «ሲኤንኤን» (CNN) መላዕክቱ ሆነ። በአንጻሩ ኢትዮጵያ በስደተኛው አይን እየቀነሰች እየወረደች ሄደች። አልሻሻል አለች እየባሰችም ሄደች። ስደተኛው ሀገሩን በጎበኛት ቁጥር ከአሜሪካ ጋር እያንጻጸረ ዘመዶቹን ያደነቁራል። በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ለማሳየት ያህል ዘመዱን ከ«ሀገር ቤት» ለመውጣት በርካታ አስር ሺዎች ዶላር ይከፍላል።
ዛሬ በኛ በኢትዮጵያውያን የዝቅተኘት መንፈስ በደምብ አድሮብናል ማለት ከእውነት የራቀ አይመስለኝም። ግን ይህ መንፈስ እውነትን ነው የሚያንጸባርቀው? እውነት ዝቅተኛ ህብረተሰብ ነን? ወይም ሀገራችን ዝቅተኛ ነው? ይበልጥ ታላቅ የሆነው ጥያቄ ሙሉ ሰው ለመሆን ወይንም በዘመኑ ቋንቋ «መሻሻል» ከፈለግን እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን ይኖርብናል? ምናልባት ዘፈናችን ጭፈራችን ምግባችንን ለትዝታ ብለን ጠብቀን በሌላው በሙሉ እንደነሱ እንደ ምዕራባዊያን መሆን ይኖርብን ይሆን?
እዚህ ላይ በቀለም ትምሕርት ከምንማረው በሚዲያ ከምንሰማው ፕሮፓጋንዳና ተራ «እውቀት» ወጥተን እናስብ። በአዲሱ ቅን ግዛት የተገዛውን አእምሮአችንን ነፃ እናውጣው የብዥታ መነጽራችንን እንጣል። በመጀመርያ እስቲ ምንድነው «ስልጣኔ» ብለን እንጀምር። ጥያቄውን በምሳሌ ኃይል ለመመርመር ታዋቂውን የሮሜን ስልጣኔን እንመልከት።
በክርስቶስ ዘመን በርካታ አይሁዶች ወደ ሀገራቸውን ወርሮ የገዛው ሮሜ ይፈልሱ ነበር። አንድ አይሁድ ወደ ሮሜ ሲሄደ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ከሀገሩ ወደ አሜሪካ እንደመሄድ እናመሳስለው። ሮሜ ሀብታም ነበረች። «ስደተኞችን» መጤዎችን ትቀበላለች ታስተናግዳለች ታበለጽጋለች። ውጣ ውረድ ቢኖረውም መጤዎች የሮሜ ዜጋ የመሆን እድል አላቸው። የሮሜ ዜግነት አንደ ይሁዳ ዜግነት በጎሳ በብሄር በደም የተወሰነ አይደለም ማንም የሮሜ ዜጋ መሆን ይችላል። የሮሜ ፍርድ ቤቶች በደምብ ይሰራሉ በተለይ ለሮሜ ዜጎች እውነተኛ ፍትሕ ይሰጣሉ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ችግር ባጋጠመው ቁጥር አይሁዶች ሲገሱት ሲሉ የሮሜ ዜግነቱን ተጠቅሞ ፍርድ ይጠይቃል! በሮሜ ፍርድ ቤት ትክክለኛ የፍርድ ሂደት እንደሚጠብቀው ስለሚያውቅ ነው። የሮሜ መንግስታዊ አስተዳደር ፍፁም ባይሆንም ከሌሎች አንጻር «የሰለጠነ» ነበር። «ዴሞክራሲ» አይነት ከነ ምክር ቤት አለው። በሮሜ የማሕበራዊ ብረ ገብ አለ። የሴቶች «መብቶች» ከሌሎች ሀገሮች ከይሁዳ ይልቅ የተከበሩ ናቸው። በስነ ሥርዓት በኩልም ሮሜ የስለጠነች ናት። መንገዶቿ ንፁ ናቸው። መንገደኛ ለመንገደኛ ጎረቤት ለጎረቤት አገልጋይ ለባለጉዳይ ያለው ግንኙነት በጥቅም የተሳሰረ ሰላማዊና የተቀላጠፈ (efficient) ነው። የድሮ «ሮሜ» ስልጣኔ እንደዚህ ይመስላል።
ለዚህም ነው አይሁዶችም ሌሎችም ወደ ሮሜ የሚፈልሱት ሃብቱን እና ስልጣኔውን ፈልገው። ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ወደ አሜሪካ እንደምንፈልሰው «ህይወትን ለማሻሻል» ወደ በአድ ሀገር ይሄዱ ነበር። ግን ሮሜ የይሁዳ ቅኝ ገዥ ነበረች! አይሁዶች ወደ የሚገዛቸው ሀገር ነበር የሚሄዱት። ወደ ዓለምን በሙሉ በጉልበቷ የተቆጣጠረቹ ሮሜ ነበር ለተሻለ ኑሮ ብለው የሚሄዱት። ግን አይሁዶቹንም ሌሎች መጤዎችንም የሮሜ ስልጣኔ ክፋነቷን እንዳያዩ አድርጓቸዋል አሳውራቸው። ለነሱ ሮሜ የብልጽግና ሀገር እንጂ የክፋት ሀገር አልነበረትም። ሮሜ ሀገራቸው ይሁዳ የሌላት ነገሮች ሁሉ አላት። በዚህ ምክንያት በራሳቸው ባህልና ማንነት ዝቅጠኝነት ተሰማቸው እንደ ሮሜዎች መሆነ ፈለጉ ወደ ሮሜ ህብረተሰብ ተቀላቀሉ።
ይህ ምሳሌ ስለ «ስልጣኔን» ምን ያስተምረናል? ለብዙዎቻችን ስልጣኔ ሀብት ማለት ነው። ሀብት ካለ ሌሎች ጉድለቶች አያታዩንም። ስልጣኔ «ቴክኖሎጂ» ይመስለናል። የሮሜ የከተማው ቧምቧ እና ፍሳሽ ስራ አይሁዶችን ይገርማቸው ነበር። ስልጣኔ ቅልጥፍና (efficiency) ይመስለናል። የሮሜ የመነግስት መዋቅሮች በተለይ ጦር ሰራዊቱ ግቡን በቀላሉ ያስፈጽም ነበር። ስልጣኔ ፍትሕ ነው። ስልጣኔ ግብረ ገብ እና ስነ መግባር ነው።
እነዚህን ሁሉ ስንመለከት ግን ባጭሩ ስልጣኔ ማለት ነግ በኔን በደምብ ማወቅ ነው። አካባቢዬን አላቆሽሽም ሌሎችን መንገደኞችን ውድጅያቸው ሳይሆን ንፁ አካባቢ ስለሚበጀኝ እኔ ካላቆሸሽኩኝ ሌሎችም ስለማያቆሽሹ ነው። እኔ መኪና የማሽከረክረው ሕግ አክብሬ ነው ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎችን ስለምወዳቸው ሳይሆን ሁላችንም በትክክል ካሽከረከርን ሁላችንም በፍጥነንት እና በሰላም የምንፈልግበት ቦታ ለመድረስ ስለሚያመችን ነው። መንግስቴ ለደሆች እርዳታ እንዲያደርግ እወዳለሁ ሰላምን ለመጠበቅ እኔም ነገ ብወድቅ እርዳታ እንዳገኝ። ወዘተ። ይህ ነው ስልጣኔ ባጭሩ። ሮሜም አሜሪካም የትም ህዝብ ሰላምና ሀብት እያገኘ ሲሄድ ለራሱ ለግል ምቾቱ የሚሆን አሰራሮች ስነ ምግባሮች እየገባው በተግባር መዋል ይጀምራል።
ግን ይህ ስልጣኔ ከጥሩነት፤ በጎነት፤ ሰላም ወዳድነት እና ከፍቅር ጋር አይገናኝም። ነግ በኔ በጎነትም ፍቅርም አይደለም። «የሰለጠነ» ራስ ወዳድነት ነው። ማንም ከጊዜ በሚያመጣው ልምድ በኋላ የሚደርስበት ነው። ማንም ደግሞ ችግሮች ሲያጋጥሙት ካልተመቸው የሚተወው ነው። ሮሜ ለራሷ የሰለጠነች ነበር ለሌሎች ሀገሮች ግን የክፋት መዓበል ነበረች። ዛሬ አሜሪካም አውሮፓም ሌሎችም ለራሳቸው የሰለጠኑ ናቸው ግን ከጠረፍ ውጭ አይደሉም።
ስለዚህ ይህ ሀገር የሰለጠነ ነው የኔ ሀገር አይደለም ብለን የበታችነት ስሜት ሊኖረን ይግባል? በፍፁም! ስልጣኔ ማንንነት አይደለም። ስልጣኔ ይመጣል ይሄዳል በዓለም ታሪክ በተለያዩ ቦታዎች ተገንብቷል ፈርሷል። ስልጣኔ ከፍቅርና በጎነት አይገናኝም። የሰው ማንነት ግን በጎነት፤ ፍቅር፤ ሰላም ወዘተ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ እነዚህን የሚሽህ እስከሆነ መቼም የበታችነት ሊሰማው አይገባም! ከፍቅር ይልቅ «ብልጭልጭን» ሲያመልክ ነው ችግሩ የሚመጣው።
ይህን ተክትሎ እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን አለብን ብሎ ማሰቡም ተገቢ አይደለም። ለምን ብትሉ የምዕራባዊያን ርዕዮት ዓለም ከኢትዮጵያዊነት ትውፊትና ማንነት 180 ዲግሪ የተቃረነ ነው። የምዕራባዊ አስተሳሰብ የሰው ልጅ የዓለም ቁንጮ አድርጎ ያስቀምጠዋል። እግዚአብሔር የለም ወይንም ምንም ሚና አይጫወትም ይላል። ኢትዮጵያዊ ግን በትውፊታችን ፈጣሪ ነው በአምሳሉ የፈጠረን ብለን እናምናለን ሁሉ ነገራችንም ከዛ ይከተላል። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ አህመድ የይቅርታ፤ ፍቅር እና ሰላም መልዕክቶችን በደስታ እና ጉጉት የምንቀበለው። እንደዚህ አይነቱ መልዕክት የተም ምዕራብ ሀገር እንደ ህፃንነት ነበር የሚታየው። ስለ ልማት፤ ነፃነት፤ መብት ነው የምዕራብ ሀገር ውይይት። እግዚአብሔር የለምና።
ታሪክ ረዥም ነው። 500 ዓመት በፊት ቻይና ከሁሉም «የሰለጠነች» ነበር። 60 ዓመት በፊት ቻይና ወደ 40 ሚሊዮን ህዝቦቿን ገደለች ግማሽ ሀገሪቷ በርሃብ እየተሰቃየ ነበር። 2000 ዓመት በፊት ስሜን አውሮፓ በሮሜዎች ዘንድ የያልሰለጠና የአረመኔ ስፍራ ነበር። ዛሬ ደግሞ ከዓለም በሙሉ የሰለጠው ጎራ ይባላል። 60 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ታላቅ ክብር ነበራት። ዛሬ እንደ ለማኝ ትታያለች። እኛ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ብናስታውስ ጥሩ ይመስለኛል።
እውነት ስልጣኔ ፍቅር እና ሰላም ነው። የኛ የኢትዮጵያዊያን በዚህ ረገድ ከማንም ልናንስም ልንበልጥም እንችላለን የኛ ፋንታ ነው። ግን የሰው ልጅ በመሆናችን ከማንም አናንስም አንበልጥምም። የዝቅተኛ ስሜታችንም በምንም መለክያ ተገቢ አይደለም። እጅግ ጎጂም ነው። ሌላውን ምዕራባዊያንም ለመገልበጥ መሻህ ዋጋ የለውም ጎጂ ነው። ማንነታች ከፈጣሪያችን የተሰጠን ነውና ምንም የምናፍርበት ሊሆን አይገባም። እርግጥም ለሌሎች ምሳሌ ሆነን መገኘት ነው ያለብን ድሮ ሆነን እናውቃለን አሁንም የማንሆንበት ምክንያት የለም።
Thursday, 12 July 2018
የቤት ሰራተኛ
አንድ ጓደኛዬ «የቤት ሰራተኛዬን እንደ ቤተሰብ ነው የምቆጥራት። ካስፈለገ እንጀራ መጋገርም ቤት ማጽዳትም እረዳታለሁ። ግዴታ ትምሕርትቤት እንድትማር አደርጋታለሁ…» ብሎ ነገረኝ። ምን ነው ይህ ያልተለመደ እንክብካቤ ብዬ ስጠይቀው እንዴት ለልጆቼ እንጀራ ጋግራ የምታበላውን አልንከባከባትም አለኝ! እውነት ነው፤ ሌሎቻችን እንዲሁ ቢገባን።
አንድ ሰሞን የቤት ሰራተኛ ፍለጋ አዲስ አበባን ከደላላ ወደ ደላላ ዚርን! ደላሎቹ ምን እንርዳችሁ ብለው በጉጉት ይጠይቁናል። የቤት ሰራተኛ ስንላቸው ፈገግራቸው የጠፋል። ሹፌር ወይንም የቀን ሰራተኛ ወዛደር ብንላቸው ይሻላቸው ነበር ብዙ አላቸው። ግን የቤት ሰራተኛ የላቸውም፤ ለነሱም ብርቅ ሆነዋል።
ብዙ የማቃቸው ቤተሰቦች አዲስ አበባም ከገጠር ከተሞችም የቤት ሰራተኞቻቸው በየ ሁለት ሶስት ወር ይለቃሉ አዲስ መቅጠር ይሆንባቸዋል። ወይንም ለመቅተር የገንዘብ አቅም የላቸውም። ወይንም ከመቀቃየር ተስፋ ቆርጠው አለ ሰራተኛ ይኖራሉ።
ዛሬ በአዲስ አበባም በመላው ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኛ ጠፍቷል። ወይንም በትክክለኛ አገላለጽ (እጅግ) ተወዷል። ለምን ይሆን? የ ኤኮኖሜ ምክንያቶች አሉ። የሰው ኃይል በጠቅላላው ተወዷል። ዛሬ የቀን የግንባታ ሰራተኛ በወር ወደ 3000 ብር ሊሰራ ይችላል። እንዲሁም የቤት ሰራተኛ ደሞዝ ጨምሯል። ሁለተኛ ምክንያት ዛሬ ሴት ልጆች ከድሮ ይልቅ በትምሕርታቸው ይገፋሉ። የገጠር ወይንም የድሃ ቤተሰብ ልጆቻችው እንዲማሩ ይፈልጋሉ እንጂ በልጅነታቸው ሰራተኛ እንዲሆኑ አይሰጧቸውም። ሶስተኛ ምክንያት ወደ አረብ ሀገር ሄዶ መስራት ነው። የአራብ ሀገር ክፍያ ይበልጣል ወደ «ውጭ» ሀገር መሄድም ምንም ችግር እንደሆነ መረጃ ቢኖርም ያጓጓል ይመስለኛል። በነዚህ ምክንያቶች የቤት ሰራተኞች ተወደዋልም አይገኙምም።
ከኤኮኖሚ ምክንያቶች በተጨማሪ ለቤት ሰራተኛ መጥፋት ማህበረሰባዊ ምክንያር አለ እና እዚህ ላይ ነው ማተኮር የምፈልገው። ዛሬ አንድ ሴት በህንጻ ጽዳት ስራ 2000 ብር በ ወር ታገኛለች። ከዚህ ብር የቤት ኪራይ፤ መጓጓዣ (ትራንስፖርት) እና የምግብ ወጪዎቿን ትከፍላለች። 1000 ከተረፋት ትልቅ ነገር ነው። ነይ በ2000 ብር የቤት ሰራተኛ ሁኚ የቤት ኪራይ፤ የመጓጓዣ እና የምግብ ወጪ አይኖርሽም ብንላት እምቢ ትላለች። ለምን ይሆን? ስራው ከባድ ስለሆነ አይደለም እትፍ ከባድ አይደለም። ነፃነቱ ይሆን እሱም 1000 ብር የሚያዋጣት አይመስለኝም። ምንም አይነት የሚመች የስራ ሁኔታዎች ብትዋዋልም የቤት ሰራተኛ መሆን አትፈልግም። ታድያ ምንድነው ምክንያቱ?
እኔ እንደሚመስለኝ ዋናው ምክንያት በባህላችን የቤት ሰራተኝነት እንደ ዝቅተኛ የሚናቅ ስራ ስለምንቆጥረው ነው። ይህን የዝቅተኝነት እና የመንናቅ ስሜት እጅግ ብዙ ብር ካልሆነ ብር አይተካውም። ተጎድቼ ውጭ ብሰራ ይሻለኛል ለብዙ ብር ከሰው ቤት ከምሰራ ነው ያለን አስተሳሰብ።
እስቲ ወደ ኋላ ሄደን የቤት ሰራተኞቻችንን እንዴት እንደምንይዝ እንደነበር እናስታውስ። 16 ሰዓት በቀን ይሰራሉ ለሌላው 8 ሰዓት ተጠሪ ናቸው። በወር አንድ ቀን እረፍት ቢኖራቸው ነው ይህም ላይከበር ይችላል። ኦርቶዶክስ ክርስትያን ነን የምንለው እንኳን እሁድ ቀን እረፍት መስጠት ቅዳሴም እንዲያስቀድሱ አንፈቅም (ከዚህ በላይ አሳዛኝ ነገር አላቅም)። እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ባርያ እንጮህባቸዋለን እናጎሳቁላቸዋለን። እንደማንም ሰው አድገው ወደፊት ማግባት እና ቤተሰብ ማፍራት እንደሚፈልጉም አንገነዘብም ልንገነዘብም አንፈልግም። ከቤተሰቦቻቸው ርቀው በመኖራቸው እኛ እንደ ሁለተኛ ቤተሰባቸው መሆን እንዳለብን አናስብም። በጠቅላላ ለራሳችን የማንወደውን እናደርግባችዋለን ለራሳችን የምንወደውን አናደርግላቸውም።
ይህ ስር የሰደደ ባህል ሆኖ የቤት ሰራተኛ እጅግ ዝቅተኛ ስራ መሆኑ ሁላችንም አሰሪዎችም ሰራተኞችም እናውቃለን። በዚህ ምክንያት ይመስለኛል በርካታ ሴቶች ከቤት ሰራተኛ ስራ የሚርቁት። ብዙ ብር ቢከፈላቸውም ከገንዘብ አንጻር ቢያዋጣቸውም «ዝቅተኛነቱን» «ውርደቱን» አይፈልጉትም።
የቶሎ የስራ መቀያየር ጉዳይሳ? ለምንድነው ብዙ የዘመኑ የቤት ሰራተኛዎች ገና ወር ሁለት ወር ሳይቆዩ ለቀው ወደ ሌላ ቤት የሚሄዱት። አንዱ ምክንያት የኤኮኖሚው ነው። ብዙ ስራ ስላለ የደሞዝ ጭማሬ ቶሎቶሎ ያገኛሉ። ሌላው ምክንያት ግን እንደሚመስለኝ የቤት ሰራተኝነት የማይፈለግ ስራ በመሆኑ ብዙ ችግር እና የማመዛዘን ድክመት ያላቸውን ሴቶች ናቸው ወደዚህ ስራ የሚገቡት። ይህ ምክንያት የስራ መቀያየራቸውን ብቻ ሳይሆን ሌሊችን ችግሮች እንደ ሌብነት ወዘተ ያስረዳል።
ለረዥም ዘመን የቤት ሰራተኞቻችንን ጎድተናል። በተዟዟሪ ሙሉ መሃበረሰባችንን ጎድተናል። የጎጂ የአሰሪ እና የንቀት ባህላችን ከትውልድ ወደትውልድ አስተላልፈናል። የአሁኑ የሰራተኛ እጥረት እስኩመጣ ድረስ ጥፋቶቻችን አልታዩንም ይሆናል ግን አሁን ጎልተው ሊታየን ይገባል። ጥፋታችንን አይተን አምነን መጸጸት፤ ንስሃ መግባት እና ይቅርታ መጠየቅ የሚኖርብን ይመስለኛል ይህን ጎጂ ባህላችንን በቋሚነት ለማስወገድ። ይህ ለህላችንም ለጠቅላላ ህብረተሰባችን ሰላም እና ፍቅርም አስፈላጊ ይመስለኛል።
አንድ ሰሞን የቤት ሰራተኛ ፍለጋ አዲስ አበባን ከደላላ ወደ ደላላ ዚርን! ደላሎቹ ምን እንርዳችሁ ብለው በጉጉት ይጠይቁናል። የቤት ሰራተኛ ስንላቸው ፈገግራቸው የጠፋል። ሹፌር ወይንም የቀን ሰራተኛ ወዛደር ብንላቸው ይሻላቸው ነበር ብዙ አላቸው። ግን የቤት ሰራተኛ የላቸውም፤ ለነሱም ብርቅ ሆነዋል።
ብዙ የማቃቸው ቤተሰቦች አዲስ አበባም ከገጠር ከተሞችም የቤት ሰራተኞቻቸው በየ ሁለት ሶስት ወር ይለቃሉ አዲስ መቅጠር ይሆንባቸዋል። ወይንም ለመቅተር የገንዘብ አቅም የላቸውም። ወይንም ከመቀቃየር ተስፋ ቆርጠው አለ ሰራተኛ ይኖራሉ።
ዛሬ በአዲስ አበባም በመላው ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኛ ጠፍቷል። ወይንም በትክክለኛ አገላለጽ (እጅግ) ተወዷል። ለምን ይሆን? የ ኤኮኖሜ ምክንያቶች አሉ። የሰው ኃይል በጠቅላላው ተወዷል። ዛሬ የቀን የግንባታ ሰራተኛ በወር ወደ 3000 ብር ሊሰራ ይችላል። እንዲሁም የቤት ሰራተኛ ደሞዝ ጨምሯል። ሁለተኛ ምክንያት ዛሬ ሴት ልጆች ከድሮ ይልቅ በትምሕርታቸው ይገፋሉ። የገጠር ወይንም የድሃ ቤተሰብ ልጆቻችው እንዲማሩ ይፈልጋሉ እንጂ በልጅነታቸው ሰራተኛ እንዲሆኑ አይሰጧቸውም። ሶስተኛ ምክንያት ወደ አረብ ሀገር ሄዶ መስራት ነው። የአራብ ሀገር ክፍያ ይበልጣል ወደ «ውጭ» ሀገር መሄድም ምንም ችግር እንደሆነ መረጃ ቢኖርም ያጓጓል ይመስለኛል። በነዚህ ምክንያቶች የቤት ሰራተኞች ተወደዋልም አይገኙምም።
ከኤኮኖሚ ምክንያቶች በተጨማሪ ለቤት ሰራተኛ መጥፋት ማህበረሰባዊ ምክንያር አለ እና እዚህ ላይ ነው ማተኮር የምፈልገው። ዛሬ አንድ ሴት በህንጻ ጽዳት ስራ 2000 ብር በ ወር ታገኛለች። ከዚህ ብር የቤት ኪራይ፤ መጓጓዣ (ትራንስፖርት) እና የምግብ ወጪዎቿን ትከፍላለች። 1000 ከተረፋት ትልቅ ነገር ነው። ነይ በ2000 ብር የቤት ሰራተኛ ሁኚ የቤት ኪራይ፤ የመጓጓዣ እና የምግብ ወጪ አይኖርሽም ብንላት እምቢ ትላለች። ለምን ይሆን? ስራው ከባድ ስለሆነ አይደለም እትፍ ከባድ አይደለም። ነፃነቱ ይሆን እሱም 1000 ብር የሚያዋጣት አይመስለኝም። ምንም አይነት የሚመች የስራ ሁኔታዎች ብትዋዋልም የቤት ሰራተኛ መሆን አትፈልግም። ታድያ ምንድነው ምክንያቱ?
እኔ እንደሚመስለኝ ዋናው ምክንያት በባህላችን የቤት ሰራተኝነት እንደ ዝቅተኛ የሚናቅ ስራ ስለምንቆጥረው ነው። ይህን የዝቅተኝነት እና የመንናቅ ስሜት እጅግ ብዙ ብር ካልሆነ ብር አይተካውም። ተጎድቼ ውጭ ብሰራ ይሻለኛል ለብዙ ብር ከሰው ቤት ከምሰራ ነው ያለን አስተሳሰብ።
እስቲ ወደ ኋላ ሄደን የቤት ሰራተኞቻችንን እንዴት እንደምንይዝ እንደነበር እናስታውስ። 16 ሰዓት በቀን ይሰራሉ ለሌላው 8 ሰዓት ተጠሪ ናቸው። በወር አንድ ቀን እረፍት ቢኖራቸው ነው ይህም ላይከበር ይችላል። ኦርቶዶክስ ክርስትያን ነን የምንለው እንኳን እሁድ ቀን እረፍት መስጠት ቅዳሴም እንዲያስቀድሱ አንፈቅም (ከዚህ በላይ አሳዛኝ ነገር አላቅም)። እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ባርያ እንጮህባቸዋለን እናጎሳቁላቸዋለን። እንደማንም ሰው አድገው ወደፊት ማግባት እና ቤተሰብ ማፍራት እንደሚፈልጉም አንገነዘብም ልንገነዘብም አንፈልግም። ከቤተሰቦቻቸው ርቀው በመኖራቸው እኛ እንደ ሁለተኛ ቤተሰባቸው መሆን እንዳለብን አናስብም። በጠቅላላ ለራሳችን የማንወደውን እናደርግባችዋለን ለራሳችን የምንወደውን አናደርግላቸውም።
ይህ ስር የሰደደ ባህል ሆኖ የቤት ሰራተኛ እጅግ ዝቅተኛ ስራ መሆኑ ሁላችንም አሰሪዎችም ሰራተኞችም እናውቃለን። በዚህ ምክንያት ይመስለኛል በርካታ ሴቶች ከቤት ሰራተኛ ስራ የሚርቁት። ብዙ ብር ቢከፈላቸውም ከገንዘብ አንጻር ቢያዋጣቸውም «ዝቅተኛነቱን» «ውርደቱን» አይፈልጉትም።
የቶሎ የስራ መቀያየር ጉዳይሳ? ለምንድነው ብዙ የዘመኑ የቤት ሰራተኛዎች ገና ወር ሁለት ወር ሳይቆዩ ለቀው ወደ ሌላ ቤት የሚሄዱት። አንዱ ምክንያት የኤኮኖሚው ነው። ብዙ ስራ ስላለ የደሞዝ ጭማሬ ቶሎቶሎ ያገኛሉ። ሌላው ምክንያት ግን እንደሚመስለኝ የቤት ሰራተኝነት የማይፈለግ ስራ በመሆኑ ብዙ ችግር እና የማመዛዘን ድክመት ያላቸውን ሴቶች ናቸው ወደዚህ ስራ የሚገቡት። ይህ ምክንያት የስራ መቀያየራቸውን ብቻ ሳይሆን ሌሊችን ችግሮች እንደ ሌብነት ወዘተ ያስረዳል።
ለረዥም ዘመን የቤት ሰራተኞቻችንን ጎድተናል። በተዟዟሪ ሙሉ መሃበረሰባችንን ጎድተናል። የጎጂ የአሰሪ እና የንቀት ባህላችን ከትውልድ ወደትውልድ አስተላልፈናል። የአሁኑ የሰራተኛ እጥረት እስኩመጣ ድረስ ጥፋቶቻችን አልታዩንም ይሆናል ግን አሁን ጎልተው ሊታየን ይገባል። ጥፋታችንን አይተን አምነን መጸጸት፤ ንስሃ መግባት እና ይቅርታ መጠየቅ የሚኖርብን ይመስለኛል ይህን ጎጂ ባህላችንን በቋሚነት ለማስወገድ። ይህ ለህላችንም ለጠቅላላ ህብረተሰባችን ሰላም እና ፍቅርም አስፈላጊ ይመስለኛል።
Monday, 19 March 2018
ሊዩ ሺያዎቦ፤ የቻይና ህሊና
ሊዩ ሺያዎቦ (Liu Xiaobo) በቅርብ ከዚህ ዓለም የተለዩ የቻይና ምሁር የሰላምና ፍትህ ተቀናቃኝ የመንግስት ተቃዋሚ ነበሩ። ታሪካቸው ለሁላችንም ኢትዮጵያዊያን እጅግ አስተማሪ ነው። ይህ ጽሑፍ ጠቅለል አድርጎ የሊዩን የፖለቲካ ማንነትን በደምብ የሚገልጽ ይመስለኛል።
ከሊዩ ሺያዎቦ ግንዛቤዎች መካከል አንዱ አትኩረን ማየት ያለብን የሚመስለኝ ስለ ምዕራቡ ዓለምና ምዕራባዊነት የነበራቸው አመለካከት ነው። ሊዩ በመጀመርያ ምዕራባዊነትንና የምዕራብ አገሮችን አጉል ያደንቁ ነበር። የአገራቸውን የፖለቲካ ችግር ከምዕራብ አገሮች «ዴሞክራሲ» «ፍትህ» «ሰላም» እና ጠቅላላ «ስልጣኔ» ሲያነጻጽሩ የምዕራብ አገሮች ገነት የሆኑ ይመስላቸው ነበር።
ግን እንደ ታላቁ ሩሲያዊ አሌክሳንደር ሶልዠኒትሲን ሊዩ አሜሪካን ሲጎበኙ ይህ አመለካከታቸው የተሳሳተ እንደሆነ ተገነዘቡ። የአሜሪካን ችግር ሲያዩ የምዕራብ አገሮች ገነት አለመሆናቸው ብቻ ሳይሆን ግነት በምድር መኖር እንደማይቻልም ተገነዘቡ! ምዕራባዊነትንም እንደ ጣዖት ማየት አቆሙ። አገሬ ቻይና እንደ ምዕራብ አገሮች መሆን አለበት ብለው ማሰብ አቆሙ። የራስችንን ችግር በራሳችን መንገድ ማስተካከል አለበን ብለው አሰቡ።
የምዕራብ ስልጣኔን ፍፁም አድርጌ የማየው የነበረው ምክንያት በአገር ወዳድ ስሜቴ ምዕራቡን ዓለም ለቻይና ተሃድሶ አራአያ ትህናለች ብዬ ነው። ግን ይህ አመለካከቴ የምዕራብ ዓለሙን ግድፈቶችን እንዳላይ አድርጎኛል። የምዕራብ ስልጣኔን አጉል አመልክ ነበር መልካምነቱን አጋንኜ ነበር። የራሴን አስተሳሰብን ትክክልነትም አጋንኜ ነበር። ምዕራብ ዓለሙ ቻይናን የሚያድን ብቻ ሳይሆን የዓለም በሙሉ የሰው ልጅ የመጨረሻ ግብ ይመስለኝ ነበር። የዓለም አገሮች በሙሉ እያደጉ ሲሄዱ እንደ ምዕራብ አገሮች እየመሰሉ ይሄዳሉ ብዬ አስብ ነበር። በተጨማሪ ይህን ቅዠታማ አስተያየቴን ይዤ አገሬን አድናለው ቢየ አስብ ነበር።
አሁን ግን የገባኝ ይህ ነው፤ የምዕራብ ስልጣኔ ቻይና አሁን ባለችበት ሁኔታ ለማደስ ጥሩ ምሳሌዎች ይኖሩታል ግን ዓለምን የሰው ልጅን ሊያድን አይችልም።
የምዕራብ ስልጣኔን ራቅ ብለን ሰከን ብለን ከተመለከትነው የሰው ልጅ ቀጥንት እስካሁን ያሉትን ችግሮች አሉት።
ለ30 ዓመት በላይ በቻይና አምባገነናዊ ሥርዓት የኖርኩኝ ሆኜ ስለ የሰው ልጅ ማንነትና ዕጣ ማሰብ ከፈለግኩኝና እውነተኛ መሆን ከፈለግኩኝ ሁለት ትንተኖች ማድረግ ይኖርብኛል፤
1. የምዕራብ ስልጣኔን ቻይናን ለመተንተን መጠቀም አለብኝሊዩ ሺያዎቦ ከጻፉት መጸሐፎች የታወቀው «ጠላት የለኝም ጥላቻም የለኝም» ነው። ሊዩ ለቻይና መሪዎች የኮምዩኒስት ፓርቲ አባሎች እና ሌሎች ገዞች ጥላቻውን አስወገደ። የሃገሩ ሥርዓት ምክንያት እነሱ ብቻ ሳይሆኑ እያንዳንዱ ቻይናዊ ሃላፊነት እንዳለበት ተገንዝበው ሁላችንም መቀየር አለብን ንለው ያምኑ ነበር። ስሜትን የሚያስተስት ለፖለቲካ ምቹ ሃሳብ ባይሆንም ትክክለኛው እውነት የሆነ ሃሳብ ነው።
2. የራሴን የፈጠራ ሃሳቦችን የምዕራብ ዓለምን ለመተቸት መጠቀም አለብኝ
ለዚህ መሰለኝ ሌሎች ይበልጥ የሚጮሁ (የሚለፈልፉ) መንግስትን የሚተቹ የመንግስት ተቃዋሚዎች ሳይታሰሩ ሊዩ ሺያዎቦ እስኪሞቱ የታሰሩት። ሊዩ ሺያዎቦ እውነቱን ደረሱበት። መንስግትን ብቻ ሳይሆን ላለው ሥርዓት ህዝቡንም ሃላፊነት አለው አሉ። ህዝቡ ቢያዳምጣቸው ደግሞ የእውነት ለውጥ እንደሚመጣ መንግስት ያውቃል።
ሊዩ ሺያዎቦ የምዕራብ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለውጥ ለማምጣት አያስፈልጉንም አሉ። የራሳችን ማንነት ስነ መግባር ፍትህ ህሊና ይበቃናል። ሊዩ በየ ምዕራብ መገናኛ ብዙኃን እየዞረ ቃለ ምልልስ አይሰጥም ነበር። ሌሎች ይህን የሚያደርጉ ሳይታሰሩ ታሰረ። የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ምን እውነት እንደሆነና ምን አይነት አስተሳሰብ ከስልጣን እንደሚያወርዱ በደምብ ያውቃል። ስለዚህ ሰላማዊው ሊዩ ሺያዎቦ ታሰረና ሞተ። ታላቅ ምሳሌ ናቸው።
Monday, 5 March 2018
እውነት አማኞች
ስለ ታላቁ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ካህን አባ አርሴኒ በተጻፈው አንዱ መጸሃፍ አቭሴንኮቭ የሚባል ባለ ታሪክ አለ። አባ አርሴንይ ለሁለተኛ ጊዜ ጉላግ የሚባለው የሶቪዬት የሞት እስርቤት ገብተው እያለ የመንግስት ባለስልጣንና ዳኛ የነበረው የኮምዩኒስት ፓርቲ አባል አቭሰንኮቭ ታስሮ ወደሳቸው እሰር ቤት ይገባል። እንዴት እንደ አቭሴንኮቭ አይነቱ ከፍተኛ ባለ ስልጣን ታሰራ። ወቅቱ እንደ የኢትዮጵያ ቀይ ሽብር ነበር። የሰው ስልጣን ወይም ስራ ለመቀማት፤ ሰው በመጠቆም ሹመት ለማግኘት፤ የሚጠሉትን ሰው ለመጉዳት፤ ጥቅም ለማግኘት ወዘተ ምክንያቶች ፖለቲከኞችም ብዙሃንም እርሰ በርስ እየተጠቋቆሙ እስር ቤቶቹንና መቃብሮቹን እየሞሉ ነበር። በዚህ ሂደት በርካታ ባለ ስልጣኖችም ታስረዋል ተገድለዋልም። አቭሴንኮቭ አንዱ ከታሰሩት ነበር።
አቭሴንኮቭ ሶቪየቶች «እውነት አማኝ» ኮምዩኒስት ከሚሏቸው አንዱ ነበር። ይህ ማለት በኮምዩኒስም ርዕዮተ ዓለም፤ በፓርቲውና በአስተዳደሩ በእውነት ያምን ነበር። «ባለጥቅም» ከሚባሉት ለስልጣ፤ ለገንዘብ፤ ለሹመት፤ ለጥቅም፤ ሰው በማሰርና በማስጨረስ ብሶቱን ለመወጣት ወዘተ አልነበረም የኮምዩኒስት ፓርቲ አባልና ባለ ስልጣን የሆነው። በእውነት የኮምዩኒዝምን መሰረተ ሐሳቦች ያምን ነበር። ለዚ ለሚያምንበት ርዕዮተ ዓለም ለማሳሰር ለመፍረድና በሞት ፍርድ ለመፍረድ ዝግጁ ነበር።
ግን እንደ ማንኛውም ድርጅት ወይም ፖለቲካ ፓርቲ የኮምዩኒስት ፓርቲም በርካታ «እውነት አማኝ» ያልሆኑ አባላት በበረው። እነዚህ ቅድም እንደጠቀስኩት ለስልጣን፤ ለገንዘብ፤ ብሶት ለመወጣት፤ ጥቅም ለማግኘት ወዘተ ፓርቲ ውስጥ የገቡ ናቸው። አንዱ እንደዚህ አይነቱ የአቭሴንኮቭ የከፍተኛ ዳኛ ስልጣንን ለመቀማት ብሎ ቀስ ብሎ ሴራ ፈጥሮ አቭሴንኮቭን ከስሶ ወደ ጉላግ የሞት እሰርቤት እንዲላክ አደረገ።
አቭሴንኮቭ እስር ቤት እንደገበ መታሰሩን እንደ የአስተዳደር ስህተት ነበር የቆጠረው። በኮምዩኒዝምም በመንግስቱና አስተዳዳሪዎቹና መዋቅሮ እምነቱ እንዳለ ሆኖ በስህተት ነው የታሰርኩትና ከትንሽ ጊዜ በኋላ ስህተቱ ተደርሶበት እፋታለው ብሎ ይጠብቅ ነበር። በእውነት አማኞች ዘንድ ይህ የተለመደ አስተሳሰብ ነበር። የእምነታቸው ጥንካሬ የፓርቲውንና የመንግስቱን መሰረታው ሐሳቦች በጥያቄ ውስት ማድረግ እንዳይችሉ ያረጋቸው ነበር።
ግን አቭሴንኮቭ በእስር ቤቱ በቆየ ቁጥር መቀየር ጀመረ። እንደ አባ አርሴኒ አይነቱን በጸረ አብዮትነት የተሳሩትን ባልደረቦቹን ሲመለከት፤ ስነ መግባራቸው፤ እምነታቸው፤ ትህትናቸው፤ ፍቅራቸውን ሲመለከት ንፁሃን እንደሆኑ ቀስ በቀስ መረዳት ጀመረ። ከእስር ቤት አስተዳዳሪዎችና አዛጆቻቸው የሚመነጨው ክፋትን ሲአይ ደግሞ ያምንበት የነበረውን የፖለቲካ መዋቅሩን መጠራጠር ጀመረ። አቭሴንኮቭ ቀስ በቀስ የመንግስቱንና ርዕዮተ ዓለሙን ክፋት እየተረዳ ሄደ፤ ወደ አባ አርሴኒ አይነቱን እያየ ወደ ክርስትና መለወጥ ጀመረ። መጨረሻ ላይ የአባ አርሴኒ ንሰሀ ልጅ ሆኖ ነበር እድለኛ ሆኖ ከእስር ቤት ሳይሞት የወጣው።
ቅድም እንደጠቀስኩት ማንኛውም የፖለቲካ ሥርዓት ወስጥ እውህነት አማኞችና ባለጥቅሞች አሉ። ሁለቱም አይነቶች አሉ። ብዙዎቻችን እውነት አማኞችን እናከብራለን ባለጥቅሞችንን እንንቃለን። ግን እንደዚህ መሆን አለበትን? ማን ነው በርካታ ጉዳት ሊአይደርስ የሚችለው፤ እውነት አማኙ ወይም ባለ ጥቅሙ? ማን ነው ይበልጥ ክፉ መሆን የሚችለው?
አቭሴንኮቭ ረስቷቸው ነበር እንጂ እሱ ነበር አባ አርሴኒን ፈርዶባቸው ወደ ሞት እስር ቤት የላካቸው። የኮምዩኒዝምና የሶቪዬት ህዝብ ጠላት ናቸው ብሎ። ሌሎችም በርካታ ሰዎችን ወደ እስር ቤትና ሞት ሲልክ ለሚያመልከው ርዕዮተ ዓለም ስለሆነ ሰው መሆናቸው ረስቶ ልቡን ደንድኖ ድርጊቱን በቀላሉ አደረገው። እውነት አማኞች እጅግ አደገኛና ጎጂ ሊሆኑ ይችላሉ። የሚያምኑበት አካዬድ መጥፎ ከሆነ ይህን መጥፎነት በሙሉ እምነትና አቅማቸው ስለሚያራምዱ በርካታ ጉዳት ይፈጽማሉ። እውነት አማኝ በጥሩና ትክክለኛ ነገር ካመነ በጣም ጥሩ ውጤት ይኖረዋል። በመጥፎ ነገር ካመነ ደግሞ መጣም ከባድ ጉዳት ያደርሳል።
ባለጥቅሙ ግን ልቡ በሙሉ ስለማያምንበት የሚፈጽመው ጉዳት አናሳ ሊሆን ይችላል። ከጥሩም ከመጥፎም ወገን ቢሰለፍ ውጤቱ መካከለኛ ነው የሚሆነው። ክፉ ስርዓት ውስጥ ከተሳተፈ የሚያመጣው ጉዳት እንደ እውነት አማኙ ላይሆን ይችላል። ጥሩ ስርዓት ውስጥም ቢሳተፍ ወጤቱ እንደ እውነት አማኙ ያህል አይሆንም።
ስለዚህ እውነት አማኞችን ከባለጥቅሞች ይበልት ልናከበራቸው አይገባም። የአብዛኛው ጸንፈኛ የፖለቲካ ንቅናቄዎች መሰረት ጠንካራ የእውነት አማኝ ቡድን እንደሆነ መርሳት የለብንም። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ከተመለከትን የግራ ርዕዮተ ዓለም ትከታይ የሆነው የተማሪ ንቅናቄ የደረሰበት ደረጃና ያደረሰው ጉዳት አለ እውነት አማኞች አይሆንም ነበር። ላይ ያሉት መሪዎች መካከል በርካታ ባለጥቅሞች ቢኖሩም አለ ጠንካራ የእውነት አማኝ አምድ የትም አይደርሱም ነበር። እነ ህወሓትና ሻብያም የእውነት ዓማኝ አምዳቸው ነው እዚህ ያደረሳቸው አንዳይታደሱም የሚከለክላቸው።
ለኛ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳታፊዎች ይህ ታላቅ ትምህርት ሊሆነን ይገባል። «አምኖበት ነው ያእደረገው» «ለአቋሙ የቆመ ነው» «ፕሪንሲፕለድ ነው» «ለአገር ብሎ ነው ያደረገው» አይነቱን አባባሎቻችንን መተው አለበን። አንድ ሰው የሚያራምደው ርዕዮተ ዓለም ክፋት የሚጎትት ከሆነ እውነት ዓማኝ መሆኑ «ፕሪንሲፕልድ» መሆኑ ምን አይጠቅምም። ጭራሽ ጉዳት ነው። በደምብ ስለሚያምንበት ይበልጥ ጉዳት ያደርሳልና። ዋናው አላማችን በተሳሳተ ርዕዮተ ዓለም ወይም አቋም አለማመን። በተቻለ ቁጥር ማንኛውም ርዕዮተ ዓለም ወይም የፖለቲካ አመለካከት ከሰው በላይ አለማረግ። ዋናው ነገር ሰው ነው። ለሰው የሚያስፈልገው ፍቅርና ፍትህ ነው። ሌላው በሙሉ እነዚህን ማግኛ ዘዴ ነው። የምናምንበት ርዕዮተ ዓለም ጭራሽ ጥላቻና ጉዳት እያደረሰ ካየን የተሳሳተ መሆኑን ቶሎ ተረድተን መተው መቻል አለብን። ጣዖታችን ሊሆን አይገባም። ከኢግዚአብሔር በቀር ለምንም የእውነት አማኞች መሆን የለብንም።
አቭሴንኮቭ ሶቪየቶች «እውነት አማኝ» ኮምዩኒስት ከሚሏቸው አንዱ ነበር። ይህ ማለት በኮምዩኒስም ርዕዮተ ዓለም፤ በፓርቲውና በአስተዳደሩ በእውነት ያምን ነበር። «ባለጥቅም» ከሚባሉት ለስልጣ፤ ለገንዘብ፤ ለሹመት፤ ለጥቅም፤ ሰው በማሰርና በማስጨረስ ብሶቱን ለመወጣት ወዘተ አልነበረም የኮምዩኒስት ፓርቲ አባልና ባለ ስልጣን የሆነው። በእውነት የኮምዩኒዝምን መሰረተ ሐሳቦች ያምን ነበር። ለዚ ለሚያምንበት ርዕዮተ ዓለም ለማሳሰር ለመፍረድና በሞት ፍርድ ለመፍረድ ዝግጁ ነበር።
ግን እንደ ማንኛውም ድርጅት ወይም ፖለቲካ ፓርቲ የኮምዩኒስት ፓርቲም በርካታ «እውነት አማኝ» ያልሆኑ አባላት በበረው። እነዚህ ቅድም እንደጠቀስኩት ለስልጣን፤ ለገንዘብ፤ ብሶት ለመወጣት፤ ጥቅም ለማግኘት ወዘተ ፓርቲ ውስጥ የገቡ ናቸው። አንዱ እንደዚህ አይነቱ የአቭሴንኮቭ የከፍተኛ ዳኛ ስልጣንን ለመቀማት ብሎ ቀስ ብሎ ሴራ ፈጥሮ አቭሴንኮቭን ከስሶ ወደ ጉላግ የሞት እሰርቤት እንዲላክ አደረገ።
አቭሴንኮቭ እስር ቤት እንደገበ መታሰሩን እንደ የአስተዳደር ስህተት ነበር የቆጠረው። በኮምዩኒዝምም በመንግስቱና አስተዳዳሪዎቹና መዋቅሮ እምነቱ እንዳለ ሆኖ በስህተት ነው የታሰርኩትና ከትንሽ ጊዜ በኋላ ስህተቱ ተደርሶበት እፋታለው ብሎ ይጠብቅ ነበር። በእውነት አማኞች ዘንድ ይህ የተለመደ አስተሳሰብ ነበር። የእምነታቸው ጥንካሬ የፓርቲውንና የመንግስቱን መሰረታው ሐሳቦች በጥያቄ ውስት ማድረግ እንዳይችሉ ያረጋቸው ነበር።
ግን አቭሴንኮቭ በእስር ቤቱ በቆየ ቁጥር መቀየር ጀመረ። እንደ አባ አርሴኒ አይነቱን በጸረ አብዮትነት የተሳሩትን ባልደረቦቹን ሲመለከት፤ ስነ መግባራቸው፤ እምነታቸው፤ ትህትናቸው፤ ፍቅራቸውን ሲመለከት ንፁሃን እንደሆኑ ቀስ በቀስ መረዳት ጀመረ። ከእስር ቤት አስተዳዳሪዎችና አዛጆቻቸው የሚመነጨው ክፋትን ሲአይ ደግሞ ያምንበት የነበረውን የፖለቲካ መዋቅሩን መጠራጠር ጀመረ። አቭሴንኮቭ ቀስ በቀስ የመንግስቱንና ርዕዮተ ዓለሙን ክፋት እየተረዳ ሄደ፤ ወደ አባ አርሴኒ አይነቱን እያየ ወደ ክርስትና መለወጥ ጀመረ። መጨረሻ ላይ የአባ አርሴኒ ንሰሀ ልጅ ሆኖ ነበር እድለኛ ሆኖ ከእስር ቤት ሳይሞት የወጣው።
ቅድም እንደጠቀስኩት ማንኛውም የፖለቲካ ሥርዓት ወስጥ እውህነት አማኞችና ባለጥቅሞች አሉ። ሁለቱም አይነቶች አሉ። ብዙዎቻችን እውነት አማኞችን እናከብራለን ባለጥቅሞችንን እንንቃለን። ግን እንደዚህ መሆን አለበትን? ማን ነው በርካታ ጉዳት ሊአይደርስ የሚችለው፤ እውነት አማኙ ወይም ባለ ጥቅሙ? ማን ነው ይበልጥ ክፉ መሆን የሚችለው?
አቭሴንኮቭ ረስቷቸው ነበር እንጂ እሱ ነበር አባ አርሴኒን ፈርዶባቸው ወደ ሞት እስር ቤት የላካቸው። የኮምዩኒዝምና የሶቪዬት ህዝብ ጠላት ናቸው ብሎ። ሌሎችም በርካታ ሰዎችን ወደ እስር ቤትና ሞት ሲልክ ለሚያመልከው ርዕዮተ ዓለም ስለሆነ ሰው መሆናቸው ረስቶ ልቡን ደንድኖ ድርጊቱን በቀላሉ አደረገው። እውነት አማኞች እጅግ አደገኛና ጎጂ ሊሆኑ ይችላሉ። የሚያምኑበት አካዬድ መጥፎ ከሆነ ይህን መጥፎነት በሙሉ እምነትና አቅማቸው ስለሚያራምዱ በርካታ ጉዳት ይፈጽማሉ። እውነት አማኝ በጥሩና ትክክለኛ ነገር ካመነ በጣም ጥሩ ውጤት ይኖረዋል። በመጥፎ ነገር ካመነ ደግሞ መጣም ከባድ ጉዳት ያደርሳል።
ባለጥቅሙ ግን ልቡ በሙሉ ስለማያምንበት የሚፈጽመው ጉዳት አናሳ ሊሆን ይችላል። ከጥሩም ከመጥፎም ወገን ቢሰለፍ ውጤቱ መካከለኛ ነው የሚሆነው። ክፉ ስርዓት ውስጥ ከተሳተፈ የሚያመጣው ጉዳት እንደ እውነት አማኙ ላይሆን ይችላል። ጥሩ ስርዓት ውስጥም ቢሳተፍ ወጤቱ እንደ እውነት አማኙ ያህል አይሆንም።
ስለዚህ እውነት አማኞችን ከባለጥቅሞች ይበልት ልናከበራቸው አይገባም። የአብዛኛው ጸንፈኛ የፖለቲካ ንቅናቄዎች መሰረት ጠንካራ የእውነት አማኝ ቡድን እንደሆነ መርሳት የለብንም። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ከተመለከትን የግራ ርዕዮተ ዓለም ትከታይ የሆነው የተማሪ ንቅናቄ የደረሰበት ደረጃና ያደረሰው ጉዳት አለ እውነት አማኞች አይሆንም ነበር። ላይ ያሉት መሪዎች መካከል በርካታ ባለጥቅሞች ቢኖሩም አለ ጠንካራ የእውነት አማኝ አምድ የትም አይደርሱም ነበር። እነ ህወሓትና ሻብያም የእውነት ዓማኝ አምዳቸው ነው እዚህ ያደረሳቸው አንዳይታደሱም የሚከለክላቸው።
ለኛ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳታፊዎች ይህ ታላቅ ትምህርት ሊሆነን ይገባል። «አምኖበት ነው ያእደረገው» «ለአቋሙ የቆመ ነው» «ፕሪንሲፕለድ ነው» «ለአገር ብሎ ነው ያደረገው» አይነቱን አባባሎቻችንን መተው አለበን። አንድ ሰው የሚያራምደው ርዕዮተ ዓለም ክፋት የሚጎትት ከሆነ እውነት ዓማኝ መሆኑ «ፕሪንሲፕልድ» መሆኑ ምን አይጠቅምም። ጭራሽ ጉዳት ነው። በደምብ ስለሚያምንበት ይበልጥ ጉዳት ያደርሳልና። ዋናው አላማችን በተሳሳተ ርዕዮተ ዓለም ወይም አቋም አለማመን። በተቻለ ቁጥር ማንኛውም ርዕዮተ ዓለም ወይም የፖለቲካ አመለካከት ከሰው በላይ አለማረግ። ዋናው ነገር ሰው ነው። ለሰው የሚያስፈልገው ፍቅርና ፍትህ ነው። ሌላው በሙሉ እነዚህን ማግኛ ዘዴ ነው። የምናምንበት ርዕዮተ ዓለም ጭራሽ ጥላቻና ጉዳት እያደረሰ ካየን የተሳሳተ መሆኑን ቶሎ ተረድተን መተው መቻል አለብን። ጣዖታችን ሊሆን አይገባም። ከኢግዚአብሔር በቀር ለምንም የእውነት አማኞች መሆን የለብንም።
Thursday, 15 February 2018
ቤተ ክርስቲያን መቅደም አለባት!
ከትላንት ወድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ያልጠበቅናቸው መልካም አሳቢዎች እንደ ለማ መገርሳና አቢይ አህመድ ብቅ ማለት ጀመሩ። ትላንትና መንግስት ለረዥም ዓመታት የሚለመነውን ነገር አደረገ፤ ያለጥፋት የታሰሩትንና የተሰቃዩትን በርካታ እስረኞችን ፈታ። ዛሬ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስቴራችን ኃይለማርያም ደሳለኝ በፈቃደኝነታቸው ስልጣናቸውን ከቀቁ። መልካ ለውጦች ይታያሉ፤ እግዚአብሔር መጨረሻውን ያሳምርልን።
ግን ከፖለቲካው ቤተ ክርስቲያናችን መቅደም አልነበረበትም? (ይህን ስል እኔም እንደ አንድ ምእመናን እራሴን እየወቀስኩኝ ነው።) የኛ ለማ መገርሳዎች፤ በትህትና አለመፍረድ፤ በፍቅርና በምሳሌ፤ የሚናገሩት የት አሉ? እርግጥ አሉ፤ ግን በሌሎቻችን ተከበው ድምጻቸው በአግባቡ አይሰማም። እስረኞችንን መቼ ነው የምንፈታው? በርካታ እስረኞች አሉን፤ ፍቅር፤ ሃላፊነት፤ እርቅ፤ ትህትና፤ ሰላም። እነዚህንንሁሉ አስረን ቁጭ ብለናል። መቼ ነው የምንፈታቸው? ደግሞ መቼ ነው ሃላፊነት ወስደን እራሳችንን ህዝብ ፊት ዝቅ የምናደርገው። እንዲህ የሚያደርጉ አሉ ግን በኔ አይነቱ ተከበው አይታዩም። እንቅፋትም ሆነናቸዋል።
ቤተ ክርስቲያናችን እንደ አቡነ ጴጥሮስ መምራት መጀመር አለባት። በፖለቲካው መመራት ወይም መቀደም እፍረት ነው። አሁን ከቤተ ክርስቲያን እርቅ በፊት በሃገራችን ፖለቲካ እርቅ ቢመጣ ታላቅ እፍረት አይደለም? ከዛ በሗላ መጀመሪያውኑ ፖለቲካ ነው ያስቸገረን ብለን ልናሳብብ ነው? እነ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ ፖለቲካ እየተሰውዉ ደፍሮ ያላሉትን ልንል ነው?! ይህ ቢሆን እጅግ አሳሳዛኝ ነው።
ስለዚህ እንምራ! በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉት ስይኖዶስ መካከል ፈጥነን እርቅ እናምጣ። ለኢትዮጵያ ህዝብ ምሳሌ እንሁን። ፈተናው ብዙ ነው። ገና እየበዛ ይሄዳል። ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ በሁሉም ቦታ ከኛ ጋር ነው። ይህን ካመንን ለፍቅር እንድፈር፤ አንፍራ!
ግን ከፖለቲካው ቤተ ክርስቲያናችን መቅደም አልነበረበትም? (ይህን ስል እኔም እንደ አንድ ምእመናን እራሴን እየወቀስኩኝ ነው።) የኛ ለማ መገርሳዎች፤ በትህትና አለመፍረድ፤ በፍቅርና በምሳሌ፤ የሚናገሩት የት አሉ? እርግጥ አሉ፤ ግን በሌሎቻችን ተከበው ድምጻቸው በአግባቡ አይሰማም። እስረኞችንን መቼ ነው የምንፈታው? በርካታ እስረኞች አሉን፤ ፍቅር፤ ሃላፊነት፤ እርቅ፤ ትህትና፤ ሰላም። እነዚህንንሁሉ አስረን ቁጭ ብለናል። መቼ ነው የምንፈታቸው? ደግሞ መቼ ነው ሃላፊነት ወስደን እራሳችንን ህዝብ ፊት ዝቅ የምናደርገው። እንዲህ የሚያደርጉ አሉ ግን በኔ አይነቱ ተከበው አይታዩም። እንቅፋትም ሆነናቸዋል።
ቤተ ክርስቲያናችን እንደ አቡነ ጴጥሮስ መምራት መጀመር አለባት። በፖለቲካው መመራት ወይም መቀደም እፍረት ነው። አሁን ከቤተ ክርስቲያን እርቅ በፊት በሃገራችን ፖለቲካ እርቅ ቢመጣ ታላቅ እፍረት አይደለም? ከዛ በሗላ መጀመሪያውኑ ፖለቲካ ነው ያስቸገረን ብለን ልናሳብብ ነው? እነ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ ፖለቲካ እየተሰውዉ ደፍሮ ያላሉትን ልንል ነው?! ይህ ቢሆን እጅግ አሳሳዛኝ ነው።
ስለዚህ እንምራ! በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉት ስይኖዶስ መካከል ፈጥነን እርቅ እናምጣ። ለኢትዮጵያ ህዝብ ምሳሌ እንሁን። ፈተናው ብዙ ነው። ገና እየበዛ ይሄዳል። ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ በሁሉም ቦታ ከኛ ጋር ነው። ይህን ካመንን ለፍቅር እንድፈር፤ አንፍራ!
Subscribe to:
Posts (Atom)