ቀሲስ ጊኦርጊስ ካልቹ በቅርብ ጊዜ ያረፉ ታላቅ የሮማኒያ ኦርቶዶክስ ካህን ናቸው። ከዚህ ቪዲዮ የሳቸውን እና የሌሎች በሮማኒያ የቀድሞው ስረአት የተሰቃዩ ሰዎች ታሪክን ይናገራል…
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Friday, 25 January 2019
የሮማኒያው እስር ቤት…
ቀሲስ ጊኦርጊስ ካልቹ በቅርብ ጊዜ ያረፉ ታላቅ የሮማኒያ ኦርቶዶክስ ካህን ናቸው። ከዚህ ቪዲዮ የሳቸውን እና የሌሎች በሮማኒያ የቀድሞው ስረአት የተሰቃዩ ሰዎች ታሪክን ይናገራል…
Thursday, 24 January 2019
በረከት ስመዖን፤ የድክመታችን መለክያ
ሃብታሙ አያሌው እንዳለው ፍትህ መታየቱ ጥሩ ነው። ሆኖም ለበረከትም፤ ለቤተሰቦቹም፤ ለኢትዮጵያም አዝናለሁ።
እንደ ኢትዮጵያዊ አፍራለሁ። እንደ ሀገር እንደ በረከት፤ ታደሰ፤ አዲሱ፤ መለስ ወዘተ አይነት አስተሳሰብ ያላቸውን ሰዎችን ማፍራታችን ያሳፍራል። መቶ እጥፍ የሚያሳፍረው ግን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎችን መሪዎቻችን እንዲሆኑ መፍቀዳችን ነው።
ሌላ ላይ መፍረድ ቀላል ነው ግን ልክ አይደለም አዋጪም አይደለም። ሃላፊነት የወሰደ ብቻ ነው ህይወቱን በትክክል መምራት የሚችለው። እኛም እንደ ኢትዮጵያዊያን በነ በረከት መኖር እና ስልጣን መያዝ ሃላፊነት መውሰድ አለብን። በተለይም የፖለቲካ መደባችን ከጃንሆይ ዘመን ጀምሮ ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥፋቶችን አይተን፤ አምነን፤ ህፍረታችንን አምነን፤ ተቀብለን፤ ንስሃ መግባት አለብን።
ከበረከት ስመዖን መማር የሚገባኝ ይህ ነው ብዬ አምናለሁ።
እንደ ኢትዮጵያዊ አፍራለሁ። እንደ ሀገር እንደ በረከት፤ ታደሰ፤ አዲሱ፤ መለስ ወዘተ አይነት አስተሳሰብ ያላቸውን ሰዎችን ማፍራታችን ያሳፍራል። መቶ እጥፍ የሚያሳፍረው ግን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎችን መሪዎቻችን እንዲሆኑ መፍቀዳችን ነው።
ሌላ ላይ መፍረድ ቀላል ነው ግን ልክ አይደለም አዋጪም አይደለም። ሃላፊነት የወሰደ ብቻ ነው ህይወቱን በትክክል መምራት የሚችለው። እኛም እንደ ኢትዮጵያዊያን በነ በረከት መኖር እና ስልጣን መያዝ ሃላፊነት መውሰድ አለብን። በተለይም የፖለቲካ መደባችን ከጃንሆይ ዘመን ጀምሮ ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥፋቶችን አይተን፤ አምነን፤ ህፍረታችንን አምነን፤ ተቀብለን፤ ንስሃ መግባት አለብን።
ከበረከት ስመዖን መማር የሚገባኝ ይህ ነው ብዬ አምናለሁ።
Tuesday, 22 January 2019
ስለ የውጭ ሀገር «የበጎ አድራጎት ድርጅቶች» ማስታወሻ
የኤንጂኦዎችን ችግር የታወቀ ነው ግን ከፕሮፓጋንዳ እና ገንዘብ ውግያ አንጻር ችግራቸውን ደጋግሞ ማስታወስ ጥሩ ይመስለኛል። ይህን እንድታነቡ እጋብዛለሁ፤
https://www.theamericanconservative.com/articles/how-a-foreign-reporter-got-jaded-over-the-united-nations/
https://www.theamericanconservative.com/articles/how-a-foreign-reporter-got-jaded-over-the-united-nations/
Friday, 18 January 2019
Unraveling NAMA's "Intellectual Cover"
የአማራ ብሄርተኝነት በመሰረቱ የብሶት ፖለቲካ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_30.html) ነው። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) መሪዎችም ተከታዮችም በትርክታቸው የሚያተኩሩት ስለአማራ ላይ የደረሰው የ27/44 ዓመት በደል ነው። አማራ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ተለይቶ ተበድሏል ይላሉ። አልፎ ተርፎ ካሳም ይገባዋል ይላሉ። ከፖለቲካዊ ፕሮፓጋንዳዎቻቸው ምናልባት 80%ኡ ስለዚህ ስለ አማራው መጨቆን ነው። ይህ የአማራ ብሄርተኝነት በመሰረቱ በብሶት የሚመራ ንቅናቄ መሆኑን ያስረዳል።
ሆኖም እንደ ማንኛውም ፖለቲካ ንቅናቄ የአማራ ብሄርተኝነት ትርክት እና ፖለቲካዊ ጽንሰ ሃሳብ (theory) ያስፈልገዋል። ይህ intellectual cover (የምሁራን ሽፋን ልበለው?) የአብን ምሁራኖች በደምብ ሰርተውበታል። ዋናው የዚህ ሽፋን መልእክት እንዲህ ነው፤
«የአማራ ብሄርተኝነት የሚያስፈልገው የሌሎች (ያጠቁን) የጎሳ ብሄርተኝነቶችን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እንዳያመዝኑ ማድረግ ነው። የአማራ ብሄርተኝነት የሌሎች የጎሳ ብሄርተኝነቶችን balance በማድረግ የአማራንም የኢትዮጵያንም ህልውና ይጠብቃል።»
ማንኛውም ትንሽም ስለፖለቲካ/ታሪክ የሚያውቅ ሰው ይህ ትክርት እጅግ የተሳሳተ እንደሆነ ያውቃል። በርካታ ጎሳዎች ወይንም ክልሎች ባሉባቸው ሀገራት የስልጣን ውድድር በመሃል እና በክልሎቹ እንደሆነ የታወቀ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/on-nama-strategies.html)። ስልጣን ከምሃሉ (ኢትዮጵያዊነት) ወደ ልልሎች (ጎሳ ብሄርተኝነት) ቁጥር ሁሉም ጎሳ ብሄርተኞች ይጠነክራሉ። የጎሳ ብሄርተኞቹ ከእርስ በርስ ይልቅል የሚሟገቱት ከመሃሉ (ከኢትዮጵያዊነት) ነው። ዋናው አላማቸው መሃሉ ማድከም ነው። በዚህ ጋራ አላማቸው ይተባበራሉ። መሃሉ መንምኖ ሲያበቃው ስልጣን በሙሉ በጎሳ ብሄርተኞች እጅ ይሆናል። ከዛ እነዚህ የጎሳ ብሄርተኞች (ለምሳሌ ህወሓት፤ ኦነግ፤ አብን፤ ወዘተ)እርስ በርስ መደራደር አይችሉም። በጎሳ እና ብሶት የተመሰረቱ ስለሆነ የጋራ ማንነት እና ጥቅም ስለማይታያቸው የሚደራደሩት በባዶ ድምር (zero sum) አቋም ነው። ወጤቱ ጦርነት እና መለያየት ነው የሚሆነው። ሰለባው በየክልሉ የሚኖር አማራ፤ አማራ ክልል፤ መላው ኢትዮጵያዊ ነው የሚሆነው። መሃሉ ሲመነምን እና ጎሳ ብሄርተኞች ሲጠነክሩ ውጤቱ ይህ ነው።
እስቲ በዚህ ረገድ አንዳንድ የአብን አስተሳሰብ የውስጥ ተቃርኖዎች (inconsistencies) እንመልከት። በአንድ በኩል የጎሳ አስተዳደርን (ethnic nationalism) እንቃወማለን፤ የዜጋ ፖለቲካ ነው የሚያስፈልገው ያላሉ። በጎሳ የተደራጀነው ነባራዊው ሁኔታ አስገድዶን ነው እንጂ የጎሳ አስተዳደር ይቁም ይላሉ። የጎሳ አስተዳደር መኖር የለብትም ሲሉ ደግሞ ምክንያቱ አንድ ሀገር በጎሳ ሲስተዳደር ግጭቶች ይበዛሉ ነው። ኦሮሚያ የሚኖሩ አማሮች ይጠቃሉ፤ ነባር እና መጤ ግጭት። ጠረፍ ላይ ግጭት ይኖራል፤ የመሬት ግጭት። በሁሉም የፖለቲካም የማህበረሰብም መስክ ሰው ጎሳውን አስቀድሞ ኢ-ፍትሃዊነት ያራምዳል፤ የፍትህ ግጭት። ለዚህ ነው የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነው እና ይቅር የሚባለው። በሌላ አባባል ፖለቲካ በጎሳ ብሄርተኝነት ሲመራ ግጭት ይመጣል ነው። እንዲህ ከሆነ ኢንዴት ነው አብን እንደሚለው የአማራ፤ የኦሮሞ፤ የትግራይ ወዘተ ብሄርተኞች ኢትዮጵያዊነትን አፍርሶ እንደገና በድርድር መገንባት የሚችሉት! የጎሳ ብሄርተኞች መደራደር አይችሉም ተብሏል። አሁን ደግሞ መደራደር ይችላሉ። ሃሳቦቹ ይቃረናሉ።
አልፎ ተርፎ «የኢትዮጵያ የብሄር (ጎሳ) እስር ቤት ናት፤ ሰለዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጎሳው ይሰብሰብ እና እነዚህ የጎሳ ብሄርተኛ ስብስቦች አንዲስ ኢትዮጵያ ይመስርቱ» የሚለው ሃሳብ በ1950/60ዎቹ በማርክሲስት የተማሪ ንቅናቄው የተወለደ ነው። እስከ ዛሬም እነ ህወሓት፤ ኦነግ እና ሌሎች ጎሳ ብሄርተኞች ይህንን አቋም ነው የያዙት። በ1983 ህወሓት ስልጣን ሲይስዝም ይህን ነው አሰምሮ የተናገረው። «እንዳንተ «አንድነቶች» ኣናንተ «አማሮች»፤ እምዬ ኢትዮጵያ ከማለት በጎሳችሁ ተሰብሰቡ እና ተደራደሩ» እያሉ መሃይም ጥሩምባቸውን ይነፉ ነበር። ይህ ሃሳብ ወድቅ መሆኑ የገባን ደግሞ የጎሳ ብሄርተኞች ስብስብ ጦርነት እንጂ ሰላም አያመጣም ነበር። እንሆ ውጤቱን አየነው። ፖለቲካ በጎሳ ሲሆን ጸብ ብቻ ነው የሚኖረው። የጎሳ ፖለቲካ በተፈጥሮ የዜሮ ድምር አስተሳሰብን ይከተላልና።
ስለዚህ አብን ይህንን ታሪክ አውቆ እንዴት ነው ወደ ጎሳ ፖለቲካ እንመለስ የሚለው? አይገባኝም። እኔ እንደሚመስለኝ የሚገባ ብሶት እና ቅሬታቸውን የምሁራን ልብስ (intellectual cover) ለማልበስ ብለው የአብን ልሂቃን እራሳቸውን ወደ የማይሆን ትምዝምዝ ውስጥ አስገበተዋል። የአማራ ብሄርተኝነት በዚህ መልኩ ምንም አይነት ምሁራዊ ድጋፍ የለውም እና ሊፈጥሩ ለት አይችሉም። የብሶት የጎሳ ብሄርተኝነት ነው፤ ሌላ ነገር አንፍጠርለት። አንዴ ይህንን ካመንን በኋላ እንዴት ነው የህዝቡን ብሶት እና በደል በሚጠቅመው ሁኔታ ማስተናገድ የሚቻለውን የፖለቲካ ጥያቄን ለመመለስ እንስራ።
ሆኖም እንደ ማንኛውም ፖለቲካ ንቅናቄ የአማራ ብሄርተኝነት ትርክት እና ፖለቲካዊ ጽንሰ ሃሳብ (theory) ያስፈልገዋል። ይህ intellectual cover (የምሁራን ሽፋን ልበለው?) የአብን ምሁራኖች በደምብ ሰርተውበታል። ዋናው የዚህ ሽፋን መልእክት እንዲህ ነው፤
«የአማራ ብሄርተኝነት የሚያስፈልገው የሌሎች (ያጠቁን) የጎሳ ብሄርተኝነቶችን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እንዳያመዝኑ ማድረግ ነው። የአማራ ብሄርተኝነት የሌሎች የጎሳ ብሄርተኝነቶችን balance በማድረግ የአማራንም የኢትዮጵያንም ህልውና ይጠብቃል።»
ማንኛውም ትንሽም ስለፖለቲካ/ታሪክ የሚያውቅ ሰው ይህ ትክርት እጅግ የተሳሳተ እንደሆነ ያውቃል። በርካታ ጎሳዎች ወይንም ክልሎች ባሉባቸው ሀገራት የስልጣን ውድድር በመሃል እና በክልሎቹ እንደሆነ የታወቀ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/on-nama-strategies.html)። ስልጣን ከምሃሉ (ኢትዮጵያዊነት) ወደ ልልሎች (ጎሳ ብሄርተኝነት) ቁጥር ሁሉም ጎሳ ብሄርተኞች ይጠነክራሉ። የጎሳ ብሄርተኞቹ ከእርስ በርስ ይልቅል የሚሟገቱት ከመሃሉ (ከኢትዮጵያዊነት) ነው። ዋናው አላማቸው መሃሉ ማድከም ነው። በዚህ ጋራ አላማቸው ይተባበራሉ። መሃሉ መንምኖ ሲያበቃው ስልጣን በሙሉ በጎሳ ብሄርተኞች እጅ ይሆናል። ከዛ እነዚህ የጎሳ ብሄርተኞች (ለምሳሌ ህወሓት፤ ኦነግ፤ አብን፤ ወዘተ)እርስ በርስ መደራደር አይችሉም። በጎሳ እና ብሶት የተመሰረቱ ስለሆነ የጋራ ማንነት እና ጥቅም ስለማይታያቸው የሚደራደሩት በባዶ ድምር (zero sum) አቋም ነው። ወጤቱ ጦርነት እና መለያየት ነው የሚሆነው። ሰለባው በየክልሉ የሚኖር አማራ፤ አማራ ክልል፤ መላው ኢትዮጵያዊ ነው የሚሆነው። መሃሉ ሲመነምን እና ጎሳ ብሄርተኞች ሲጠነክሩ ውጤቱ ይህ ነው።
እስቲ በዚህ ረገድ አንዳንድ የአብን አስተሳሰብ የውስጥ ተቃርኖዎች (inconsistencies) እንመልከት። በአንድ በኩል የጎሳ አስተዳደርን (ethnic nationalism) እንቃወማለን፤ የዜጋ ፖለቲካ ነው የሚያስፈልገው ያላሉ። በጎሳ የተደራጀነው ነባራዊው ሁኔታ አስገድዶን ነው እንጂ የጎሳ አስተዳደር ይቁም ይላሉ። የጎሳ አስተዳደር መኖር የለብትም ሲሉ ደግሞ ምክንያቱ አንድ ሀገር በጎሳ ሲስተዳደር ግጭቶች ይበዛሉ ነው። ኦሮሚያ የሚኖሩ አማሮች ይጠቃሉ፤ ነባር እና መጤ ግጭት። ጠረፍ ላይ ግጭት ይኖራል፤ የመሬት ግጭት። በሁሉም የፖለቲካም የማህበረሰብም መስክ ሰው ጎሳውን አስቀድሞ ኢ-ፍትሃዊነት ያራምዳል፤ የፍትህ ግጭት። ለዚህ ነው የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነው እና ይቅር የሚባለው። በሌላ አባባል ፖለቲካ በጎሳ ብሄርተኝነት ሲመራ ግጭት ይመጣል ነው። እንዲህ ከሆነ ኢንዴት ነው አብን እንደሚለው የአማራ፤ የኦሮሞ፤ የትግራይ ወዘተ ብሄርተኞች ኢትዮጵያዊነትን አፍርሶ እንደገና በድርድር መገንባት የሚችሉት! የጎሳ ብሄርተኞች መደራደር አይችሉም ተብሏል። አሁን ደግሞ መደራደር ይችላሉ። ሃሳቦቹ ይቃረናሉ።
አልፎ ተርፎ «የኢትዮጵያ የብሄር (ጎሳ) እስር ቤት ናት፤ ሰለዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጎሳው ይሰብሰብ እና እነዚህ የጎሳ ብሄርተኛ ስብስቦች አንዲስ ኢትዮጵያ ይመስርቱ» የሚለው ሃሳብ በ1950/60ዎቹ በማርክሲስት የተማሪ ንቅናቄው የተወለደ ነው። እስከ ዛሬም እነ ህወሓት፤ ኦነግ እና ሌሎች ጎሳ ብሄርተኞች ይህንን አቋም ነው የያዙት። በ1983 ህወሓት ስልጣን ሲይስዝም ይህን ነው አሰምሮ የተናገረው። «እንዳንተ «አንድነቶች» ኣናንተ «አማሮች»፤ እምዬ ኢትዮጵያ ከማለት በጎሳችሁ ተሰብሰቡ እና ተደራደሩ» እያሉ መሃይም ጥሩምባቸውን ይነፉ ነበር። ይህ ሃሳብ ወድቅ መሆኑ የገባን ደግሞ የጎሳ ብሄርተኞች ስብስብ ጦርነት እንጂ ሰላም አያመጣም ነበር። እንሆ ውጤቱን አየነው። ፖለቲካ በጎሳ ሲሆን ጸብ ብቻ ነው የሚኖረው። የጎሳ ፖለቲካ በተፈጥሮ የዜሮ ድምር አስተሳሰብን ይከተላልና።
ስለዚህ አብን ይህንን ታሪክ አውቆ እንዴት ነው ወደ ጎሳ ፖለቲካ እንመለስ የሚለው? አይገባኝም። እኔ እንደሚመስለኝ የሚገባ ብሶት እና ቅሬታቸውን የምሁራን ልብስ (intellectual cover) ለማልበስ ብለው የአብን ልሂቃን እራሳቸውን ወደ የማይሆን ትምዝምዝ ውስጥ አስገበተዋል። የአማራ ብሄርተኝነት በዚህ መልኩ ምንም አይነት ምሁራዊ ድጋፍ የለውም እና ሊፈጥሩ ለት አይችሉም። የብሶት የጎሳ ብሄርተኝነት ነው፤ ሌላ ነገር አንፍጠርለት። አንዴ ይህንን ካመንን በኋላ እንዴት ነው የህዝቡን ብሶት እና በደል በሚጠቅመው ሁኔታ ማስተናገድ የሚቻለውን የፖለቲካ ጥያቄን ለመመለስ እንስራ።
Thursday, 17 January 2019
የጎሳ አስተዳደር አንድ እና አንድ ችግር ነው፤ የግጭት ምንጭ ነው
ፖለቲካ በሃሳብ ብቻ ነው ምሆነ ያለበት እንጂ በጎሳ መሆን የለበትም ሲባል ዋናው ምክንያቱን አጥብቀን ማስረዳት አለብን። ምክንያቱ የብሄር ፖለቲካዊ ጥያቄ ስለሌለ አይደለም፤ ጎሳዎች ስላልተጨቆኑ አይደለም፤ የርዕዮት ዓለም ጉዳይ አይደለም። መሰረታዊ ምክንያቱ፤
«ጎሳ ወደ በፖለቲካ ሲገባ የግጭት ምንጭ ይሆናል ነው»።
አሁን ደግሞ «ነፃነት» ባለበት የጠ/ሚ ዓቢይ ዘመን የጎሳ ግጭቶች እየቀጠሉ ነው። ይህ አስምሮ የሚያሳየው የጎሳ አስተዳደር ወይንም የጎሳ ፖለቲካ በነፃነት እና ዴሞክራሲያዊ አገዛዝም ግጭቶች የመጣል ነው።
ስለዚህ የጎሳ ፖለቲካ/አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነው። መብት ነው። ጥያቄዎችን ያስተናግዳል። ግን ግጭት እና ጦርነት ያመጣል።
አማራጩ ምንድነው። የጎሳ ጥያቄዎች በጎሳ አስተዳደር ሳይሆን በሌላ መልኩ ይመለሱ። ለምሳሌ «የአካባቢዬ ባህል አይናድ» ከሆነ በአካባቢ ፖለቲካዊ መብቶች ይመለስ። «ቋንቋዬ ይስፈን» ከሆነ በአካባቢ ፖለቲካ እና በብሄራዊ ዴሞክራሲ መንገድ ይመለስ። ወዘተ። የጎሳ ጥያቄዎች በዚህ መልኩ ሊመለሱ ይችላሉ። እንኳን እንደ ኦሮሞ አይነት የግዙፍ ጎሳ ጥያቄ የአናሳዎችም በዚህ መልኩ ይመለሳል።
Wednesday, 16 January 2019
የድሮ ስረአት ናፋቂ ነኝ!
የአብን አመራሮች ክርስቲያን ታደለ እና በለጠ ሞላ እራሳቸውን «ትምክሕተኞች» ነን ካሉ እኔም እውነቱን ለመናገር በአቅሚቲዬ «የድሮ ስረአት ናፋቂ» ነኝ ማለት የምችል ይመስለኛል። የኃይለ ሥላሴ መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ እድሜዬ ገና ሁለት ዓመት ቢሆንም ታሪክ በመስማት ስሜቴ ያንን ዘመን እንድናፍቀው አድርጎኛል።
ግን ዘመኑም አገዛዙም በርካታ ችግሮች ነበራቸው። የፍትህ እጦት፤ አድሎአዊነት፤ ወዘተ ነበረ። ሁላችንም እንደምናውቀው በርካታ ጪሰኞች እነሱ ወይንም አባት አያቶቻቸው ከመሬታቸው ተፈናቅለው በኢፍትሃዊ አሰራር ባላባቶችን ያገለግሉ ነበር። እንደዚህ አይነት ችግሮች እንደነበሩ እያወኩኝ እንዴት ያዘመን ይበልጥ ያስረአት ይናፍቀኛል።
ለቤተሰቦቼ ያዘመንን ጥሩ ነበር። ችግሩ እነሱን በቀጥታ አላጠቃም እና እነሱ በሰላም እና ብልጽግና ይኖሩ ነበር። ደርግ ሲመጣ ግን ችግር እየመጣ ጀመረ። የፖለቲካ ቀሱም ቤታችን ላይ ሊያንኳኳ ሆነ። በዚህ ምክንያት ደርግን ጠላሁ የጃንሆይ መንግስትን ናፈኩኝ። እንደ ማንኛውም ልጅ የራሴ ህይወት እና ልምድ (experience) አመለካከቴን ወሰነው።
መቼም አሁን ይህ አመለካከት የተሟላ እንዳልሆነ ይገባኛል። እኔ እና ቤተሰቦቼ ሰላም ስለነበራቸው ያዘመን እና ስረአት ጥሩ ነበር ማለት እንዳልሆነ ይገባኛል! ግን አሁንም ይናፍቀኛል። ለምን? ያኔ እኛ ኢትዮጵያዊያን የቆፈርነው ጉድጓድ ገና ብዙ ጥልቅ አልነበረም! ማለትም በርካታ ችግሮቻችንን በቀላሉ በአንዳንድ ትናንሽ ማስተካከያዎች ልናስወግድ እንችል ነበር። የኔ መሬት በሽ ነበር፤ ደን ነበር፤ ልሂቃኖቻችን ብዙ በማርክሲዝም አልተዋጡም ነበር፤ ጎሰኝነት አልሰፈነም ነበር። ተስፋ ቅርብ ነበር።
አሁን ግን ተጨማሪ ሌላ የ50 ዓመት የጉድጓድ ቁፈራ አካሄደናል። ጥልቅ የሆነ ጉድጓድ ውስጥ ነን። አሁንም ተግተን ሰርተን መውጣት እንችላለን ግን ስራው ከበፊቱ ይልቅ እጅግ ከባድ ነው። ብዙ በጣም የተመላሹ ነገሮች አሉ።
ስለዚህ አዎን የድሮ ስረአት ናፋቂ ነኝ። ግን የምናፍቀው ምክንያት ያኔ ችግሮች ቢኖሩም እንደ ዛሬ ያህል ለማስተካከል አይከብዱም ነበር ብዬ ስለማምን ነው። እንጂ የጃንሆይ ዘመን እና ስረአት ችግሮች አልነበረባቸውም ለማለት አይደለም!
ግን ዘመኑም አገዛዙም በርካታ ችግሮች ነበራቸው። የፍትህ እጦት፤ አድሎአዊነት፤ ወዘተ ነበረ። ሁላችንም እንደምናውቀው በርካታ ጪሰኞች እነሱ ወይንም አባት አያቶቻቸው ከመሬታቸው ተፈናቅለው በኢፍትሃዊ አሰራር ባላባቶችን ያገለግሉ ነበር። እንደዚህ አይነት ችግሮች እንደነበሩ እያወኩኝ እንዴት ያዘመን ይበልጥ ያስረአት ይናፍቀኛል።
ለቤተሰቦቼ ያዘመንን ጥሩ ነበር። ችግሩ እነሱን በቀጥታ አላጠቃም እና እነሱ በሰላም እና ብልጽግና ይኖሩ ነበር። ደርግ ሲመጣ ግን ችግር እየመጣ ጀመረ። የፖለቲካ ቀሱም ቤታችን ላይ ሊያንኳኳ ሆነ። በዚህ ምክንያት ደርግን ጠላሁ የጃንሆይ መንግስትን ናፈኩኝ። እንደ ማንኛውም ልጅ የራሴ ህይወት እና ልምድ (experience) አመለካከቴን ወሰነው።
መቼም አሁን ይህ አመለካከት የተሟላ እንዳልሆነ ይገባኛል። እኔ እና ቤተሰቦቼ ሰላም ስለነበራቸው ያዘመን እና ስረአት ጥሩ ነበር ማለት እንዳልሆነ ይገባኛል! ግን አሁንም ይናፍቀኛል። ለምን? ያኔ እኛ ኢትዮጵያዊያን የቆፈርነው ጉድጓድ ገና ብዙ ጥልቅ አልነበረም! ማለትም በርካታ ችግሮቻችንን በቀላሉ በአንዳንድ ትናንሽ ማስተካከያዎች ልናስወግድ እንችል ነበር። የኔ መሬት በሽ ነበር፤ ደን ነበር፤ ልሂቃኖቻችን ብዙ በማርክሲዝም አልተዋጡም ነበር፤ ጎሰኝነት አልሰፈነም ነበር። ተስፋ ቅርብ ነበር።
አሁን ግን ተጨማሪ ሌላ የ50 ዓመት የጉድጓድ ቁፈራ አካሄደናል። ጥልቅ የሆነ ጉድጓድ ውስጥ ነን። አሁንም ተግተን ሰርተን መውጣት እንችላለን ግን ስራው ከበፊቱ ይልቅ እጅግ ከባድ ነው። ብዙ በጣም የተመላሹ ነገሮች አሉ።
ስለዚህ አዎን የድሮ ስረአት ናፋቂ ነኝ። ግን የምናፍቀው ምክንያት ያኔ ችግሮች ቢኖሩም እንደ ዛሬ ያህል ለማስተካከል አይከብዱም ነበር ብዬ ስለማምን ነው። እንጂ የጃንሆይ ዘመን እና ስረአት ችግሮች አልነበረባቸውም ለማለት አይደለም!
Subscribe to:
Posts (Atom)