ለረዥም ዓመታት የኢህአዴግ መንግስት «ብዛት ቀጥሎ ጥራት» የሚለውን መፈክር ለመንግስት አገልግሎት በሙሉ ይጠቀም ነበር። በትምሕርት፤ ጤና፤ መሠረተ ልማት፤ ቴሌኮም፤ ውሃ፤ መብራት ወዘተ የመንግስት ቱክረት ለብዙሃኑ አገልግሎት በሰፊው ማቅረብ ነበር። እንደሚታወቀው «ብዛት» እና «ጥራት» ተፎካካሪ ናቸው፤ ብዛትን ለመጨመር ጥራትን መቀነስ ያስገድዳል ጥራትን ለመጨመር ብዛትን መቀነስ ያስገድዳል። የኢህአዴግ መንግስት ያደላው ወደ ብዛት፤ ወጪ መቀነስ አና ጥራት በመከነስ። ውጤቱ ብዛት እና አነስተኛ ጥራት ነው።
መንግስት ይህን የብዛት እና ጥራት ሚዛን ምን ይምሰል እና ወደ የትኛው እናዳላ ብሎ ሲገመግም ለግምገማው ብዙ ግብአቶች (መስፈርቶች) ታይተዋል ብዬ እገምታለሁ። ለምሳሌ 1) ህዝቡ ምንድነው የሚጎድለው፤ 2) ህዝቡ የተወሰነ አገልግሎት ነው ወይንም ዜሮ አገልግሎት ነው የሚያገኘው፤ 3) የሌሎች ሀገሮች ልምድ ምንድነው፤ 4) አቅማችን ምንድነው የሚፈቅደው፤ ዛሬውኑ ጥራት ማቅረብ እንችላለን ወይንስ አንችልም፤ 4) ለፖለቲካ የሚያዋጣን ምንድነው፤ 5) በጀታችን ምንድነው የሚፈቅደው፤ ወዘተ። እነዚህ የተለመዱ "textbook" ጥያቄዎች ናቸው።
ግን እንደሚመስለኝ አንዱ ያልተካተተ መስፈርት «ባህል» ነው። ባህል ስል ብዛት ላይ ስናተኩር እና ጥራት ለጊዜውም ቢሆን አያስፈልግም ስንል፤ ይህን ስንሰብክ እና እንደ ፖሊሲ ስናራምድ ምን አይነት የስራ እና ሌላ ባህል ነው ስራተኛው እና መላ ህዝቡ ላይ እያዳበርን ያለነው የሚለው ጥያቄ ነው። በስነ መግባር እና ግብረ ገብ በኩል ምን አይነት የባህል ጫናዎች ነው ይህ ፖሊሲ የሚያመጣው? ይህ ጉዳይ ምናልባትም ዋናው ቢሆንም የታየ አይመስለኝም።
እኔ እንደሚገባኝ ጥራትን ትቶ ብዛት ላይ ማተኮር ባለሞያዎቻችን ላይ የ«ችልተኝነት» ባህል እና ባህሪ እንዲያድርባቸው አድርጓል። በስራቸው ከመኩራት እና ለሞያቸው ክብር እንዳይኖራቸው አድርጓል። የስነ መግባር እጦትንም አስፋፍቷል። እነዚህ ጉዳቶች በሰው ስነ ልቦና እና አቅም (human capital) ዙርያ ስለሆኑ ከብዛት ለሚገኘው ቁሳዊ ጥቅም ይልቅ ጉዳቱ እጅግ ከባድ ነው።
እስቲ ይህ «ችልተኝነት» እና ስነ መግባር እጦት» እንዴት እንደሚከሰት ምሳሌ ላቅርብ። አንድ ሐኪም ብዙ ቀዶ ጥገና ለማድረግ አቋራጭ መንገዶች (short cut) ይጠቀማል። አንድ አንድ አስፈላጊ የሆኑ ጥንቃቄዎችንም አያደርግም። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ይህ ልምድ እና ባህል ይሆናል በሐኪሙ ዘንድ ብቻ ሳይሆን በሐኪም ቤቱ እና ባልደረቦቹ። ችልተኝነት ባህል ይሆንበታል። ለሐኪም ቤቱም የችልተኝነት እና የግድየለሽነት ባህል እንዲሰፍን ያደርጋል። ከዛ በኋላ አንድ ቀን ይህ ሐኪም ወደ ጥራት ያለው አሰራር ተቀየር ቢባል መቀየር ያስቸግረዋል። ልምድ እና ባህል ለመቀየር ረዥም ጊዜ ይፈጃል።
አልፎ ተርፎ ይህ የችልተኝነት እና በፍጥነት አለ ጥንቃቄ መስራት ባህሪ ሐኪሙ ተካሚውን እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ቁጥር እንዲመለከት ያደርገዋል። 100 ሰው ከማክም ዛሬ 150 ነው የማክመው ብሎ እራሱን ቢያዝናናም ውስጡ የሚያደርገው ነገር ትክክል አለመሆኑ ስለሚያውቅ ታካሚውን እንደ ሰው አለማየት ይሞክራል ("objectify" ያደርጋቸዋል)። ህሊናችን 100 ሰው ክምንጠቅም አንድ ሰው ባንገድል እንደሚሻል ስለሚነግረን ("do no harm" እንደሚባለው) ማለት ነው። ሐኪሙ ቀዶ ጥገና ላይ ተገቢው ጥንቃቄ ባለማድረግ ሰዎች ይጎዳሉ ወይንም ይሞታሉ። ሐኪሙ ይህ ጸጸት ህሊናውን ያስቸግረዋል።
«ብዛት ቀጥሎ ጥራት» የሚል ፖሊሲ ሲነደፍ ይህ ሁሉ መታሰብ ነበረበት። ግን አልታየም። ዛሬ የጠ/ሚ አብይ መንግስት ይህን መፈክር ትተነዋል እና ወደ ጥራት እንሄዳልን ብሏል። ጥሩ ውሳኔ ይመስለኛል። ይህ የፕሊሲ ለውጥ የሰው አቅምን (human capital) ከጊዚያዊ የቁስ ጥቅምን አብልጦ ያያል እና ትክክለኛ እና አዋጪ ነው። በዋናነት ሰውን ከራሱ ጋር ከህሊናው ጋር የሚያጣላ መርህውን ያስቆማል። ቀጥሎ ሰራተኛም አዛዥም በስራው እንዲኮራ እና የ«ሙያ ስነ መግባር» እንዲኖረው ያደርጋል። የአገልግሎት ተጠቃሚ ጉዳትን እንዲቀንስ ያደርጋል። ሙያተኛው በስራው እና በሙያው ሲኮራ፤ ህሊናው ንፁ ሲሆን፤ ለተስተናጋጁ ሲቆረቆር ወዘተ ስራው ጥሩ ይሆናል፤ እየተሻሻለ ይሄዳል እና ለኤኮኖሚው ዘለቀታ ያለው መሻሻል ያደርጋል።
ግን የተበላሸ ባህልን መቀየር እጅግ ከባድ ነው። ቁሳቁስ መስራት እና መገንባት ቀላል ነው። ግን የሰው ልጅን መጠገን እና ማጎልበት ከማድ ነው። በዚህ ምክንያት ወደ ፊት ፖሊሲዎች ሲዋከሩ በሰው አቅም እና ስነ ልቦና ያላቸው ጫናዎች በጥንቃቄ መታየት የሚኖሩባቸው ይመስለኛል።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ስነ መግባር. Show all posts
Showing posts with label ስነ መግባር. Show all posts
Monday, 10 September 2018
Friday, 7 September 2018
የግብረ ገብ እጦት በኢትዮጵያ
ባለፈው ጽሁፌ የቻይና የአምባገነናዊ ስረዓት የህዝቡ ግብረ ገብ እጦት ስልጣኑን ለመቀጠል እንደሚመቸው አስረድቼ ነበር (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_31.html)። ይህን ለማስረዳት በቅርብ ያረፉት የቻይና ፖለቲካ ተንታኝ ሊዩ ሺያኦቦ የጻፉትን ተርጉሜ አብራራሁኝ። እሳቸውም እንዲህ አሉ፡
«ህዝቡ የፖለቲካ ነፃነት ከመጠየቅ በርክሰት እንዲጨማለቅ ያረገዋል።»
በኢትዮጵያም እንዲሁ ነበር። የኢህአዴግ መንግስት በተለይ ላለፉት 13 ዓመት ከምርጫ 1997 በኋላ በ«ልማታዊ አስተዳደር» መፈክር ህዝቡን «ገንዘብ ስሩ አብታም ሁኑ ግን በፖለቲካ፤ ፍትህ፤ ሰላም አትምጡብኝ» ብሎ አዘዘ።
እኛ የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ ኤኮኖሚው ሲአድግ ገንዘብ ስናገኝ ፖለቲካ፤ ፍትህ እና ሰላም ምን ያደርጋል ሆዳችን እስከሞላ በገንዘባችን እስከንደላቀቅን አልን (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html)። ጎረቤታችን መሬቱ ለ«ልማት» ተብሎ ሲወሰድበት እንኳን ለመንግስት ታቃውሞ ማቅረብ ጎረቤታችንን በትንሽ ገንዘብ አልረዳነውም። ለመንግስት ተቃውሞ ብናሳይ ህልውናችን አሳሳቢ ይሆናል ግን ለጎረቤታችን ትንሽ ብር ብንሰጠው ምንም አንሆን። ግን ይህንንም አላደረግንም።
ገንዘብን ስናሳድድ ጉቦ ብንጠየቅ እንደምንም አድርገን ላለመክፈል ከመሞከር ይልቅ አይናችንን ሳናሽ እንከፋላለን። ከተቻለ ደግሞ ጉቦ ጠያቂም እንሆናለን! ለገንዘብ ወይንም ለንግዳችን ማጭበርበር ካስፈለገን እናጭበረብራለን። ከሰዎች አለአግባብ የተነጠቀ ሃብት ለመጠቀም እድል ካገኘን እንጠቀምበታለን። ሃብት ለማከማቸት ህሊናችን በምንም መንገድ አይከለክለንም።
ይህንን ሁሉ ስናደርግ የግብረ ገብ እጦት ወይንም የክፉ መንፈስ በውስጣችን እያደረ ይሄዳል። በገንዘብ ዙርያ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ነበር ህሊናችንን እናወድቀዋለን። በማህበራዊ ኑሮ፤ በቤተሰባዊ ኑሮ ወዘተ ወደ ርክሰት እንገባለን። ወደ ዝሙት እንገባለን። በዚህ ምክንያት መጠጥ ቤቶች አለ ቅት ይስፋፋሉ። ሴተኛ አዳሪዎች ይበዛሉ በየ መንገዱ በየ መሸታ ቤቱ በየ ሆቴሉ ይገኛሉ። ልጆቻችንን ለዚህ «ስራ» እናቀርባቸዋለን ገንዘብ እንዲሰሩልን። የልጆች የውሲብ ክስተት ይስፋፋል ዓለም ዙርይ በዚህ እየታወቅን እንሄዳለን። ወዘተ። ህሊናችን ይጣመማል ግብረ ገባችን ይጠፋል።
ለዚህ ሁሉ የሚያበቃን ሁለት ነገሮች አብሮ ሲመጡ ነው። እነዚህ ገንዘብ ውየንም ሃብት እና ሁለተኛው ሀፍረት ነው። ኤኮኖሚው እያደጋ በማጭበርበርም በመስራትም ገንዘብ እናገኛለን። ግን በርካታ ሰዎች ሲጎዱ እናያለን። ቤት እና መሬታቸው ለ«ልማት» ሲነጠቅ፤ ሲታሰሩ፤ በእስር ሲሰቃዩ፤ ከስራ ሲባረሩ፤ በተለያየ መንገድ በመንግስትና ከመንግስት ቅርበት ባላቸው ሲጭቆኑ ወዘተ እናያለን። የሰላም እና የፍትህ እጦትን በደምብ እናያለን። ግን በአንጻሩ ኑሮአችን ተመችቷል። ሃብት እያከማችን ነው። ሰው ማለት ባለ እንጀራዬ ይጎዳል ልረዳው ምንም አላደርግም። ግን እኔ «እየተመቸኝ» ይሄዳል።
ይህ በኛ ቁጭት፤ ጸጸት (guilt) እና ህፍረትን ያመጣል። ህሊናችን ይወጋናል። ሃብታችን ከግብረ ገብ እጦት ጋር አብሮ እንደመጣ እናውቀዋለን። ግን በትክክሉ ተጸጸተን ወደ ንስሐ ለመቀየር ይከብደናል። ይህን ከማድረግ ፋንታ ጸጸታችን እና ህፍረታችን ልባችንን እየቆረጠን እያለ ስለሆነ ወደ ማደንዘዣ እጽ እንሄዳለን። የቅንጦት ኑሮ፤ ዝሙት፤ ስለ ሃብት ብቻ ማሰብ ወዘተ እጽ ናቸው። ጎረቤተ ሲሰቃይ ዝም ብዬው ወደ መጠጥ ቤት የምሄደው ስለ እሱ እንዳላስብ እንዳላየው ነው።
አምባገናናዊ የ«ልማት አስተዳደር» ሰውን እንዲህ ነው የሚያደርገው። የደነዘዘ ገብረ ገብ የሌለው ማህበራዊ ኑሮ የሌለው እርስ በርስ የማይተሳሰብ ህዝብ ነው የሚፈጥረው። የሚፈጥረው ብቻ ሳይሆን የሚፈልገው። ህዝቡ እርስ በርስ ሲራራቅ፤ መተማመን ሳይኖር፤ ማህበራዊ ኑሮ ከሌለ፤ ብጨኝነት ከበዛ ወዘተ ለአምባገናናዊ ስረዓቱ ይጠቅመዋል። ህዝቡ በገንዘብ፤ ቅንጦት እና ዝሙት «እጽ» ሲባክን ስለ ሰላም፤ ፍቅር፤ ፍትህ እና የፖለቲካ ለውጥ አያስብም። አልፎ ተርሮ እራሱ በሚያደርገው ስለሚያፍር መንግስት ሲጨቁን ብዙ አይሰማውም! ዓለም በሙሉ ክፉ ሆኗል ብሎ እራሱን ያሰምናል።
በዚህ መንገዱ ነው አሁን በሃገራችን ላይ ያለው ልክ የለሽ የግብረ ገብ እጦት የመጣው። ለዚህም ነው «ልማት» ወይንም «ልማታዊ አስተዳደር» የሚለው መፈክር ከሀገራችን መጥፋት ያለበት (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_5.html)። የሀገር ህዝብ ማንነት ከሃብት ጋር በዋናነት ከተቆራኘ የግብረ ገብ እጦት መምጣቱ አይቀርም። ይህ ለሰው ልጅ ጤናማ አይደለምና።
አሁን የጠ/ሚ አብይ መንግስት ይሄንን ለመለወጥ እጅግ ከባድ ስራ ነው የሚሆንበት። ከተሳካም የዓመታት ከባድ ስራ ይጠይቃል። የቤተክርስቲያን እና የመስጊድ ታላቅ ስራ ያስፈልገዋል። ግን ዛሬ ባይመስልም አቶ ለማ መገርሳ እንዳሉት የሀገር ህልውና ጉዳይ ነው እና ጠንክረን ብንሰራበት ነው የሚበጀን።
«ህዝቡ የፖለቲካ ነፃነት ከመጠየቅ በርክሰት እንዲጨማለቅ ያረገዋል።»
በኢትዮጵያም እንዲሁ ነበር። የኢህአዴግ መንግስት በተለይ ላለፉት 13 ዓመት ከምርጫ 1997 በኋላ በ«ልማታዊ አስተዳደር» መፈክር ህዝቡን «ገንዘብ ስሩ አብታም ሁኑ ግን በፖለቲካ፤ ፍትህ፤ ሰላም አትምጡብኝ» ብሎ አዘዘ።
እኛ የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ ኤኮኖሚው ሲአድግ ገንዘብ ስናገኝ ፖለቲካ፤ ፍትህ እና ሰላም ምን ያደርጋል ሆዳችን እስከሞላ በገንዘባችን እስከንደላቀቅን አልን (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html)። ጎረቤታችን መሬቱ ለ«ልማት» ተብሎ ሲወሰድበት እንኳን ለመንግስት ታቃውሞ ማቅረብ ጎረቤታችንን በትንሽ ገንዘብ አልረዳነውም። ለመንግስት ተቃውሞ ብናሳይ ህልውናችን አሳሳቢ ይሆናል ግን ለጎረቤታችን ትንሽ ብር ብንሰጠው ምንም አንሆን። ግን ይህንንም አላደረግንም።
ገንዘብን ስናሳድድ ጉቦ ብንጠየቅ እንደምንም አድርገን ላለመክፈል ከመሞከር ይልቅ አይናችንን ሳናሽ እንከፋላለን። ከተቻለ ደግሞ ጉቦ ጠያቂም እንሆናለን! ለገንዘብ ወይንም ለንግዳችን ማጭበርበር ካስፈለገን እናጭበረብራለን። ከሰዎች አለአግባብ የተነጠቀ ሃብት ለመጠቀም እድል ካገኘን እንጠቀምበታለን። ሃብት ለማከማቸት ህሊናችን በምንም መንገድ አይከለክለንም።
ይህንን ሁሉ ስናደርግ የግብረ ገብ እጦት ወይንም የክፉ መንፈስ በውስጣችን እያደረ ይሄዳል። በገንዘብ ዙርያ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ነበር ህሊናችንን እናወድቀዋለን። በማህበራዊ ኑሮ፤ በቤተሰባዊ ኑሮ ወዘተ ወደ ርክሰት እንገባለን። ወደ ዝሙት እንገባለን። በዚህ ምክንያት መጠጥ ቤቶች አለ ቅት ይስፋፋሉ። ሴተኛ አዳሪዎች ይበዛሉ በየ መንገዱ በየ መሸታ ቤቱ በየ ሆቴሉ ይገኛሉ። ልጆቻችንን ለዚህ «ስራ» እናቀርባቸዋለን ገንዘብ እንዲሰሩልን። የልጆች የውሲብ ክስተት ይስፋፋል ዓለም ዙርይ በዚህ እየታወቅን እንሄዳለን። ወዘተ። ህሊናችን ይጣመማል ግብረ ገባችን ይጠፋል።
ለዚህ ሁሉ የሚያበቃን ሁለት ነገሮች አብሮ ሲመጡ ነው። እነዚህ ገንዘብ ውየንም ሃብት እና ሁለተኛው ሀፍረት ነው። ኤኮኖሚው እያደጋ በማጭበርበርም በመስራትም ገንዘብ እናገኛለን። ግን በርካታ ሰዎች ሲጎዱ እናያለን። ቤት እና መሬታቸው ለ«ልማት» ሲነጠቅ፤ ሲታሰሩ፤ በእስር ሲሰቃዩ፤ ከስራ ሲባረሩ፤ በተለያየ መንገድ በመንግስትና ከመንግስት ቅርበት ባላቸው ሲጭቆኑ ወዘተ እናያለን። የሰላም እና የፍትህ እጦትን በደምብ እናያለን። ግን በአንጻሩ ኑሮአችን ተመችቷል። ሃብት እያከማችን ነው። ሰው ማለት ባለ እንጀራዬ ይጎዳል ልረዳው ምንም አላደርግም። ግን እኔ «እየተመቸኝ» ይሄዳል።
ይህ በኛ ቁጭት፤ ጸጸት (guilt) እና ህፍረትን ያመጣል። ህሊናችን ይወጋናል። ሃብታችን ከግብረ ገብ እጦት ጋር አብሮ እንደመጣ እናውቀዋለን። ግን በትክክሉ ተጸጸተን ወደ ንስሐ ለመቀየር ይከብደናል። ይህን ከማድረግ ፋንታ ጸጸታችን እና ህፍረታችን ልባችንን እየቆረጠን እያለ ስለሆነ ወደ ማደንዘዣ እጽ እንሄዳለን። የቅንጦት ኑሮ፤ ዝሙት፤ ስለ ሃብት ብቻ ማሰብ ወዘተ እጽ ናቸው። ጎረቤተ ሲሰቃይ ዝም ብዬው ወደ መጠጥ ቤት የምሄደው ስለ እሱ እንዳላስብ እንዳላየው ነው።
አምባገናናዊ የ«ልማት አስተዳደር» ሰውን እንዲህ ነው የሚያደርገው። የደነዘዘ ገብረ ገብ የሌለው ማህበራዊ ኑሮ የሌለው እርስ በርስ የማይተሳሰብ ህዝብ ነው የሚፈጥረው። የሚፈጥረው ብቻ ሳይሆን የሚፈልገው። ህዝቡ እርስ በርስ ሲራራቅ፤ መተማመን ሳይኖር፤ ማህበራዊ ኑሮ ከሌለ፤ ብጨኝነት ከበዛ ወዘተ ለአምባገናናዊ ስረዓቱ ይጠቅመዋል። ህዝቡ በገንዘብ፤ ቅንጦት እና ዝሙት «እጽ» ሲባክን ስለ ሰላም፤ ፍቅር፤ ፍትህ እና የፖለቲካ ለውጥ አያስብም። አልፎ ተርሮ እራሱ በሚያደርገው ስለሚያፍር መንግስት ሲጨቁን ብዙ አይሰማውም! ዓለም በሙሉ ክፉ ሆኗል ብሎ እራሱን ያሰምናል።
በዚህ መንገዱ ነው አሁን በሃገራችን ላይ ያለው ልክ የለሽ የግብረ ገብ እጦት የመጣው። ለዚህም ነው «ልማት» ወይንም «ልማታዊ አስተዳደር» የሚለው መፈክር ከሀገራችን መጥፋት ያለበት (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_5.html)። የሀገር ህዝብ ማንነት ከሃብት ጋር በዋናነት ከተቆራኘ የግብረ ገብ እጦት መምጣቱ አይቀርም። ይህ ለሰው ልጅ ጤናማ አይደለምና።
አሁን የጠ/ሚ አብይ መንግስት ይሄንን ለመለወጥ እጅግ ከባድ ስራ ነው የሚሆንበት። ከተሳካም የዓመታት ከባድ ስራ ይጠይቃል። የቤተክርስቲያን እና የመስጊድ ታላቅ ስራ ያስፈልገዋል። ግን ዛሬ ባይመስልም አቶ ለማ መገርሳ እንዳሉት የሀገር ህልውና ጉዳይ ነው እና ጠንክረን ብንሰራበት ነው የሚበጀን።
Friday, 31 August 2018
የቻይና ገብረ ገብ እጦት፤ ትምሕርች ለኢትዮጵያ
የሰው ልጅ ከወደቀ ጀምሮ የግብረ ገብ ጉድለት እንዳለው ነው። በማህበረሰብ ደረጃ የግብረ ገብ እጦት ጎልቶ የሚታይበት ደግሞ ደበቅ የሚልበት ሁኔታዎች እና ወቅቶች አሉ።
ብዙዎቻችን በኢህአዴግ አገዛዝ ዘመን በሀገራችን ታልቅ የግብረ ገብ እጦት እየታየ ነው እንላለን። ለማ መገርሳም አብይ አህመድም ይህን ጉዳይ በተደጋጋሚ ያነሱታል። ባለ ስልጣን ይጨቁናል እና ይሰርቃል፤ የመንግስት ስራተኛ ጉቦ ይጠይቃል፤ ብዙሃኑ ያጭበረብራል፤ ስርቆት፤ ግድያ፤ ማጭበርበር፤ ለሰው ግድ ዬለሽነት፤ ዝሙት፤ ርክሰት፤ ሌብነት ወዘተ። ሁላችንም ሰምተነዋል አይተነዋልም።
መፍትሄውን ለማግኘት ለምን ይህ ሆነ ብለን መጠየቅ አለብን። ስንጠይቅ በቅርብ ያረፉት ታዋቂ የቻይና የፖለቲካ ተንታኝ እና እስረኛ ሊዩ ሺያዎቦ ጥሩ መልስ ይሰጡናል። የቻይና እና የኢትዮጵያ የፖለቲካ አገዛዝ እና በማሀበረሰቡ ላይ ያሳደረው ጫና በተወሰነ ደረጃ ተመሳሳይነት አላቸው።
በቻይና አንድ አውራ ፓርቲ በሙሉ ስልጣን ይገዛል። የማይፈልጋቸውን ያስራል ይገላል (በአመት ወደ 2,000 ሰዎች በይፋ በሞት ፍርድ ይገደላሉ)። ማንም ሰው መማር ማደግ ወይንም ስልጣን መያዝ ከፈለገ ከገዥ ፓርቲው ጋር ጥሩ ወይም ቢያንሽ መልካም ግንኙነት ሊኖረው ይገባል። ከፓርቲው ጋር ጥሩ ግንኙነት ያላቸው ከሌላው ሀብረተሰብ ሃብታም እና ባለ ስልጣን ይሆናሉ። ይህ ሃብት እና ስልጣን በስራ እና እውቀት የተገኘ ሳይሆን ከፓርቲ አባል እና መሪዎች ጋር በመሻረክ ነው የሚመጣው። በዚህ ምክንያት በርካታው የሀገሪቷ ሃብት በጥቂት ሰዎች የተቆጣጠረ ነው።
እንዲሁም ሆኖ የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ህዝቡ ከስልጣን በአመጽ እንዳያወርደው ብሎ ኤኮኖሚው የገበያ ኤኮኖሚ እንዲሆን እና በፍጥነት እንዲያድግ አድርጓል። ለብዙ ዓመት ኤኮኖሚው በየአመቱ ከ10% በላይ ነው እድገቱ። በርካታ ስዎች በፍጥነት ሃብታም ሆነዋል። መካከለኛ መደቡም አድጓል። ግን የእድገት ፍጥነቱ በሃብታም እና ድሃ ያለውን ልዩነት በጣም አስፍቶ ከዓለም አንደኛ አድርጎታል (30 ዓመት በፊት በእውነተኛ ኮምዩኒዝም ዘመን እኩልነቱ በዓለም አንደኛ ነበር)። ግን ብዙ ሰው ማደግ የሚችለው ሃብት ማከማቸት የሚችለው አጭበርብሮ፤ ጉቦ ከፍሎ ወይንም ወስዶ ወይንም በተለያየ መንገድ ህግን ጥሶ ወይን ስነ መግባርን ጥሶ ነው።
በአጭሩ የቻይና መንግስት ከህዝቡ ጋር ያለው ስምምነት እንዲህ ነው፤ በፖለቲካ እና ስልጣናችን አትምጡ ከመጣችሁ እናጠፋችኋለን፤ ግን እንደፈለጋችሁ ሃብታም ሁኑ ከፈለጋችሁ ከኛ ጋር ተሻረኩ እና ስረቁ። የቻይና «ልማታዊ መንግስት» እና «አውራ ፓርቲ» አገዛዝ ርዕዮእተ ዓለም እንዲህ ነው። በህወሓት ዘመን የነበረውን በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ የነበረውን አገዛዝ ሊያስታውሳችሁ ይገባል። አንድ ነው።
ወደ የቻይና የፖለቲካ ተንታኙ ሊዩ ሺያዎቦ እንመለስ። ሊዩ ይህንን ልማታዊ መንግስት ሲተቹ ይህ ስርአት የሚያመጣውን የስነ መግባር እጦትን በደምብ ተንትነዋል (https://www.nybooks.com/articles/2012/02/09/liu-xiaobo-he-told-truth-about-chinas-tyranny/)። ከዚህ ጽሁፍ የተወሰነውን ተርጉሜ ከታች አቀርባለሁ…
ኅብረተሰብን በመቀየር አገዛዙን እንቀይር» በሚል ጽሁፉ ሊዩ ሺያዎቦ ለቻይና ያሉትን ተስፋዎቹን ዘርዝሯል። የፖለቲካ አንባገነንነቱ ቢቀጥልም ህዝቡ ድንቁርናውን እና መከፋፈሉን ያሸንፋል። ህዝቡ ያለውን ኢፍትሃዊ አሰራር ለመታገል አስፈላጊ የሆነውን ህብረት ይረዳል እና መተባበርን ይጀምራል። ህዝቡ አይን ያወጣ ሙስናውን እና ሹማምንቱ የሚሰራውን አድሎአዊ ስራዎችን አብሮ በህብረት እንደሚቃውም ተረድቷል። ማህበራዊ ጥንካሬ እና ስለ ህዝብ መብት ማወቅ ይስፋፋል። ዜጎች የኢኮኖሚያዊ ነፃነት ሲያገኙ መረጃ ለማግኘት እና ለመቀያየር ይቀላቸዋል።
ህዝቡ በቀላሉ መንግስት መቆጣጠር በማይችልበት መንገድ ሃሳብ እንዲቀያየር ኢንተርነት ይፈቅዳል ያጎላብታል። የምነግስት የመረጃ አፈናን አቅመ-ቢስ እያደረገ ይሄዳል። የቻይና ህብረተሰብ ነፃ መሆን የሚችለው ህብረተሰቡ ከታች (ከብዙሃኑ) ወደ ላይ ቀስ በቀስ እየተሻሻለ ሲሄድ ነው። ይህ ቀስ በቀስ የህብረተሰብ ለውጥ አገዛዙን በግድ እንዲቀየር ያደርገዋል።
ሊዩ እነዚህን ተስፋዎች እየዘረዘርም በተቃራኒው የቻይና ህብረተሰብ የመንፈሳዊ ድኻነት በአሳዛኝ መልኩ ይገልጻል። መንግስት ህዝብ ታሪክን እንዲረሳ አውጆ ለማስረሳት ትልቅ ስራ እየሰራ ነው። የቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ (Tiananmen Massacre) ታሪክ ከአዲሱ ትውልድ አዕምሮ እንዲጠፋ ተደርጓል (ለኢትዮጵያ ተመሳሳዩ ክስተት ምርጫ 97 እና የተከተሉት ጭቆናዎች ናቸው)። የቻይና መንግስት ወጣቱ ይህን ትዝታ እንዲረሳ በጭፍን ብሄርተኝነት ይተከዋል ወጣቱ ያሉትን እውነታዊ ችግሮችን እንዲረሳ (በኢትዮጵያ context መንግስት ወጣቱን በ «ልማት» ፕሮፓጋንዳ ነው የሚሞላው) ነው። ሥን ጽሑፍ፤ መጽሔት፤ ፊልም እና ቪዲዮዎች ሁሉ በዝሙት እና ሁከት (violence) የተሞሉ ናቸው «የህብረተሰባችን የግብረ ገብ በርሃነትን» ያንጸባረቃል።
አንዳንድ የግራ ፖለቲካ አማኞች የዛሬ የቻይና የግብረ ገብ እና መንፈስ እጦትን በገበየ ኤኮኖሚው (market economy) እና ግሎባላይዛሽን (globalization) የመጣ ነው ብለው ያሳብባሉ። እነዚህም ናቸው የቻይናን ግዙፍ የሙስና ችግር ያመጡት ያላሉ። ግን ሊዩ በተቃራኒው የዛሬው ተስፋ መቁረጥ፤ ጥርጣሬ፤ እምነት ማጣት፤ ርክሰት፤ ብልግና እና ጥቅላላ የግብረ ገብ እጦትን በማኦ ዘመን ያሳብባል። የዛ የ«ንፁ» የኮምዩኒዝም ዘመን ነው የሀገሪቷን መንፈስ የዘረራት ይላል። ያ መንግስት፤
ብዙዎቻችን በኢህአዴግ አገዛዝ ዘመን በሀገራችን ታልቅ የግብረ ገብ እጦት እየታየ ነው እንላለን። ለማ መገርሳም አብይ አህመድም ይህን ጉዳይ በተደጋጋሚ ያነሱታል። ባለ ስልጣን ይጨቁናል እና ይሰርቃል፤ የመንግስት ስራተኛ ጉቦ ይጠይቃል፤ ብዙሃኑ ያጭበረብራል፤ ስርቆት፤ ግድያ፤ ማጭበርበር፤ ለሰው ግድ ዬለሽነት፤ ዝሙት፤ ርክሰት፤ ሌብነት ወዘተ። ሁላችንም ሰምተነዋል አይተነዋልም።
መፍትሄውን ለማግኘት ለምን ይህ ሆነ ብለን መጠየቅ አለብን። ስንጠይቅ በቅርብ ያረፉት ታዋቂ የቻይና የፖለቲካ ተንታኝ እና እስረኛ ሊዩ ሺያዎቦ ጥሩ መልስ ይሰጡናል። የቻይና እና የኢትዮጵያ የፖለቲካ አገዛዝ እና በማሀበረሰቡ ላይ ያሳደረው ጫና በተወሰነ ደረጃ ተመሳሳይነት አላቸው።
በቻይና አንድ አውራ ፓርቲ በሙሉ ስልጣን ይገዛል። የማይፈልጋቸውን ያስራል ይገላል (በአመት ወደ 2,000 ሰዎች በይፋ በሞት ፍርድ ይገደላሉ)። ማንም ሰው መማር ማደግ ወይንም ስልጣን መያዝ ከፈለገ ከገዥ ፓርቲው ጋር ጥሩ ወይም ቢያንሽ መልካም ግንኙነት ሊኖረው ይገባል። ከፓርቲው ጋር ጥሩ ግንኙነት ያላቸው ከሌላው ሀብረተሰብ ሃብታም እና ባለ ስልጣን ይሆናሉ። ይህ ሃብት እና ስልጣን በስራ እና እውቀት የተገኘ ሳይሆን ከፓርቲ አባል እና መሪዎች ጋር በመሻረክ ነው የሚመጣው። በዚህ ምክንያት በርካታው የሀገሪቷ ሃብት በጥቂት ሰዎች የተቆጣጠረ ነው።
እንዲሁም ሆኖ የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ህዝቡ ከስልጣን በአመጽ እንዳያወርደው ብሎ ኤኮኖሚው የገበያ ኤኮኖሚ እንዲሆን እና በፍጥነት እንዲያድግ አድርጓል። ለብዙ ዓመት ኤኮኖሚው በየአመቱ ከ10% በላይ ነው እድገቱ። በርካታ ስዎች በፍጥነት ሃብታም ሆነዋል። መካከለኛ መደቡም አድጓል። ግን የእድገት ፍጥነቱ በሃብታም እና ድሃ ያለውን ልዩነት በጣም አስፍቶ ከዓለም አንደኛ አድርጎታል (30 ዓመት በፊት በእውነተኛ ኮምዩኒዝም ዘመን እኩልነቱ በዓለም አንደኛ ነበር)። ግን ብዙ ሰው ማደግ የሚችለው ሃብት ማከማቸት የሚችለው አጭበርብሮ፤ ጉቦ ከፍሎ ወይንም ወስዶ ወይንም በተለያየ መንገድ ህግን ጥሶ ወይን ስነ መግባርን ጥሶ ነው።
በአጭሩ የቻይና መንግስት ከህዝቡ ጋር ያለው ስምምነት እንዲህ ነው፤ በፖለቲካ እና ስልጣናችን አትምጡ ከመጣችሁ እናጠፋችኋለን፤ ግን እንደፈለጋችሁ ሃብታም ሁኑ ከፈለጋችሁ ከኛ ጋር ተሻረኩ እና ስረቁ። የቻይና «ልማታዊ መንግስት» እና «አውራ ፓርቲ» አገዛዝ ርዕዮእተ ዓለም እንዲህ ነው። በህወሓት ዘመን የነበረውን በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ የነበረውን አገዛዝ ሊያስታውሳችሁ ይገባል። አንድ ነው።
ወደ የቻይና የፖለቲካ ተንታኙ ሊዩ ሺያዎቦ እንመለስ። ሊዩ ይህንን ልማታዊ መንግስት ሲተቹ ይህ ስርአት የሚያመጣውን የስነ መግባር እጦትን በደምብ ተንትነዋል (https://www.nybooks.com/articles/2012/02/09/liu-xiaobo-he-told-truth-about-chinas-tyranny/)። ከዚህ ጽሁፍ የተወሰነውን ተርጉሜ ከታች አቀርባለሁ…
ኅብረተሰብን በመቀየር አገዛዙን እንቀይር» በሚል ጽሁፉ ሊዩ ሺያዎቦ ለቻይና ያሉትን ተስፋዎቹን ዘርዝሯል። የፖለቲካ አንባገነንነቱ ቢቀጥልም ህዝቡ ድንቁርናውን እና መከፋፈሉን ያሸንፋል። ህዝቡ ያለውን ኢፍትሃዊ አሰራር ለመታገል አስፈላጊ የሆነውን ህብረት ይረዳል እና መተባበርን ይጀምራል። ህዝቡ አይን ያወጣ ሙስናውን እና ሹማምንቱ የሚሰራውን አድሎአዊ ስራዎችን አብሮ በህብረት እንደሚቃውም ተረድቷል። ማህበራዊ ጥንካሬ እና ስለ ህዝብ መብት ማወቅ ይስፋፋል። ዜጎች የኢኮኖሚያዊ ነፃነት ሲያገኙ መረጃ ለማግኘት እና ለመቀያየር ይቀላቸዋል።
ህዝቡ በቀላሉ መንግስት መቆጣጠር በማይችልበት መንገድ ሃሳብ እንዲቀያየር ኢንተርነት ይፈቅዳል ያጎላብታል። የምነግስት የመረጃ አፈናን አቅመ-ቢስ እያደረገ ይሄዳል። የቻይና ህብረተሰብ ነፃ መሆን የሚችለው ህብረተሰቡ ከታች (ከብዙሃኑ) ወደ ላይ ቀስ በቀስ እየተሻሻለ ሲሄድ ነው። ይህ ቀስ በቀስ የህብረተሰብ ለውጥ አገዛዙን በግድ እንዲቀየር ያደርገዋል።
ሊዩ እነዚህን ተስፋዎች እየዘረዘርም በተቃራኒው የቻይና ህብረተሰብ የመንፈሳዊ ድኻነት በአሳዛኝ መልኩ ይገልጻል። መንግስት ህዝብ ታሪክን እንዲረሳ አውጆ ለማስረሳት ትልቅ ስራ እየሰራ ነው። የቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ (Tiananmen Massacre) ታሪክ ከአዲሱ ትውልድ አዕምሮ እንዲጠፋ ተደርጓል (ለኢትዮጵያ ተመሳሳዩ ክስተት ምርጫ 97 እና የተከተሉት ጭቆናዎች ናቸው)። የቻይና መንግስት ወጣቱ ይህን ትዝታ እንዲረሳ በጭፍን ብሄርተኝነት ይተከዋል ወጣቱ ያሉትን እውነታዊ ችግሮችን እንዲረሳ (በኢትዮጵያ context መንግስት ወጣቱን በ «ልማት» ፕሮፓጋንዳ ነው የሚሞላው) ነው። ሥን ጽሑፍ፤ መጽሔት፤ ፊልም እና ቪዲዮዎች ሁሉ በዝሙት እና ሁከት (violence) የተሞሉ ናቸው «የህብረተሰባችን የግብረ ገብ በርሃነትን» ያንጸባረቃል።
«ቻይና የተስፋ መቁረጥ እና ጥርጣሬ ዘመን ውስጥ ገብታለች ማንም በምንም አያምንም… የኮምዩኒስት ፓሪቲ መሪዎቹም አባላቶቹም በራሳቸው ፓርቲ ፕሮፓጋንዳ ማመን ትተዋል። በመርህ፤ ስነ መግባር፤ እምነት መመራት ትተን አሁን በገንዘብ እና አለማዊ ነገር ሆናል «እምነታችን»። የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ልክ የለሽ የማያቋርጥ ፕሮፓጋንዳ ትዝታ እና ታሪክ የለለው ትውልዶች ፈጥሯል…አንዳንድ ምዕራባዊ ሊበራሎች የማኦ ጥብቅ ዘመን ሲፈርስ የዝሙት ነፃነት ይመጣ እና እንደ ቦምብ የህብረተሰባዊ እና ፖለቲካዊ ነፃነት ያመጣል ብለው ይገምቱ ነበር። አሁን ግን ሊዩ እንደሚለው የ«ዝሙት ፌሽታ» ሀገሪቷን አጥለቅልቆታል። ሀገሪቷን በዝሙት፤ ሁከት እና ስግብግብነት ሞልቶታል። ህብረተሰቡ በረዥም ዓመታት ጭቆና እና ውሸት ፕሮፓጋንዳ ምክንያት የግብረ ገቡን ማጣት ነው ይህ ሁሉ የሚያሳየው። «ድሮ ለፖለቲካዊ አብዮት ያበደው ዛሬ ለገንዘብ እና ዝሙት አብዷል» ይላል ሊዩ።
በደህና የኑሮ ሁነታ ያደገው ከ«ቲዬንአንሜን» ቀጥሎ የተወለደው ትውልድ አሁን እንደ አላማ ያለው የመንግስት ሹም መሆን (አስፋው፤ በጉቦ ሃብታም ለመሆን)፤ ሃብታም መሆን ወይንም ውጭ ሃገር መሄድ… ስለ ታሪካዊ ስቃዮች መስማት አይፈልጉም ትዕግስቱ የላቸውም… «ታላቁ እርምጃ» (ወደ 40 ሚሊዮን የሞቱበት ማኦ የፈጠረው ርሃብ "The Great Leap Forward")፤ «ባህላዊ አብዮት» (አንዱ የቻይና ቀይ ሽብር "Cultural Revolution")፤ የቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ። ለአዲሱ ትውልድ እነዚህን የመንግስት ጥፋቶች ማንሳት እና የህብረተሰባችን «ጭለማ ወገን» ማሳየት አስፈላጊ አይደለም። የራሳቸውን የሞልቃቃ አኗኗር እና የመንግስትን ፕሮፓጋንዳ ተጠቅመው ቻይና ታላቅ ተራምዳለች ማለት ይሻላቸዋል።»
አንዳንድ የግራ ፖለቲካ አማኞች የዛሬ የቻይና የግብረ ገብ እና መንፈስ እጦትን በገበየ ኤኮኖሚው (market economy) እና ግሎባላይዛሽን (globalization) የመጣ ነው ብለው ያሳብባሉ። እነዚህም ናቸው የቻይናን ግዙፍ የሙስና ችግር ያመጡት ያላሉ። ግን ሊዩ በተቃራኒው የዛሬው ተስፋ መቁረጥ፤ ጥርጣሬ፤ እምነት ማጣት፤ ርክሰት፤ ብልግና እና ጥቅላላ የግብረ ገብ እጦትን በማኦ ዘመን ያሳብባል። የዛ የ«ንፁ» የኮምዩኒዝም ዘመን ነው የሀገሪቷን መንፈስ የዘረራት ይላል። ያ መንግስት፤
«ኢ-ሰባዊ እና ገብረ ገብ የሌለው ነበር። የማኦ አምባገነናዊ መንግስት ሰዎችን መንፈሳቸውን እንዲሸጡ ሰውነታቸውን እንዲከዱ አድርጓል። ባለቤትን መጥላት፤ አባትን ማውገዝ፤ ጓደኛን መካድ፤ ተጎጂን ይበልጥ ምጉዳት፤ ጥሩ ኮምዩኒስት ለመባል ማንኛውም ነበር ማለት። ልክ እና ገደብ ያልነበረው አለማቆም ጨፍላቂ የሆነው የማኦ የፖለቲካ እርምጃዎች መሰረታዊ የሆኑትን የቻይና ህዝብ ስነ መግባሮችን አጠፋ።»ከማኦ በኋላ ይህ አካሄድ ቢቀንስም አለ። ከቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ በኋላ መንግስት ህዝቡ እንዲረሳው ጣላቅ ፕሮፓጋንዳ እና ሽብር አራመደ (አስፋው፤ ልክ እንደ ኢህአዴግ ከምርጫ 97 በኋላ እንዳረገው ሰውው ትዝታ እንዳይኖረው ስለ «ልማት» ብቻ እንዲያስብ)። ህዝቡ ህሊናውን ክዶ ለምንግስት ተገዢነቱን እንዲያሳይ ተገደደ። «ቻይና ህዝቧ ለህሊናው የሚዋሽ ሀገር ከሆነች በምን ተዓምር ነው ጤናማ ግብረ ገብ ያለው ህብረተሰብ መገንባት የሚቻለው?» ሊዩ ይቺን ምዕራፍ እንደዚህ ደመደመው፤
«ቻይናን ያረከሳት ዛሬ የምናየው በሀገሪቷ ዙርያ የሰፈነው የግብረ ገብ እጦት ምንጩ የማኦ ኢ-ሰባዊ ዘመን ነው። በዚህ ዘመን የዝሙት ማሳደድ ዘመቻ ለአምባገናናዊ ስረዓቱ እጅግ ይጠቅመዋል። ህዝቡ በልማት እየተጠቀመ ቢሆንም ወደ ፖለቲካ እንዳያስብ ያደርገዋል። የዝሙት «ነፃነት» ዴሞክራሲን ከማምጣት ይልቅ የድሮ የመሳፍንቶቻን የዝሙት ጥንቅን ነው የሚመልሰው… ይህ የዛሬዎቹን አምባገነኖችን በጣም ይመቻቸዋል። ከዘመናት ግብዝነት ያመጣውን ገብረ ገብ መበስበስ እና የፖለቲካ ጭቁና ጋር አብሮ ይሄዳል። ህዝቡ የፖለቲካ ነፃነት ከመጠየቅ በርክሰት እንዲጨማለቅ ያረገዋል።»በሌላ ጽሁፍ ይህ እንዴት ኢትዮጵያን እንዲሚመለከት እወያያለሁ።
Labels:
China,
Liu Xiaobo,
morality,
responsibility,
ሊዩ ሺያውቦ,
ሙስና,
ስነ መግባር,
ቻይና,
አምባገነንነት,
ወንጀል,
ዝሙት,
ጉቦ,
ግብረ ገብ,
ግድዬለሽነት
Friday, 3 August 2018
የበታችነት ስሜት
ሰላሳ አርባ ዓመታት በፊት ከሀገሩ የሚሰደድ ኢትዮጵያዊ ወደ ምዕራብ ሀገር ሲሄድ ከሀገሩ ይበልጥ «የሰለጠነ» እና «የበለጸገ» ሀገር አግኝቻለሁ ብሎ ያስቡ ነበር። የምዕራብ ሀገሮች በሀብት፤ በብልጽግና፤ በግብረ ገብነት፤ በቅልትፍና (efficiency)፤ በንፅህና ወዘተ ከኢትዮጵያ የላቁ መሆናቸው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ያምን ነበር።
ሆኖም ግን ስደተኛው ምዕራብ ሀገሮችን ቢያደንቅም የሚተችባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ለምሳሌ «ዘረኝነትን ያራምዳሉ» ይላል። በአዲስ ቅኝ ግዛት ታዳጊ ሀገራትን ያጠቃሉ ይዘርፋሉ። ኢትዮጵያ ለቅኝ ግዛት ስለማትመች እነ አሜሪካ ካዷት እና በደርግ አይነቱ አረመኔ መንግስት በማርክሲዝም እንድትገዛ አደረጉ። በተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ የሆኑ መንግስታትን ይገለብጣሉ። ወዘተ። ኢትዮጵያዊ ስደተኛው ልሂቃኑም የምዕራብ ሀገሮችን በዚህ መልኩ ይከሱ ነበር።
በርካታ ስደተኞች እንደዚህ በማለት የምዕራብ ሀገሮችን ተችተው ሀገራቸው ኢትዮጵያ ችግሮች ቢኖሯትም ከነዚህ ሀገሮች በማንነት ደረጃ አታንስም ብለው ያምኑ ነበር። በዚህ ምክንያት የሀገር የማንነት የበታችንነት ስሜት (inferiority complex) ገና ብዙ አላደረባቸውም። በኢትዮጵያዊነቱ ያለው ኩራት ብዙ አልተቦረቦረም ነበር።
ግን ጊዜው ባለፈ ቁጥር ኢትዮጵያ «አልሻሻል» ስትል ባንጻሩ የምዕራብ ሀገሮች በብልጽግና እይናሩ እና አንዳንድ ልውጦች ሲያደርጉ የፕሮፓጋንዳ ስልታቸውም እየዳበረ ሲሄድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛው በአሙሮው የምዕራቡን ዓለም እያበለጠ ሀገሩ ኢትዮጵያን እያሳነሰ ሄደ። ቀስ በቀስ የበታችነት ስሜት (inferiority complex) እያደረበት ሄደ። የህ የበታችነት ስሜት ወደ ሀገር ቤትም ገባ።
ወደ ምዕራብ ሀገር የተሰደደ ኢትዮጵያዊ ደህና ገቢ ማግኘት እና ሃብት ማከማቸት ቻለ። ስደተኛው ድሮ ቢገጥመውም ባይገጥመውም የሚያማርረው ዘረኝነቱ እየቀነሰ ሲሄድ አየ። ለነገሩ ዘረኝነቱ ድሮም ኑሮውን ከማሻሻል አልከለከለውም ነበር። አህን ግን ጭራሽ በጥቁርነቱ ስራ ከማጣት ማግኘት ጀመረ! ባሜሪካ ልጆቹ በጉብዝናቸው ብቻ ሳይሆን የጭቁን (ጥቅር) ዘር በመሆናቸው ስኮላርሺፕ ማግኘት ጀመሩ። የአሜሪካ ኑሮ ከድሮም ይበልጥ እየተመቸ ሄደ።
ይህ ስደተኛ ኑሮው «እየተሳካለት» በሄደ ቁጥር አሜሪካ በሱ አይን ይበልጥ እያማረች ሄደች። ፍትሐዊና መሐበራዊ ስነ ሥርዐቱን ከድሮም ይበልጥ ማደነቅ ጀመረ። ለሴቶች፤ ለልጆች፤ ለጥቁሮች ወዘተ ያለው «መብት» እና ጥንቃቄ ከኢትዮጵያ ጋር ሲያነጻጽረው ይገርመዋል። በፖለቲካ ደረጃ «ዴሞክራሲ» አምላኩ ሆነ «ሲኤንኤን» (CNN) መላዕክቱ ሆነ። በአንጻሩ ኢትዮጵያ በስደተኛው አይን እየቀነሰች እየወረደች ሄደች። አልሻሻል አለች እየባሰችም ሄደች። ስደተኛው ሀገሩን በጎበኛት ቁጥር ከአሜሪካ ጋር እያንጻጸረ ዘመዶቹን ያደነቁራል። በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ለማሳየት ያህል ዘመዱን ከ«ሀገር ቤት» ለመውጣት በርካታ አስር ሺዎች ዶላር ይከፍላል።
ዛሬ በኛ በኢትዮጵያውያን የዝቅተኘት መንፈስ በደምብ አድሮብናል ማለት ከእውነት የራቀ አይመስለኝም። ግን ይህ መንፈስ እውነትን ነው የሚያንጸባርቀው? እውነት ዝቅተኛ ህብረተሰብ ነን? ወይም ሀገራችን ዝቅተኛ ነው? ይበልጥ ታላቅ የሆነው ጥያቄ ሙሉ ሰው ለመሆን ወይንም በዘመኑ ቋንቋ «መሻሻል» ከፈለግን እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን ይኖርብናል? ምናልባት ዘፈናችን ጭፈራችን ምግባችንን ለትዝታ ብለን ጠብቀን በሌላው በሙሉ እንደነሱ እንደ ምዕራባዊያን መሆን ይኖርብን ይሆን?
እዚህ ላይ በቀለም ትምሕርት ከምንማረው በሚዲያ ከምንሰማው ፕሮፓጋንዳና ተራ «እውቀት» ወጥተን እናስብ። በአዲሱ ቅን ግዛት የተገዛውን አእምሮአችንን ነፃ እናውጣው የብዥታ መነጽራችንን እንጣል። በመጀመርያ እስቲ ምንድነው «ስልጣኔ» ብለን እንጀምር። ጥያቄውን በምሳሌ ኃይል ለመመርመር ታዋቂውን የሮሜን ስልጣኔን እንመልከት።
በክርስቶስ ዘመን በርካታ አይሁዶች ወደ ሀገራቸውን ወርሮ የገዛው ሮሜ ይፈልሱ ነበር። አንድ አይሁድ ወደ ሮሜ ሲሄደ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ከሀገሩ ወደ አሜሪካ እንደመሄድ እናመሳስለው። ሮሜ ሀብታም ነበረች። «ስደተኞችን» መጤዎችን ትቀበላለች ታስተናግዳለች ታበለጽጋለች። ውጣ ውረድ ቢኖረውም መጤዎች የሮሜ ዜጋ የመሆን እድል አላቸው። የሮሜ ዜግነት አንደ ይሁዳ ዜግነት በጎሳ በብሄር በደም የተወሰነ አይደለም ማንም የሮሜ ዜጋ መሆን ይችላል። የሮሜ ፍርድ ቤቶች በደምብ ይሰራሉ በተለይ ለሮሜ ዜጎች እውነተኛ ፍትሕ ይሰጣሉ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ችግር ባጋጠመው ቁጥር አይሁዶች ሲገሱት ሲሉ የሮሜ ዜግነቱን ተጠቅሞ ፍርድ ይጠይቃል! በሮሜ ፍርድ ቤት ትክክለኛ የፍርድ ሂደት እንደሚጠብቀው ስለሚያውቅ ነው። የሮሜ መንግስታዊ አስተዳደር ፍፁም ባይሆንም ከሌሎች አንጻር «የሰለጠነ» ነበር። «ዴሞክራሲ» አይነት ከነ ምክር ቤት አለው። በሮሜ የማሕበራዊ ብረ ገብ አለ። የሴቶች «መብቶች» ከሌሎች ሀገሮች ከይሁዳ ይልቅ የተከበሩ ናቸው። በስነ ሥርዓት በኩልም ሮሜ የስለጠነች ናት። መንገዶቿ ንፁ ናቸው። መንገደኛ ለመንገደኛ ጎረቤት ለጎረቤት አገልጋይ ለባለጉዳይ ያለው ግንኙነት በጥቅም የተሳሰረ ሰላማዊና የተቀላጠፈ (efficient) ነው። የድሮ «ሮሜ» ስልጣኔ እንደዚህ ይመስላል።
ለዚህም ነው አይሁዶችም ሌሎችም ወደ ሮሜ የሚፈልሱት ሃብቱን እና ስልጣኔውን ፈልገው። ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ወደ አሜሪካ እንደምንፈልሰው «ህይወትን ለማሻሻል» ወደ በአድ ሀገር ይሄዱ ነበር። ግን ሮሜ የይሁዳ ቅኝ ገዥ ነበረች! አይሁዶች ወደ የሚገዛቸው ሀገር ነበር የሚሄዱት። ወደ ዓለምን በሙሉ በጉልበቷ የተቆጣጠረቹ ሮሜ ነበር ለተሻለ ኑሮ ብለው የሚሄዱት። ግን አይሁዶቹንም ሌሎች መጤዎችንም የሮሜ ስልጣኔ ክፋነቷን እንዳያዩ አድርጓቸዋል አሳውራቸው። ለነሱ ሮሜ የብልጽግና ሀገር እንጂ የክፋት ሀገር አልነበረትም። ሮሜ ሀገራቸው ይሁዳ የሌላት ነገሮች ሁሉ አላት። በዚህ ምክንያት በራሳቸው ባህልና ማንነት ዝቅጠኝነት ተሰማቸው እንደ ሮሜዎች መሆነ ፈለጉ ወደ ሮሜ ህብረተሰብ ተቀላቀሉ።
ይህ ምሳሌ ስለ «ስልጣኔን» ምን ያስተምረናል? ለብዙዎቻችን ስልጣኔ ሀብት ማለት ነው። ሀብት ካለ ሌሎች ጉድለቶች አያታዩንም። ስልጣኔ «ቴክኖሎጂ» ይመስለናል። የሮሜ የከተማው ቧምቧ እና ፍሳሽ ስራ አይሁዶችን ይገርማቸው ነበር። ስልጣኔ ቅልጥፍና (efficiency) ይመስለናል። የሮሜ የመነግስት መዋቅሮች በተለይ ጦር ሰራዊቱ ግቡን በቀላሉ ያስፈጽም ነበር። ስልጣኔ ፍትሕ ነው። ስልጣኔ ግብረ ገብ እና ስነ መግባር ነው።
እነዚህን ሁሉ ስንመለከት ግን ባጭሩ ስልጣኔ ማለት ነግ በኔን በደምብ ማወቅ ነው። አካባቢዬን አላቆሽሽም ሌሎችን መንገደኞችን ውድጅያቸው ሳይሆን ንፁ አካባቢ ስለሚበጀኝ እኔ ካላቆሸሽኩኝ ሌሎችም ስለማያቆሽሹ ነው። እኔ መኪና የማሽከረክረው ሕግ አክብሬ ነው ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎችን ስለምወዳቸው ሳይሆን ሁላችንም በትክክል ካሽከረከርን ሁላችንም በፍጥነንት እና በሰላም የምንፈልግበት ቦታ ለመድረስ ስለሚያመችን ነው። መንግስቴ ለደሆች እርዳታ እንዲያደርግ እወዳለሁ ሰላምን ለመጠበቅ እኔም ነገ ብወድቅ እርዳታ እንዳገኝ። ወዘተ። ይህ ነው ስልጣኔ ባጭሩ። ሮሜም አሜሪካም የትም ህዝብ ሰላምና ሀብት እያገኘ ሲሄድ ለራሱ ለግል ምቾቱ የሚሆን አሰራሮች ስነ ምግባሮች እየገባው በተግባር መዋል ይጀምራል።
ግን ይህ ስልጣኔ ከጥሩነት፤ በጎነት፤ ሰላም ወዳድነት እና ከፍቅር ጋር አይገናኝም። ነግ በኔ በጎነትም ፍቅርም አይደለም። «የሰለጠነ» ራስ ወዳድነት ነው። ማንም ከጊዜ በሚያመጣው ልምድ በኋላ የሚደርስበት ነው። ማንም ደግሞ ችግሮች ሲያጋጥሙት ካልተመቸው የሚተወው ነው። ሮሜ ለራሷ የሰለጠነች ነበር ለሌሎች ሀገሮች ግን የክፋት መዓበል ነበረች። ዛሬ አሜሪካም አውሮፓም ሌሎችም ለራሳቸው የሰለጠኑ ናቸው ግን ከጠረፍ ውጭ አይደሉም።
ስለዚህ ይህ ሀገር የሰለጠነ ነው የኔ ሀገር አይደለም ብለን የበታችነት ስሜት ሊኖረን ይግባል? በፍፁም! ስልጣኔ ማንንነት አይደለም። ስልጣኔ ይመጣል ይሄዳል በዓለም ታሪክ በተለያዩ ቦታዎች ተገንብቷል ፈርሷል። ስልጣኔ ከፍቅርና በጎነት አይገናኝም። የሰው ማንነት ግን በጎነት፤ ፍቅር፤ ሰላም ወዘተ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ እነዚህን የሚሽህ እስከሆነ መቼም የበታችነት ሊሰማው አይገባም! ከፍቅር ይልቅ «ብልጭልጭን» ሲያመልክ ነው ችግሩ የሚመጣው።
ይህን ተክትሎ እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን አለብን ብሎ ማሰቡም ተገቢ አይደለም። ለምን ብትሉ የምዕራባዊያን ርዕዮት ዓለም ከኢትዮጵያዊነት ትውፊትና ማንነት 180 ዲግሪ የተቃረነ ነው። የምዕራባዊ አስተሳሰብ የሰው ልጅ የዓለም ቁንጮ አድርጎ ያስቀምጠዋል። እግዚአብሔር የለም ወይንም ምንም ሚና አይጫወትም ይላል። ኢትዮጵያዊ ግን በትውፊታችን ፈጣሪ ነው በአምሳሉ የፈጠረን ብለን እናምናለን ሁሉ ነገራችንም ከዛ ይከተላል። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ አህመድ የይቅርታ፤ ፍቅር እና ሰላም መልዕክቶችን በደስታ እና ጉጉት የምንቀበለው። እንደዚህ አይነቱ መልዕክት የተም ምዕራብ ሀገር እንደ ህፃንነት ነበር የሚታየው። ስለ ልማት፤ ነፃነት፤ መብት ነው የምዕራብ ሀገር ውይይት። እግዚአብሔር የለምና።
ታሪክ ረዥም ነው። 500 ዓመት በፊት ቻይና ከሁሉም «የሰለጠነች» ነበር። 60 ዓመት በፊት ቻይና ወደ 40 ሚሊዮን ህዝቦቿን ገደለች ግማሽ ሀገሪቷ በርሃብ እየተሰቃየ ነበር። 2000 ዓመት በፊት ስሜን አውሮፓ በሮሜዎች ዘንድ የያልሰለጠና የአረመኔ ስፍራ ነበር። ዛሬ ደግሞ ከዓለም በሙሉ የሰለጠው ጎራ ይባላል። 60 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ታላቅ ክብር ነበራት። ዛሬ እንደ ለማኝ ትታያለች። እኛ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ብናስታውስ ጥሩ ይመስለኛል።
እውነት ስልጣኔ ፍቅር እና ሰላም ነው። የኛ የኢትዮጵያዊያን በዚህ ረገድ ከማንም ልናንስም ልንበልጥም እንችላለን የኛ ፋንታ ነው። ግን የሰው ልጅ በመሆናችን ከማንም አናንስም አንበልጥምም። የዝቅተኛ ስሜታችንም በምንም መለክያ ተገቢ አይደለም። እጅግ ጎጂም ነው። ሌላውን ምዕራባዊያንም ለመገልበጥ መሻህ ዋጋ የለውም ጎጂ ነው። ማንነታች ከፈጣሪያችን የተሰጠን ነውና ምንም የምናፍርበት ሊሆን አይገባም። እርግጥም ለሌሎች ምሳሌ ሆነን መገኘት ነው ያለብን ድሮ ሆነን እናውቃለን አሁንም የማንሆንበት ምክንያት የለም።
ሆኖም ግን ስደተኛው ምዕራብ ሀገሮችን ቢያደንቅም የሚተችባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ለምሳሌ «ዘረኝነትን ያራምዳሉ» ይላል። በአዲስ ቅኝ ግዛት ታዳጊ ሀገራትን ያጠቃሉ ይዘርፋሉ። ኢትዮጵያ ለቅኝ ግዛት ስለማትመች እነ አሜሪካ ካዷት እና በደርግ አይነቱ አረመኔ መንግስት በማርክሲዝም እንድትገዛ አደረጉ። በተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ የሆኑ መንግስታትን ይገለብጣሉ። ወዘተ። ኢትዮጵያዊ ስደተኛው ልሂቃኑም የምዕራብ ሀገሮችን በዚህ መልኩ ይከሱ ነበር።
በርካታ ስደተኞች እንደዚህ በማለት የምዕራብ ሀገሮችን ተችተው ሀገራቸው ኢትዮጵያ ችግሮች ቢኖሯትም ከነዚህ ሀገሮች በማንነት ደረጃ አታንስም ብለው ያምኑ ነበር። በዚህ ምክንያት የሀገር የማንነት የበታችንነት ስሜት (inferiority complex) ገና ብዙ አላደረባቸውም። በኢትዮጵያዊነቱ ያለው ኩራት ብዙ አልተቦረቦረም ነበር።
ግን ጊዜው ባለፈ ቁጥር ኢትዮጵያ «አልሻሻል» ስትል ባንጻሩ የምዕራብ ሀገሮች በብልጽግና እይናሩ እና አንዳንድ ልውጦች ሲያደርጉ የፕሮፓጋንዳ ስልታቸውም እየዳበረ ሲሄድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛው በአሙሮው የምዕራቡን ዓለም እያበለጠ ሀገሩ ኢትዮጵያን እያሳነሰ ሄደ። ቀስ በቀስ የበታችነት ስሜት (inferiority complex) እያደረበት ሄደ። የህ የበታችነት ስሜት ወደ ሀገር ቤትም ገባ።
ወደ ምዕራብ ሀገር የተሰደደ ኢትዮጵያዊ ደህና ገቢ ማግኘት እና ሃብት ማከማቸት ቻለ። ስደተኛው ድሮ ቢገጥመውም ባይገጥመውም የሚያማርረው ዘረኝነቱ እየቀነሰ ሲሄድ አየ። ለነገሩ ዘረኝነቱ ድሮም ኑሮውን ከማሻሻል አልከለከለውም ነበር። አህን ግን ጭራሽ በጥቁርነቱ ስራ ከማጣት ማግኘት ጀመረ! ባሜሪካ ልጆቹ በጉብዝናቸው ብቻ ሳይሆን የጭቁን (ጥቅር) ዘር በመሆናቸው ስኮላርሺፕ ማግኘት ጀመሩ። የአሜሪካ ኑሮ ከድሮም ይበልጥ እየተመቸ ሄደ።
ይህ ስደተኛ ኑሮው «እየተሳካለት» በሄደ ቁጥር አሜሪካ በሱ አይን ይበልጥ እያማረች ሄደች። ፍትሐዊና መሐበራዊ ስነ ሥርዐቱን ከድሮም ይበልጥ ማደነቅ ጀመረ። ለሴቶች፤ ለልጆች፤ ለጥቁሮች ወዘተ ያለው «መብት» እና ጥንቃቄ ከኢትዮጵያ ጋር ሲያነጻጽረው ይገርመዋል። በፖለቲካ ደረጃ «ዴሞክራሲ» አምላኩ ሆነ «ሲኤንኤን» (CNN) መላዕክቱ ሆነ። በአንጻሩ ኢትዮጵያ በስደተኛው አይን እየቀነሰች እየወረደች ሄደች። አልሻሻል አለች እየባሰችም ሄደች። ስደተኛው ሀገሩን በጎበኛት ቁጥር ከአሜሪካ ጋር እያንጻጸረ ዘመዶቹን ያደነቁራል። በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ለማሳየት ያህል ዘመዱን ከ«ሀገር ቤት» ለመውጣት በርካታ አስር ሺዎች ዶላር ይከፍላል።
ዛሬ በኛ በኢትዮጵያውያን የዝቅተኘት መንፈስ በደምብ አድሮብናል ማለት ከእውነት የራቀ አይመስለኝም። ግን ይህ መንፈስ እውነትን ነው የሚያንጸባርቀው? እውነት ዝቅተኛ ህብረተሰብ ነን? ወይም ሀገራችን ዝቅተኛ ነው? ይበልጥ ታላቅ የሆነው ጥያቄ ሙሉ ሰው ለመሆን ወይንም በዘመኑ ቋንቋ «መሻሻል» ከፈለግን እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን ይኖርብናል? ምናልባት ዘፈናችን ጭፈራችን ምግባችንን ለትዝታ ብለን ጠብቀን በሌላው በሙሉ እንደነሱ እንደ ምዕራባዊያን መሆን ይኖርብን ይሆን?
እዚህ ላይ በቀለም ትምሕርት ከምንማረው በሚዲያ ከምንሰማው ፕሮፓጋንዳና ተራ «እውቀት» ወጥተን እናስብ። በአዲሱ ቅን ግዛት የተገዛውን አእምሮአችንን ነፃ እናውጣው የብዥታ መነጽራችንን እንጣል። በመጀመርያ እስቲ ምንድነው «ስልጣኔ» ብለን እንጀምር። ጥያቄውን በምሳሌ ኃይል ለመመርመር ታዋቂውን የሮሜን ስልጣኔን እንመልከት።
በክርስቶስ ዘመን በርካታ አይሁዶች ወደ ሀገራቸውን ወርሮ የገዛው ሮሜ ይፈልሱ ነበር። አንድ አይሁድ ወደ ሮሜ ሲሄደ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ከሀገሩ ወደ አሜሪካ እንደመሄድ እናመሳስለው። ሮሜ ሀብታም ነበረች። «ስደተኞችን» መጤዎችን ትቀበላለች ታስተናግዳለች ታበለጽጋለች። ውጣ ውረድ ቢኖረውም መጤዎች የሮሜ ዜጋ የመሆን እድል አላቸው። የሮሜ ዜግነት አንደ ይሁዳ ዜግነት በጎሳ በብሄር በደም የተወሰነ አይደለም ማንም የሮሜ ዜጋ መሆን ይችላል። የሮሜ ፍርድ ቤቶች በደምብ ይሰራሉ በተለይ ለሮሜ ዜጎች እውነተኛ ፍትሕ ይሰጣሉ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ችግር ባጋጠመው ቁጥር አይሁዶች ሲገሱት ሲሉ የሮሜ ዜግነቱን ተጠቅሞ ፍርድ ይጠይቃል! በሮሜ ፍርድ ቤት ትክክለኛ የፍርድ ሂደት እንደሚጠብቀው ስለሚያውቅ ነው። የሮሜ መንግስታዊ አስተዳደር ፍፁም ባይሆንም ከሌሎች አንጻር «የሰለጠነ» ነበር። «ዴሞክራሲ» አይነት ከነ ምክር ቤት አለው። በሮሜ የማሕበራዊ ብረ ገብ አለ። የሴቶች «መብቶች» ከሌሎች ሀገሮች ከይሁዳ ይልቅ የተከበሩ ናቸው። በስነ ሥርዓት በኩልም ሮሜ የስለጠነች ናት። መንገዶቿ ንፁ ናቸው። መንገደኛ ለመንገደኛ ጎረቤት ለጎረቤት አገልጋይ ለባለጉዳይ ያለው ግንኙነት በጥቅም የተሳሰረ ሰላማዊና የተቀላጠፈ (efficient) ነው። የድሮ «ሮሜ» ስልጣኔ እንደዚህ ይመስላል።
ለዚህም ነው አይሁዶችም ሌሎችም ወደ ሮሜ የሚፈልሱት ሃብቱን እና ስልጣኔውን ፈልገው። ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ወደ አሜሪካ እንደምንፈልሰው «ህይወትን ለማሻሻል» ወደ በአድ ሀገር ይሄዱ ነበር። ግን ሮሜ የይሁዳ ቅኝ ገዥ ነበረች! አይሁዶች ወደ የሚገዛቸው ሀገር ነበር የሚሄዱት። ወደ ዓለምን በሙሉ በጉልበቷ የተቆጣጠረቹ ሮሜ ነበር ለተሻለ ኑሮ ብለው የሚሄዱት። ግን አይሁዶቹንም ሌሎች መጤዎችንም የሮሜ ስልጣኔ ክፋነቷን እንዳያዩ አድርጓቸዋል አሳውራቸው። ለነሱ ሮሜ የብልጽግና ሀገር እንጂ የክፋት ሀገር አልነበረትም። ሮሜ ሀገራቸው ይሁዳ የሌላት ነገሮች ሁሉ አላት። በዚህ ምክንያት በራሳቸው ባህልና ማንነት ዝቅጠኝነት ተሰማቸው እንደ ሮሜዎች መሆነ ፈለጉ ወደ ሮሜ ህብረተሰብ ተቀላቀሉ።
ይህ ምሳሌ ስለ «ስልጣኔን» ምን ያስተምረናል? ለብዙዎቻችን ስልጣኔ ሀብት ማለት ነው። ሀብት ካለ ሌሎች ጉድለቶች አያታዩንም። ስልጣኔ «ቴክኖሎጂ» ይመስለናል። የሮሜ የከተማው ቧምቧ እና ፍሳሽ ስራ አይሁዶችን ይገርማቸው ነበር። ስልጣኔ ቅልጥፍና (efficiency) ይመስለናል። የሮሜ የመነግስት መዋቅሮች በተለይ ጦር ሰራዊቱ ግቡን በቀላሉ ያስፈጽም ነበር። ስልጣኔ ፍትሕ ነው። ስልጣኔ ግብረ ገብ እና ስነ መግባር ነው።
እነዚህን ሁሉ ስንመለከት ግን ባጭሩ ስልጣኔ ማለት ነግ በኔን በደምብ ማወቅ ነው። አካባቢዬን አላቆሽሽም ሌሎችን መንገደኞችን ውድጅያቸው ሳይሆን ንፁ አካባቢ ስለሚበጀኝ እኔ ካላቆሸሽኩኝ ሌሎችም ስለማያቆሽሹ ነው። እኔ መኪና የማሽከረክረው ሕግ አክብሬ ነው ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎችን ስለምወዳቸው ሳይሆን ሁላችንም በትክክል ካሽከረከርን ሁላችንም በፍጥነንት እና በሰላም የምንፈልግበት ቦታ ለመድረስ ስለሚያመችን ነው። መንግስቴ ለደሆች እርዳታ እንዲያደርግ እወዳለሁ ሰላምን ለመጠበቅ እኔም ነገ ብወድቅ እርዳታ እንዳገኝ። ወዘተ። ይህ ነው ስልጣኔ ባጭሩ። ሮሜም አሜሪካም የትም ህዝብ ሰላምና ሀብት እያገኘ ሲሄድ ለራሱ ለግል ምቾቱ የሚሆን አሰራሮች ስነ ምግባሮች እየገባው በተግባር መዋል ይጀምራል።
ግን ይህ ስልጣኔ ከጥሩነት፤ በጎነት፤ ሰላም ወዳድነት እና ከፍቅር ጋር አይገናኝም። ነግ በኔ በጎነትም ፍቅርም አይደለም። «የሰለጠነ» ራስ ወዳድነት ነው። ማንም ከጊዜ በሚያመጣው ልምድ በኋላ የሚደርስበት ነው። ማንም ደግሞ ችግሮች ሲያጋጥሙት ካልተመቸው የሚተወው ነው። ሮሜ ለራሷ የሰለጠነች ነበር ለሌሎች ሀገሮች ግን የክፋት መዓበል ነበረች። ዛሬ አሜሪካም አውሮፓም ሌሎችም ለራሳቸው የሰለጠኑ ናቸው ግን ከጠረፍ ውጭ አይደሉም።
ስለዚህ ይህ ሀገር የሰለጠነ ነው የኔ ሀገር አይደለም ብለን የበታችነት ስሜት ሊኖረን ይግባል? በፍፁም! ስልጣኔ ማንንነት አይደለም። ስልጣኔ ይመጣል ይሄዳል በዓለም ታሪክ በተለያዩ ቦታዎች ተገንብቷል ፈርሷል። ስልጣኔ ከፍቅርና በጎነት አይገናኝም። የሰው ማንነት ግን በጎነት፤ ፍቅር፤ ሰላም ወዘተ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ እነዚህን የሚሽህ እስከሆነ መቼም የበታችነት ሊሰማው አይገባም! ከፍቅር ይልቅ «ብልጭልጭን» ሲያመልክ ነው ችግሩ የሚመጣው።
ይህን ተክትሎ እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን አለብን ብሎ ማሰቡም ተገቢ አይደለም። ለምን ብትሉ የምዕራባዊያን ርዕዮት ዓለም ከኢትዮጵያዊነት ትውፊትና ማንነት 180 ዲግሪ የተቃረነ ነው። የምዕራባዊ አስተሳሰብ የሰው ልጅ የዓለም ቁንጮ አድርጎ ያስቀምጠዋል። እግዚአብሔር የለም ወይንም ምንም ሚና አይጫወትም ይላል። ኢትዮጵያዊ ግን በትውፊታችን ፈጣሪ ነው በአምሳሉ የፈጠረን ብለን እናምናለን ሁሉ ነገራችንም ከዛ ይከተላል። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ አህመድ የይቅርታ፤ ፍቅር እና ሰላም መልዕክቶችን በደስታ እና ጉጉት የምንቀበለው። እንደዚህ አይነቱ መልዕክት የተም ምዕራብ ሀገር እንደ ህፃንነት ነበር የሚታየው። ስለ ልማት፤ ነፃነት፤ መብት ነው የምዕራብ ሀገር ውይይት። እግዚአብሔር የለምና።
ታሪክ ረዥም ነው። 500 ዓመት በፊት ቻይና ከሁሉም «የሰለጠነች» ነበር። 60 ዓመት በፊት ቻይና ወደ 40 ሚሊዮን ህዝቦቿን ገደለች ግማሽ ሀገሪቷ በርሃብ እየተሰቃየ ነበር። 2000 ዓመት በፊት ስሜን አውሮፓ በሮሜዎች ዘንድ የያልሰለጠና የአረመኔ ስፍራ ነበር። ዛሬ ደግሞ ከዓለም በሙሉ የሰለጠው ጎራ ይባላል። 60 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ታላቅ ክብር ነበራት። ዛሬ እንደ ለማኝ ትታያለች። እኛ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ብናስታውስ ጥሩ ይመስለኛል።
እውነት ስልጣኔ ፍቅር እና ሰላም ነው። የኛ የኢትዮጵያዊያን በዚህ ረገድ ከማንም ልናንስም ልንበልጥም እንችላለን የኛ ፋንታ ነው። ግን የሰው ልጅ በመሆናችን ከማንም አናንስም አንበልጥምም። የዝቅተኛ ስሜታችንም በምንም መለክያ ተገቢ አይደለም። እጅግ ጎጂም ነው። ሌላውን ምዕራባዊያንም ለመገልበጥ መሻህ ዋጋ የለውም ጎጂ ነው። ማንነታች ከፈጣሪያችን የተሰጠን ነውና ምንም የምናፍርበት ሊሆን አይገባም። እርግጥም ለሌሎች ምሳሌ ሆነን መገኘት ነው ያለብን ድሮ ሆነን እናውቃለን አሁንም የማንሆንበት ምክንያት የለም።
Tuesday, 21 November 2017
ምርጥ ንግግር ከአቶ ለማ መገርሳ
ምርጥ ንግግር (https://www.youtube.com/watch?v=aim-D4EKMlI)።
1. በመጀመርያ በንግግሩ የጎሳ ብሄርተኝነትና የሱ መዘዞች አንዱ ዋና የኢትዮጵያ ችግር መሆኑን አምኗልም አስረድቷልም።
2. የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ወይም ርዕዮተ ዓለም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ለህልውናው አስፈላጊ መሆኑን አሳየ።
3. ህብረተሳባዊ ችግሮች እንደ ስረዓትና ስነ መግባር ማጣት እያመለጠን (runaway) እያለ የሆነ ችግር መሆኑን ተረድቷል። በዚህ ረገድ የህብረተሰብ - ወላጅና የሃይማኖት መዋቅሮች - በዋናነት ሃላፊነት እንዳለበትም መገነዘቡ ትልቅ ነገር ነው። በርካታ ዪትዮጵያ ምሁራኖች በዘመናዊነት ርዕዮተ ዓለም ተለቅፈው መንግስት ሁሉን አዋቂ ሁሉን ማድረግ የሚችል ይመስለዋል።
4. መልካም አስተዳደርም አለመኖሩ (በሌላ አባባል የሙስና ከሙስና ጋር የተገ መብዛት) ሌላው ዋና ችግር መሆኑ የብአዴን ስብሰባ ላይ መቶ መናገሩ ትልቅ ነገር ነው። ባአዴን ከህዝቡ ጋር ያለው ዋናው ችግር በዚህ ዙርያ ነው። እርግጥ የወልቃይትና ሌሎች ከሌልች ክልሎች የሚያገናኗቸው ቢኖሩም ዋናው የብአዴን ችግር መልካም አስተዳደር ነው። ወንድ ሆነው ይህን እንቅፋት ቢያሸንፉና ጭቆናና ሙስናን ቢያጠፋ ከህዝቡ ጋር አንድ ይሆናል ሀገራዊ ሃይሉም እጅግ ያይል ነበር።
እግዚአብሔር አቶ ለማ መገርሳን በዚው መንገድ እንዲቀጥል ዪርዳው።
1. በመጀመርያ በንግግሩ የጎሳ ብሄርተኝነትና የሱ መዘዞች አንዱ ዋና የኢትዮጵያ ችግር መሆኑን አምኗልም አስረድቷልም።
2. የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ወይም ርዕዮተ ዓለም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ለህልውናው አስፈላጊ መሆኑን አሳየ።
3. ህብረተሳባዊ ችግሮች እንደ ስረዓትና ስነ መግባር ማጣት እያመለጠን (runaway) እያለ የሆነ ችግር መሆኑን ተረድቷል። በዚህ ረገድ የህብረተሰብ - ወላጅና የሃይማኖት መዋቅሮች - በዋናነት ሃላፊነት እንዳለበትም መገነዘቡ ትልቅ ነገር ነው። በርካታ ዪትዮጵያ ምሁራኖች በዘመናዊነት ርዕዮተ ዓለም ተለቅፈው መንግስት ሁሉን አዋቂ ሁሉን ማድረግ የሚችል ይመስለዋል።
4. መልካም አስተዳደርም አለመኖሩ (በሌላ አባባል የሙስና ከሙስና ጋር የተገ መብዛት) ሌላው ዋና ችግር መሆኑ የብአዴን ስብሰባ ላይ መቶ መናገሩ ትልቅ ነገር ነው። ባአዴን ከህዝቡ ጋር ያለው ዋናው ችግር በዚህ ዙርያ ነው። እርግጥ የወልቃይትና ሌሎች ከሌልች ክልሎች የሚያገናኗቸው ቢኖሩም ዋናው የብአዴን ችግር መልካም አስተዳደር ነው። ወንድ ሆነው ይህን እንቅፋት ቢያሸንፉና ጭቆናና ሙስናን ቢያጠፋ ከህዝቡ ጋር አንድ ይሆናል ሀገራዊ ሃይሉም እጅግ ያይል ነበር።
እግዚአብሔር አቶ ለማ መገርሳን በዚው መንገድ እንዲቀጥል ዪርዳው።
Subscribe to:
Posts (Atom)