ስለ ታላቁ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ካህን አባ አርሴኒ በተጻፈው አንዱ መጸሃፍ አቭሴንኮቭ የሚባል ባለ ታሪክ አለ። አባ አርሴንይ ለሁለተኛ ጊዜ ጉላግ የሚባለው የሶቪዬት የሞት እስርቤት ገብተው እያለ የመንግስት ባለስልጣንና ዳኛ የነበረው የኮምዩኒስት ፓርቲ አባል አቭሰንኮቭ ታስሮ ወደሳቸው እሰር ቤት ይገባል። እንዴት እንደ አቭሴንኮቭ አይነቱ ከፍተኛ ባለ ስልጣን ታሰራ። ወቅቱ እንደ የኢትዮጵያ ቀይ ሽብር ነበር። የሰው ስልጣን ወይም ስራ ለመቀማት፤ ሰው በመጠቆም ሹመት ለማግኘት፤ የሚጠሉትን ሰው ለመጉዳት፤ ጥቅም ለማግኘት ወዘተ ምክንያቶች ፖለቲከኞችም ብዙሃንም እርሰ በርስ እየተጠቋቆሙ እስር ቤቶቹንና መቃብሮቹን እየሞሉ ነበር። በዚህ ሂደት በርካታ ባለ ስልጣኖችም ታስረዋል ተገድለዋልም። አቭሴንኮቭ አንዱ ከታሰሩት ነበር።
አቭሴንኮቭ ሶቪየቶች «እውነት አማኝ» ኮምዩኒስት ከሚሏቸው አንዱ ነበር። ይህ ማለት በኮምዩኒስም ርዕዮተ ዓለም፤ በፓርቲውና በአስተዳደሩ በእውነት ያምን ነበር። «ባለጥቅም» ከሚባሉት ለስልጣ፤ ለገንዘብ፤ ለሹመት፤ ለጥቅም፤ ሰው በማሰርና በማስጨረስ ብሶቱን ለመወጣት ወዘተ አልነበረም የኮምዩኒስት ፓርቲ አባልና ባለ ስልጣን የሆነው። በእውነት የኮምዩኒዝምን መሰረተ ሐሳቦች ያምን ነበር። ለዚ ለሚያምንበት ርዕዮተ ዓለም ለማሳሰር ለመፍረድና በሞት ፍርድ ለመፍረድ ዝግጁ ነበር።
ግን እንደ ማንኛውም ድርጅት ወይም ፖለቲካ ፓርቲ የኮምዩኒስት ፓርቲም በርካታ «እውነት አማኝ» ያልሆኑ አባላት በበረው። እነዚህ ቅድም እንደጠቀስኩት ለስልጣን፤ ለገንዘብ፤ ብሶት ለመወጣት፤ ጥቅም ለማግኘት ወዘተ ፓርቲ ውስጥ የገቡ ናቸው። አንዱ እንደዚህ አይነቱ የአቭሴንኮቭ የከፍተኛ ዳኛ ስልጣንን ለመቀማት ብሎ ቀስ ብሎ ሴራ ፈጥሮ አቭሴንኮቭን ከስሶ ወደ ጉላግ የሞት እሰርቤት እንዲላክ አደረገ።
አቭሴንኮቭ እስር ቤት እንደገበ መታሰሩን እንደ የአስተዳደር ስህተት ነበር የቆጠረው። በኮምዩኒዝምም በመንግስቱና አስተዳዳሪዎቹና መዋቅሮ እምነቱ እንዳለ ሆኖ በስህተት ነው የታሰርኩትና ከትንሽ ጊዜ በኋላ ስህተቱ ተደርሶበት እፋታለው ብሎ ይጠብቅ ነበር። በእውነት አማኞች ዘንድ ይህ የተለመደ አስተሳሰብ ነበር። የእምነታቸው ጥንካሬ የፓርቲውንና የመንግስቱን መሰረታው ሐሳቦች በጥያቄ ውስት ማድረግ እንዳይችሉ ያረጋቸው ነበር።
ግን አቭሴንኮቭ በእስር ቤቱ በቆየ ቁጥር መቀየር ጀመረ። እንደ አባ አርሴኒ አይነቱን በጸረ አብዮትነት የተሳሩትን ባልደረቦቹን ሲመለከት፤ ስነ መግባራቸው፤ እምነታቸው፤ ትህትናቸው፤ ፍቅራቸውን ሲመለከት ንፁሃን እንደሆኑ ቀስ በቀስ መረዳት ጀመረ። ከእስር ቤት አስተዳዳሪዎችና አዛጆቻቸው የሚመነጨው ክፋትን ሲአይ ደግሞ ያምንበት የነበረውን የፖለቲካ መዋቅሩን መጠራጠር ጀመረ። አቭሴንኮቭ ቀስ በቀስ የመንግስቱንና ርዕዮተ ዓለሙን ክፋት እየተረዳ ሄደ፤ ወደ አባ አርሴኒ አይነቱን እያየ ወደ ክርስትና መለወጥ ጀመረ። መጨረሻ ላይ የአባ አርሴኒ ንሰሀ ልጅ ሆኖ ነበር እድለኛ ሆኖ ከእስር ቤት ሳይሞት የወጣው።
ቅድም እንደጠቀስኩት ማንኛውም የፖለቲካ ሥርዓት ወስጥ እውህነት አማኞችና ባለጥቅሞች አሉ። ሁለቱም አይነቶች አሉ። ብዙዎቻችን እውነት አማኞችን እናከብራለን ባለጥቅሞችንን እንንቃለን። ግን እንደዚህ መሆን አለበትን? ማን ነው በርካታ ጉዳት ሊአይደርስ የሚችለው፤ እውነት አማኙ ወይም ባለ ጥቅሙ? ማን ነው ይበልጥ ክፉ መሆን የሚችለው?
አቭሴንኮቭ ረስቷቸው ነበር እንጂ እሱ ነበር አባ አርሴኒን ፈርዶባቸው ወደ ሞት እስር ቤት የላካቸው። የኮምዩኒዝምና የሶቪዬት ህዝብ ጠላት ናቸው ብሎ። ሌሎችም በርካታ ሰዎችን ወደ እስር ቤትና ሞት ሲልክ ለሚያመልከው ርዕዮተ ዓለም ስለሆነ ሰው መሆናቸው ረስቶ ልቡን ደንድኖ ድርጊቱን በቀላሉ አደረገው። እውነት አማኞች እጅግ አደገኛና ጎጂ ሊሆኑ ይችላሉ። የሚያምኑበት አካዬድ መጥፎ ከሆነ ይህን መጥፎነት በሙሉ እምነትና አቅማቸው ስለሚያራምዱ በርካታ ጉዳት ይፈጽማሉ። እውነት አማኝ በጥሩና ትክክለኛ ነገር ካመነ በጣም ጥሩ ውጤት ይኖረዋል። በመጥፎ ነገር ካመነ ደግሞ መጣም ከባድ ጉዳት ያደርሳል።
ባለጥቅሙ ግን ልቡ በሙሉ ስለማያምንበት የሚፈጽመው ጉዳት አናሳ ሊሆን ይችላል። ከጥሩም ከመጥፎም ወገን ቢሰለፍ ውጤቱ መካከለኛ ነው የሚሆነው። ክፉ ስርዓት ውስጥ ከተሳተፈ የሚያመጣው ጉዳት እንደ እውነት አማኙ ላይሆን ይችላል። ጥሩ ስርዓት ውስጥም ቢሳተፍ ወጤቱ እንደ እውነት አማኙ ያህል አይሆንም።
ስለዚህ እውነት አማኞችን ከባለጥቅሞች ይበልት ልናከበራቸው አይገባም። የአብዛኛው ጸንፈኛ የፖለቲካ ንቅናቄዎች መሰረት ጠንካራ የእውነት አማኝ ቡድን እንደሆነ መርሳት የለብንም። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ከተመለከትን የግራ ርዕዮተ ዓለም ትከታይ የሆነው የተማሪ ንቅናቄ የደረሰበት ደረጃና ያደረሰው ጉዳት አለ እውነት አማኞች አይሆንም ነበር። ላይ ያሉት መሪዎች መካከል በርካታ ባለጥቅሞች ቢኖሩም አለ ጠንካራ የእውነት አማኝ አምድ የትም አይደርሱም ነበር። እነ ህወሓትና ሻብያም የእውነት ዓማኝ አምዳቸው ነው እዚህ ያደረሳቸው አንዳይታደሱም የሚከለክላቸው።
ለኛ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳታፊዎች ይህ ታላቅ ትምህርት ሊሆነን ይገባል። «አምኖበት ነው ያእደረገው» «ለአቋሙ የቆመ ነው» «ፕሪንሲፕለድ ነው» «ለአገር ብሎ ነው ያደረገው» አይነቱን አባባሎቻችንን መተው አለበን። አንድ ሰው የሚያራምደው ርዕዮተ ዓለም ክፋት የሚጎትት ከሆነ እውነት ዓማኝ መሆኑ «ፕሪንሲፕልድ» መሆኑ ምን አይጠቅምም። ጭራሽ ጉዳት ነው። በደምብ ስለሚያምንበት ይበልጥ ጉዳት ያደርሳልና። ዋናው አላማችን በተሳሳተ ርዕዮተ ዓለም ወይም አቋም አለማመን። በተቻለ ቁጥር ማንኛውም ርዕዮተ ዓለም ወይም የፖለቲካ አመለካከት ከሰው በላይ አለማረግ። ዋናው ነገር ሰው ነው። ለሰው የሚያስፈልገው ፍቅርና ፍትህ ነው። ሌላው በሙሉ እነዚህን ማግኛ ዘዴ ነው። የምናምንበት ርዕዮተ ዓለም ጭራሽ ጥላቻና ጉዳት እያደረሰ ካየን የተሳሳተ መሆኑን ቶሎ ተረድተን መተው መቻል አለብን። ጣዖታችን ሊሆን አይገባም። ከኢግዚአብሔር በቀር ለምንም የእውነት አማኞች መሆን የለብንም።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ፍትህ. Show all posts
Showing posts with label ፍትህ. Show all posts
Monday, 5 March 2018
Monday, 10 October 2016
የትግሬ አድሎ
2009/1/29
ዓ.ም.
(2016/10/9)
(pdf)
ፖሊሱን
ምንድነው የሚያበሳጭህ
ብዬ ስጠይቀው እንደዚህ
ይለኛል።
«አድሎው
በዛ፤ እድገት «ለነሱ
ሰው»
ብቻ ነው፤
ምርጥ ቦታ «ለነሱ»፤
የማይፈለግ
ስራ ለሌላው። አይን ያወጣ ነው
እኮ!
ሰዉ
እጅግ መሮታል»
ለመንግስት
እቃ የሚያቀርብ ነጋዴ
እንደዚሁ ብሎ
ይነግረኛል።
«ኮንትራቶች
አገኛለሁ። ግን ምርጥ ኮንትራቶች «ለነሱ»
ብቻ
ነው።
ጊዜ
ቢያሳልፉም ጥራት ቢያጎሉም ምንም አይባሉም።
እንደ
በፊቱ አይደለም፤ አሁን
አይን
ያወጣ ሆኗል፤ ሰዉ
በጣም ተናዷልና ሁኔታው ያስፈራል»
ባለ
ሀብቱም እንደዚሁ አይነት
እሮሮ
ያሰማኛል።
«አዎ
ደህና መሬት ማግኘት እችላለሁ
ግን ምርጥ ቦታዎቹ «ለነሱ»
ሰው
ነው። አንድ
ቆንጆ ቦታ አግንቼ ከፍተኛውን ብር ተጫርቼ
«ለነሱ»
ተሰጠ።
እጅግ
ተበሳጭቻለሁ።
አይን ያውጣ
አድሎ
ነው»
ይለኛል።
በተዘዋዋሪ
ይህ ባለ ሀብት ከገዥ
ፓርቲው ጋር በሚያስፈልገው
ደረጃ ግንኙነት አለው።
የዩኒቨርሲቲ
ተማሪውም ከትንሽ ውይይት
በኋላ
ወደዚሁ አርእስት የገባል። «የነሱ»
ተማሪዎች
የሚያገኙትን እርዳታ ብታይ። ትርፍ ትምህርታዊ
ምክር፤ ሳምፕል ፈተናዎች፤ ከነሱ አስተማሪዎች
በትርፍ ግዜ እርዳታ»
ዝምብሎ
ከማማረር ለምን እናንተም እንደዚህ አታረጉም
ብዬ ጠይቀዋለሁ።
ጥያቄዬን
ያልፈዋል፤ ስለ «እነሱ»
ነው
ማውራት የሚፈልገው።
«እነሱ»
ማን
እንደሆኑ ሁላችንም እናውቃለን። አዎ በትክክሉ
ለመናገር የኢህአዴግ አባላትና አደርባዮቻቸው
ናቸው። ግን ሰዉ
«እነሱ»
ሲል
ባጭሩ
ትግሬዎች
ማለቱ ነው፤ አድሎ ሲል የትግሬ አድሎ ማለቱ
ነው።
እውነቱን
ለመናገር የትግሬ አድሎ ገርሞኝም
አያቅም። የመንግስታችን
አወቃቀር ይህን
አድሎ የሚያስከትል ነው።
የአንድ
ፓርቲ አገዛዝ
ነው ያለን።
የፖለቲካ
ተቀናቃኝ
የለም
አይፈቀድምም። እንኳን የነፃ
ምርጫ
ከፊል
የነፃ
ምርጫ የለም። በዚህ አይነት የ«አውራ
ፓርቲ»
አገዛዝ
ሁልግዜ ለፓርቲ አባላትና ለአደርባዮቻቸው
ከፍተኛ
አደሎ ይኖራል። በደርግ ዘመን ለኢሳፓ አባላት
አድሎ አልነበረምን?
በኃይለ
ስላሴ ዘመን
ከቤተ መንግስት ግንኙነት ያላቸው የተሻለ
ያገኙ አልነበረምን?
የዛሬውም
እንደዚህ ነው።
ይህን
ሃሳብ ስናገር አብዛኛው አዳማጭ
ይገረመዋል።
«የዛሬው
አድሎ
ግን በዘር
ነው እኮ»
ይሉኛል።
አዎን
የዘር
አድሎ ነው
ግን ህይ የዘር አድሎ፤
ማለት የትግሬ አድሎ፤
መኖሩንም
ልንገረም
አይገባም። ሁላችንም የኢህአዴግን
ታሪካዊ
አመጣጥን
እናውቃለን።
ከመጀመሪያው
ህውሃት
ከኢህአዴግ
ከፍተኛ
ኃይል ያለው
ፓርቲ ነበር
ዛሬም ነው፤
ቶር ስራዊቱንና በተለይ ደህንነቱን እንደሚቆጣጠር
እናውቃለን። ደግሞ
በአንድ
ግንባር
ወይም ፓርቲ
አገዛዝ ከዛ
ፓርቲ ውስጥ ኃይል
ያለው
ቡድን
ይበልጥ
ሙስና
አድሎ
ይታይበታል!
ለምን
ቢባል ሙስናና
አድሎ ዋና የኃይል ማከማቸትና ማንጸባረቅ
መንገድ
ናችሀው።
ምርጫ ወይም የፖለቲካ ውድድር ሰለሌለ ኃይል
በዚህ መልኩ ነው የሚከማቸው። በአውራ
ፓርቲ አገዛዝ ሌላ
አካሄድ ሊኖር
አይችልም።
ይህ
ሁሉ እያልኩኝ ሳለ
በኔ
አመለካከት የትግሬ
አድሎ ካሉት
የሀገራችን የፖለቲካና
ህብረተሰባዊ ችግሮች
ትንሹ
ነው። ለኢህአዴግ ግን
ዋናው ችግሩ
ነው!
ይህ
እንዴት ይሆናል?
ለኔ
ዋናው ችግር የአንድ ፓርቲ የልማት መንግስት
አገዛዙ የህዝቡን የአንድነትና
የህብረተሰባዊ
መንፈስ እያጠፋ መሆኑ ነው። ከሌሎች
ጽሁፎች
እንደጠቀስኩት የኢህአዴግ
መንግስት
ለህዝቡ ያቀረበው
ውል እንዲህ ነው፤ ልማት
ሰጥሃለሁ፤
አንተ
ደግሞ በስልጣኔም
ይሁን በሙስናዬ
አትምጣብኝ።
በዚህ ውል
መሰረት
ሰዎች ከመሬታቸው ይፈነቀላሉ። መሬታችሁ
ለባለ ሀብት ይፈለጋል እየተባለ
ሳንቲም ተሰተው ይባረራሉ፤ ክስ ላይ ባለስልጣኑ
ወይም አደርባዩ ጥፋተና ቢሆንም ይረታል፤
ሰዎች ትንሽ ጸረ ኢህአዴግ ነበር ቢናገሩ
ይታሰራሉ፤
ህዝቡ ከፍርድ ቤት ፍትህ አያገኝም፤
ጉቦ ካልሰጠ ውይም ወዳጅ ከሌለው ንብረቱን፤
ስራውን፤
ወዘተ ሊያጣ
ይችላል። ለኔ
እነዚህ ችግሮች ከትግሬ
አድሎ እጅግ
የሚበልጡ ናቸው።
ፍትህ፤ ነፃነት፤ ወዘተ አለመኖራቸው
ነው ዋናው ችግር። ሁለተኛ ደረጃ
ችግር
የማንም
አድሎ።
ሶስተኛ ደረጃ
ችገር የትግሬ
አድሎ
ነው።
በተዘዋዋሪ
ባለንጀራችን
መሬቱን ሲቀማ፤ አለ አግባብ ሲታሰር፤ ፍትህ
ሲያጣ፤
ወዘተ ማንኛችንም
ዞር ብለን
እንርዳህ አንለውም።
አይዞህ ብለን
የገንዘብም ወይም ሌላ
ድጋፍ አንሰጠውም።
የራሳችንን
ኑሮ፤ የራሳችንን
የ«ልማት»
ድርሻ
እያሳደድን
ባለንጀራችን
እየተጎዳ
ዝም እንላለን።
ምንስት
ላይ ጮኸን እንታሰር አደለም። እንርዳው፤
ግን አንረዳውም። ታላቁ
ችግር ይህ ነው። እውነቱን
ለመናገር ኢህአዴግን በስልጣን እስካሁን
የጠበቀውም ይህ መንፈስ ነው።
ግን ይህ መሰረታዊ ችግር እያለ መንግስቱን የሚያናጋው የዘር ችግሩ ነው። ይህ የሰውን አስገራሚ ባህሪ ያሳያ። «ሀገሬን በዚህም በዛም አበላሽ ግን በዘሬ አትምጣብኝ! ጉቦኛና ዘራፊ ሁን ግን በዘር ስም አታድርገው!» እኛ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እንላለን። ያሳዝናል።
ይህን አውቆ ኢህአዴግ የዘራውን ነው የሚያጭደው። ግን ለሀገሪቷ ህልውና አይበጅም። እኛ የ«ትግሬ አድሎ» ሳይሆን ምንም አይነት «አድሎ»ን አንፈልግም ስንል ነው ሀገራችን የሰላም መንገድ የምትጀምረው።
ይህን አውቆ ኢህአዴግ የዘራውን ነው የሚያጭደው። ግን ለሀገሪቷ ህልውና አይበጅም። እኛ የ«ትግሬ አድሎ» ሳይሆን ምንም አይነት «አድሎ»ን አንፈልግም ስንል ነው ሀገራችን የሰላም መንገድ የምትጀምረው።
Labels:
contradictions,
developmental state,
ልማታዊ መንግስት,
ልማት,
መሬት,
ሙስና,
አውራ ፓርቲ,
አድሎ,
የትግሬ አድሎ,
ጎሰኝነት,
ፍትህ
Subscribe to:
Posts (Atom)