Showing posts with label multiculturalism. Show all posts
Showing posts with label multiculturalism. Show all posts

Tuesday, 16 April 2019

በስመ አብ! አሁንም ምሁሮቻችን ይህን ስርዓት «multiculturalism» ይሉታል

ይህ ውይይት ገንቢ ይመስለኛል፤ ተመልከቱት። ግን አሁንም በርካታ ሰዎች የሚሳሳቱትን ስህተት ሰርተዋል። አሁን ያለውን multinational federalism (ይጎሳ አስተዳደር) "multiculturalism" ብለው ይጠሩታል። ይህ መሰረታዊ የቃል እና ሃሳብ አጠቃቅም ስህተት ነው።

የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በዓለም ብቸኛ እና ጸንፈኛ የሚያደርገው በጎሳ፤ በ«ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች»፤ የተመሰረተ ነው። ይህ ሌላ ሀገር የለም። የጎሳ ፖለቲካ እና የጎሳ ምብት ሌሎች ሀገራት አሉ፤ ግን የህገ መንግስታቸው መሰረት አይደለም። እንደ ካናዳ፤ ህንድ፤ ወዘተ የጎሳ ፍላጎት፤ መብት፤ ጥያቄ፤ ወዘተ፤ የባህል እና ቋንቋ ብዝሃነት፤ የማንነት ምዝያነት ወዘተ ከኢትዮጵያ በተሻለ መንገድ ያስተናግዳሉ። ግን ይህን የሚያደርጉት የባህል እና እቋንቋ ብዝሃነት የሚያስተናግድ የዜግነት ህገ መንግስት ተጠቅመው ነው እንጂ ቀጥታ የጎሳ ሀገ መንግስት ተጠቅመው አይደለም።

ልዩመንት ምንድነው? የኢትዮጵያ ባለቤቶች ጎሳዎች ናቸው። ስለዚህ እንደ ቤኒሻንጉል አይነቱ ክልል ክልሉ የተወሰኑ ብሄር ተወላጆች ንብረት ነው ብለው በህግ መደንገግ ይችላሉ። የሌላ ብሄር ተወላጅ ቤኒሻንጉል ሲኖር እንደ ሁለተኛ ዜጋ ነው። የዜግነቱ መብቶች ከቤኒሻንጉል ጎሳ መቶች በታች ነው። ይህ ዜጋ መሬትና ቤት ካለው ከቤኒሻንጉል ጎሳዎች የተከራየው ነው። ወዘተ፤ ሁለተኛ ዜጋ ነው።

በነ ህንድ አይነቱ ሀገር ክፍለ ሀገሮቹ የተከለሉት ከሞላ ጎደል ጎሳን ታስቦ ነው። ስለዚህ በያንዳንዱ ክልል ብዙ ቁጥር ያለው ጎሳ የጎሳ መብቱን ያስፈጽማል። ለምሳሌ ቋንቋውን እና ባህሉን የክልሉ ቋንቋእና ባህል ያደርጋል። ወዘተ። ግን እዛ የሚኖር የማንኛውም ጎሳ ተወላጅ ሙሉ መብት አለው! ይህ ነው ልዩነቱ። «መጤ» አይደለም። የክልሉ እኩል ባለቤት ነው።

ይህ ልዩነት ውጤቱ ምንድነው? በጎሳ ፌደራሊዝም ጎሳ ከሁሉም በላይ ስለሆነ ግጭት ይበዛዋል። ይህን በኢትዮጵያ በደምብ አይተነዋል እያየነውም ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_4.html)። የቋንቋ እና ባህል ብዝሃነት ያለው የዜግነት ፌደራሊዝም ግን ግጭት ቢኖርም ዜግነት ከሁሉም በላይ ስለሆነ ግጭቶቹ እጅግ አነስተኛ ናቸው።

ስለዚህ እንደገና... ቁንቋችንን እናስተካከል። ይህ ህገ መንግስት multiculturalism አይደለም ያመጣው። Multinationalismን ነው ያመጣው። የትም ሀገር የሌለ ጸንፈኛ experiment ነው የሚያደርገው። ይህ ሙከራ ኢትዮጵያን የግጭቶች ምህዳር አርገዋታል። አሁን የሚያስፈልገን ወደ ለዘብተኛ መንገድ ተመልሶ ወደ የቋንቋ እና የባህል ብዝሃነት ያለው በተዘዋዋሪ የጎሳ ፋልጎቶችን የሚያስተናግድ የዜግነት አስተዳደር ነው የሚያስፈልገን።


Monday, 1 October 2018

የጎሳ አስተዳደር ጎጂ መሆኑን ሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች አምነዋል!

የጎሳ አስተዳደር የኢትዮጵያ ግጭት ምንጭ መሆኑ ሁሉም ፖለቲከኞቻችን ልሂቃኖቻችንም እንዳመኑበት እናውቃለን?!

1. እነ ህወሓት ከነ ቀድሞ መሪአቸው መለስ ዜናዊ ደጋግመው በሀገራችን የጎሳ እልቂት እንዳይፈጠር ያስጠነቅቁ ነበር። እንደ «ርዋንዳ» ልንሆን እንችላለን ይሉ ነበር አሁንም ይላሉ።

2. ኦሮሞ ብሄርተኞችም እንዲህ ደጋግመው ጎሳዎች በሰላም እርስ በርስ ተማምነው ተፋቅረው መኖር አለባቸው ብለው ይሰብካሉ። ካልተከባበርን የጎሳ እልቂት ሊመጣ ይችላል ብለው ያስጠነቅቃሉ። የጎሳ ግጭት እና እልቂት አንድ የሀገራችን ዋናው potential ችግር መሆኑን በተደጋጋሚ ይገልጻሉ።

3. የለማ ቡድን ከነ ጠ/ሚ አብይ አህመድም ደጋግሞ የጎሳ አብሮ መኖር አስፈላጊነት እና የጎሳ ግጭት አደጋን ደጋግመው ይቀልጻሉ።

4. የ«ኢትዮጵያዊነት» ጎራውም ደጋግሞ ስለ በጎሳዎች የሚያስፈልገው ፍቅር እና ሰላም ይሰብካል። ይህን «የመጨረሻ» የፖለቲካ እድል ካጣን ወደ ጎሳ እልቂት ልንገባ እንችላለን ይላሉ።

እንሆ በሁሉም ጎራ ያሉት ፖለቲከኞቻችን ለኢትዮጵያን ህልውና ዋና አስጊ ነገር የጎሳ ግጭት እንደሆነ እንደሚያምኑ አሳይተዋል።

ታድያ በጎሳ አስተዳደር (ethnic federalism) እና በጎሳ ብሄርተኝነት ከዚህ በላይ ፍርድ አለ! ሀገራችን የጎሳ ግጭት አደጋ ላይ ናት ከሆነ ምክንያቱ ለ27 ዓመት የነበረን የጎሳ አስተዳደር መዋቅር ነው ማለት ነው! ብያንስ ይህ ጎሳ አስተዳደር አልሰራም ግጭቶችን አባብስዋል ማለት ነው! የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ መሆኑ ሁላችንም አይተነዋል። ማመን ብቻ ነው የቀረን።

በመጨረሻ ማለት የምፈልገው አንዳንድ የጎሳ ብሄርተኞች የጎሳ አስተዳደር ቢቀር ታላቅ ፍርሃት አላቸው። ማንነታችን ይዋጣል ይላሉ። በፍፁም። ሀገራችን ህብረ ባህላዊ ህብረ ቋንቋዊ ነው መሆን ያለበት። ኦሮምኛ በሀገራችን በሙሉ ይነገር ነው የምንለው በኦሮሚያ ብቻ አይነገር። አዲስ አበባም ኦሮሚያም የሁላችንም ነው የምንለው የኦሮሞውች ብቻ አይደለም። ሌላውም ኢትዮጵያ የኦሮሞ ነው ነው የምንለው። ይህ እንዲሆን የሚያስፈልገው ህብረ ባህላዊ/ቋንቋዊ ስርዓት ነው ንጂ የጎሳ የክልል የአጥር አስተዳደር አይደለም።