ያለፉት 60 ዓመት የኢትዮጵያ ብሄርተኛ የፖለቲካ ጎራው ታሪክ እጅግ አሳዛኝ እና አሳፋሪ ነው። ከዛ በፊት እስከ ወደ 1955 ሀገራችን ዓለም ዙርያ የተከበረች ነበረች። በዲፕሎማሲ፤ በሀገራዊ ኃይል ወዘተ ከአቅሟ በላይ የምትሰራ ነበረች። አንድ አንድ ምሳሌዎች፤
1. የበርካታ የዓለም ሀገሮች ተቃውሞ በላቀ የዲፕሎማሲ ስራ አሸንፋ ኤርትራን ወደ ኢትዮጵያ መለሰች። ይህ የዲፕሎማሲ ድል ከሀገራችን ከአቅማችን አስር እጥፍ በላይ ነበር ግን አደረግነው።
2. የአፍሪካ ቁንጮ ሆንን ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት እኛን እንደ ምሳሌ ያይን ነበር። በዲፕሎማሲ እና ሀገር ኃይል ደረጃ ብቻ ሳይሆን በታሪክ እና ባህል። ይህ ክብሬታ ለኢትዮጵያ ብዙ ጠቅሟታል።
3. በዓለም ዙርያ ያሉት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያኖች ስብሰባ አቀደች የኦሪዬንታል ኦርቶዶክስ ስብሰባውን አከናወነች ስምምነቶች አስፈጸመች።
ከ1955 አካባቢ በኋላ ግን እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኖች እርስ በርስ በመጣላት ሀገራችንን ድራሹን አጥፍተናል። መጀመርያ አስፈላጊ የፖለቲካ ለውጦች ባለማድረግ ቀጥሎ ልዩነቶቻችንን በጡንቻ በማካሄድ ሀገራችንን አሳልፈን ለጎሳ ብሄርተኞች ሰጠን። የመጨረሻ ውጤት ምን ሆነ ሻዕብያ እና ወያኔ የሀገራችን 10%ን ወክለው ኢትዮጵያን ተቆጣጠሩት። ይህ ለኛ 90% እጅግ አሳፋሪ ክስተት ነበር አሁንም ነው።
ይህ ታሪክ እንዳለ ሆኖ አሁን ያለፉትን ስህተቶቻችንን ለማርም የሀገራችን ሆደ ሰፊ ብዙሃን እና እግዚአብሔር ዳግም ለማረም እድሉን ሰጥተውናል። ሆንም አንታረምም ብለናል። ዋናው እና መሰረታዊ ችግራችን ያለፉትን አሳፋሪ ድርጊታችንን አለማመናችን ነው ሰው ችግሩን ካላመኑ መፍትሔ አያገኝምና። ጥፋቶቻችንን ላለማምን እና ለመደበቅ ብለን ይመስለኛል ሁል ጊዜ ለችሮቻችን ወያኔ፤ ሻዕብያ፤ ኦነግ፤ «አሜሪካ»፤ ሩሲያ፤ ኤርትራ፤ «አራብ ሀገራት» ወዘተን የምንወቅሰው። እኛ የገዛ ቤታችንን በር ከፍተን እነዚህ ደብተው እንደፈለጉት ሲያደርጉ በራችንን እንዴት ተከፈተ እንዝጋው ከማለት ለሚን ይገባሉ ብለን መጮህ! ዋናው ጣፍቱ የኛ እንደሆነ እናውቃለን ግን እፍረታችን ከባድ ነው መሸሽ ብቻ ነው የምንፈልገው።
ለማስተዋስ ያህል ባለፈው ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አንድ የኤርትራ የጦር አዛዥ ያለው ነገር አለ። አንድ ኤርትራዊ አስር ኢትዮጵያዊ ዋጋ አለው ብሎ ፎከረ። ይህ አዲስ ፉከራ አልነበረም በደርግ ጦርነት ላይ የተመሰረተ ነው። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምን ያህል እንደተናቁ ነው የሚያሳየው። ድሮ ኤርትራ በሰላም ያጠቃለልን ዛሬ ይቀልዱምን ጀመረ። እስከ ዛሬ በጦር ሜዳ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የፖለቲካ ዋይንም የንግድ ዘርፎች በሙሉ ኤርትራዊዎችም ትግሬዎችም እደዚህ ያስባሉ። እኛ ደደብ አህዮች እነሱ አስር እጥፍ ጎበዝ። ከኢትዮጵያዊዎች ብልጥ፤ ጠንካራ፤ የተማርን ወዘተ ነን ብለው ያስባሉ። ይህ የተሳሳተ አስተሳሰብ ግን የነሱ ጥፋት አይደለም። በፍፁም የነሱ ጥፋት አይደለም። እኛ እርስ በርስ ተጨራርሰን እራሳችንን ከታላቅ ህዝብ እና ሀገር ወደ ደካማ ለማኝ ስላወረድን እነሱ የሚያዩትን እውነታ ነው የሚናገሩት። ይህ ለኛ እጅግ አሳፋሪ ነው።
የሰው ልጅ ግን እፍረቱ ስለሚያሳምመው ሊደብቀው ይፈልጋል። ለችግሮቹ ሃላፊነት ከመውሰድ ሁል ጊዜ በውነትም በውሸትም ሌሎችን ይወነጅላል። እኛም አሳፋሪ ድርጊቶቻችንን እና ውድቀታችንን ለመደበቅ ያህል ለ27 ዓመት መጀመርያ ሻዕብያን፤ ኦነግን፤ ወያኔን ወዘተ እየወቀስን ቆይተናል። አሁንም እግዚአብሔር የማይገባንን ጠንካራ የድሮ ዘመን አይነት ኢትዮጵያዊ መሪ ልኮልን አሁን ላሉን ችግሮች ህወሓትን እንወቅሳለን! እንደ ወቀሳችን መጠን ህወሓት ማንም የማይሳነው ግዙፍ ኃይል እንዲመስለን አድርገናል! (ግን 6% ነው የሚወክለው እንላለን!) የራሳችንን ድክመንት ለመሸፈን ላለማየት ለህወሓት የሌለውን አቅም ፈጠርንለት የሌለውን ጥንካሬ ሰየምንለት።
አሁንም እዛው ላይ ነን። አሁንም ከኢትዮጵያ ብሄርተኛ ፖለቲከኛ ተንታኝ አስር ጽሁፎች ካነበብን አስሩም ስለ «ሌሎች»፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች፤ ኦነጎች ወዘተ ለቅሶ ነው። እንጂ አንድም ስለራሳችን ጥፋቶች እና ማረምያኦች የሚናገር የሚጽፍ የለም። ኢሳትን ከተመለከትን ስለ«ጠላት» ለቅሶ ነው። ጋዜቶች ሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁ። የኛ የ«ተፎካካሪ» ድርጅቶች ወሬም እንዲሁ ምናላባትም ይብሳል። እንደ ሚና እና አቅም የሌላው ተጨቋኞች ማልቀስ፤ ማልቀስ፤ ማልቀስ።
እንደዚህ በማድረግ ለራሳችን ጥልቅ የሆነ የእፍረት ጉድጓድ ቆፍረናል። የራሳችን ህልውና በራሳችን ሳይሆን በሌሎች የተቆጣጠረ ነው ብለናል። እነዚህ ሌሎች ደግሞ ከኛ እጅግ አናሳ የሆኑ ናቸው። ይህ አስተሳሰብ ግልጽ የሆነ የዝቅተኝነት መንፈስ እንዲያድርብን አድርጓል። እውነት ነው በተፈጥሮ ሻ'ዕብያዎች፤ ወያኔዎች፤ ኦነጎች ወዘተ ከኛ ይሻላሉ ይበልጣሉ ብለን አምነናል! ይህን የተሳሳተ እምነት የገባንበት ለችግሮቻችን በሙሉ እነሱን ፈላጭ ቆራች እራሳችንን አቅመ ቢስ ስለምናደርግ ነው። ይህ የዝቅተኝነት መንፈስ የሚፈጥረውን እፍረት ለመሸፈን ደግሞ እንደገና እነሱ ላይ እንወርዳለን ከእፍረታችን ለመሸሽ ብለን። ይህ "vicious cycle" ሆኖናል ማቆም ያልቻልነው ሱስ ሆኖናል። የድሮ መሪዎቻችን (ከነ ስህተቾቻቸው) ይህን ቢያዩ ኢትዮጵያዊ መሆናችንን የሚያምኑ አይመስለኝም።
እግዚአብሔር ችር ነው እና አሁን በራሱ የሚኮራ፤ ሃላፊነት የሚወስድ፤ ጥፋቱን የሚያምን፤ ለጥፋቶቹ ንስሃ ገብቶ ይቅርታ የሚጠይቅ፤ ሌሎችን ለራሱ ጥፋቶች እና ችግሮች ከመውቀስ እራሱን በተገቢው ወቅሶ መፍትሔውን ፈልጎ አግኝቶ ስራ ላይ የሚያውል ጀግና መሪ ሰጥቶናል። ለኛ ለኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምሳሌ ሊሆን የሚገባን መሪ። ከ60 ዓመት ጥፋታችን በኋላ አሁንም እራሳችንን ለማረም እድል ተሰጥቶናል። ይገርማል!
አሁን የ60 ዓመት ጥፋታችን ውጤት ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ተዝናንተን አድሃሪ፤ ተራማጅ፤ ደርግ፤ ኢዲኡ፤ ኢህአፓ፤ ሜሶን ወዘተ እየተባባልን ተጨራረስን። ባቃጠልነው ባዶ ሜዳ የጎሳ ብሄርተኞች ገቡ። አሁንም የሀገራችን ታላቅ የፖለቲካ ችግር የጎሳ ብሄርተኝነት ነው ብለን እናምናለን ላለፉት 27 ዓመት ያመጣውን ግጭቶች አይተናልና። ስለዚህ የእርስ በርስ መጣላታችን የመስማማት እና አብሮ መስራት አለመቻላችን ምን አይነት ውጤት እንደሚያመጣ እናውቃለን። በዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን ለመቀነስ ለማጥፋት ከፈለግን እኛ የሀገር ብሄርተኞች አንድ መሆነ እንዳለብን የእርስ ብሰር ችግሮቻችንን መፍታት መችሃል እንዳለብን ለጋራ ጥቅም አብሮ መሰለፍ እንዳለብን ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። ግልጽ ብቻ ሳይሆን ብቸኛ መንገዳችን እንደሆነ ሊገባን ይገባል። አማራጭ የለንም።
ካሁን ወድያ ከማህላችን ጣት መጠቆም ስለ ሻዕብያ፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች ወዘተ ማልቀስ ክልክል ይሁን! ክልክል ይሁን! ይህ አስተሳሰብ ነው ወደ ኋላ የሚጎትተንና። እንደ ጠ/ሚ አብይ ችግር ሲያጋጥምን እራሳችንን ምን አድርገን ነው ይህ ችግር የገጠመን ነው ማለት ያለብን። ወሬዎቻችንን፤ አነጋገራችንን፤ አስተሳሰባችንን፤ ጽሁፎቻችንን እንቀይር። ሌሎች አጎልብተን ስለነሱ በኛ ያላቸውን ሚና ከማውራት እራሳችንን አጎልብትን እንገኝ እራሳችን ለራሳችን አለቃ ነን ችግር ካለን እንፈታለን እንበል። ያህን አይነት ባህል ማዳበር አለብን የ60 ዓመት የውድቅ ልምድ ለመቀየር። ታላቅ ስራ ነው ግን እድለኛ ነን እንደ አብይ አይነቱ የጎላ ምሳሌ ሰጥቶናል።
በመጨረሻ አንድ የጠ/ሚ አቢይ ምሳሌ ልጥቀስላችሁ። ከኢሳያስ ጋር ያለውን ግንኝነት እንየው። እራሱን እንደ ታናሽ ወንድም ትሁት አድርጎ ነው የሚያሳየው። እራሱን ዝቅ ያደርጋል ለምሳሌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሲመጣ እራሱ ጠቅላይ ሚኒስጤር ሆነ ይቀበላል። የ100 ሚሊኦን ህዝብ መሪ ሆኖ ወደ ስድስት ሚሊዮንዋ ኤርትራ መጀመርያ እሱ ነው የሄደው። ለምን። ይህን ማድረግ የሚችሉ በራሱ ስለሚተማመን ነው። ሁኔታውን እራሱ እንደሚቆጣጠር ስለሚያውቀው የራሱን አጀንዳ ማስረገጥ እንደሚችል ስለሚያውቅ እራሱን ዝቅ ማድረግ ምንም አይመስለውም። በራሱ የሚኮራ ብቻ ነው እራሱን ዝቅ ማድረግ የሚችለው። ሌሎቻችን በራሳችን የምናፍር ሰውው ገበናችንን ያቅብናል ብለን የውሸት ጭምብል አድርገን እንኮፈሳለን። አያችሁ እንዴት በራስ ሃላፊነት መውሰድ ሌሎችን ለራስ ችግር ሌሎችን አለመወንጀል እራስን እንደሚያጎለብት። ሌላው መንገድ እራስን አቅመ ቢስ ያደርጋል። ለራስ ሃላፊነት መውሰድ ግን ያጎለብታል። ዶ/ር አብይም የፖለቲካውን ጉልበት ከዚህ ነው የሚያገኘው። እስቲ ትንሽም እንማር!
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ሃላፊነት መክዳት. Show all posts
Showing posts with label ሃላፊነት መክዳት. Show all posts
Sunday, 15 July 2018
Friday, 17 November 2017
ከማነኛዉ ወገን ነህ? ቄሱ!
(from Father Arseny: Priest, Prisoner, Spiritual Father)
በመጀመሪያ ወደ እስር ቤት ስትገባ ቀናትን ትቆጥራለህ፣ ከዚያም ሳምንታትን፣ ከሁለትዓመታት በኋላ በሚመጣዉ ጊዜ የምታደርገው ሞትን መጠበቅ ብቻ ነው፡፡ አድካሚ የጉልበት ሥራ፣መራራ ረሐብ፣ እርስ በእርስ መናቆር፣ መደባደብ፣ ብርዱና ከቤተ-ሰብ መለየቱ ያደድቡህናየማይቀረውን ሞት ብቻ እንድታስብ ትሆናለህ፡፡ ስለዚህ አብዛኛዎቹ እስረኞች በስነ-ምግባር ረገድደካሞች የሚሆኑት፡፡
ለብዙዎቻችን የፖለቲካና ለሁሉም የወንጀለኛ እስረኞች ስሜታችን እንደ ሁኔታዉ ግራና ቀኝየሚዋልል ነበር፣ የአለቃው ቁጥጥር፣ የሚሠረቅ ዳቦ፣ እርስ በእርስ መናቆር፣ በተለይ በእስር ቤቱለተመደቡ እስረኞች የተመደበው እጅግ ከባድ የጉልበት ሥራ፣ ልዩዉ የቅጣት ክፍል፣ በረዶየሚሆኑ ጣቶች ወይም በጎረቤት የእስር ቤቱ ክፍሎች ውስጥ የሚሞቱት እስረኞች ስሜትንለመቀያየር ምክንያቶች ነበሩ፡፡ ሐሳብህ ሁሉ ተራና በእነዚህ ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ይሆናሉ፡፡ እጅግበጣም የአያሌዎቹ እስረኞች ሕልም እስከሚጠግቡ በልተው ለሁለት ወይም ለሦስት ሰዓታት ያህልመተኛት ወይም ግማሽ ሊትር ቮድካ አግኝተው ሁሉንም ጨልጠው እንደገና ሌላ ተጨማሪ ምግብቢሰለቅጡ በወደዱ ነበር፣ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ባዶ ምኞቶች ብቻ ነበሩ፡፡
እጅግ በጣም ትቂት የፖለቲካ እስረኞች በተቻላቸው መጠን ርኅሩኅ ሆነው ለመቆየት ሞከሩ፣ራሳቸውንም ከሌላዉ በመለየት፣ እርስ በእርስ በመደጋገፍና ራሳቸውን ወደ ተራ የወንጀለኛ እስረኞችዝቅ ላለማድረግ እየጣሩ ነበር፡፡ በተቻላቸው መጠን የእስር ቤቱ ደንብ በሚፈቅደው መሠረትራሳቸውን በማያዋርድ ሁኔታ ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከእስር ቤቱ የበረንዳ ማዕዘን ላይ ቆመውቃለ-ተናብቦ/ሌክቸር ያደርጋሉ፣ ግጥም ወይም አጭር ሳይንስ-ነክ ጽሑፍ ያነባሉ፣ አልፎ አልፎምየትም ባገኙት ብጣሽ ወረቀት ሳይቀር ማስታዎሻ ይጽፋሉ፡፡ በሆነ ርእሰ-ጉዳይ ላይ ሞቅ ያለ ክርክርይነሣል፣ ይሁን እንጂ እጅግ በጣም የሚጦፈው ፖለቲካን አስመልክቶ የሚደረገው ክርክር ነበር፡፡አልፎ አልፎ የወንጀል እስረኞችም ሳይቀር በክርክሩ ይቀላቀሉ ነበር፤ ፖለቲከኞች በፖለቲካ ረገድብዙም ፍላጎት አይታይባቸውም፣ ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ፍላጎቱ ነበራቸው፡፡ ሰዎች በስሜትየሚቃወሟቸውን በጥላቻ ይከራከሯቸው ነበር፡፡ አባ አርሴኒ በዚህ ክርከር ፈጽመው አይሳተፉም፡፡ነገር ግን ከዕለታት አንድ ቀን ያለፍላጎታቸው ተጎትተው ገቡ፡፡
ምንም ጊዜም እስረኞች ሐሳባቸውን ለመግለጽ ይፈራሉ፣ ይሁን እንጂ ወደሞቀ ክርክርውስጥ ሲገቡ ፍርሃት ሊያስከትል የሚችለውን ነገር ሁሉ ይረሱታል፡፡ በክርክሩ ከሚሳተፉት መካከልትቂቶቹ የአሰብሁትን መናገር ሳልችል ድምፄ ታፈነ፣” ይላሉ፡፡
እስረኞች ተቆጥረው የእስር ቤቱ በሮች ተቆለፉ፣ ከግድግዳዉ በስተጀርባ ነፋሱ እየነፈሰነበር፤ ግግሩ በረዶ መስኮቶችን እንዳይከፈቱ አደረጋቸው፣ ክፍሉ የታፈነና ዕርጥበት-አዘል ነበር፣ሆኖም ግን ውስጡ ሞቃት ነው፡፡ አምፖሎቹ ከሚፈለገው ከግማሽ በታች ብርሃናቸው መጠን ባነሰያበሩ ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ትካዜና ሐዘን እንዲኖር ያደርጋሉ፡፡ በመሆኑም ሰዎች ብቸኛ ይሆናሉ፡፡እስረኞቹ በአንድነት ተሰበስበው መነጋገር፣መከራከርና ያለፈውን ማስታወስ ጀመሩ፡፡ ወንጀለኛእስረኞች ካርድ ወይም እንዶሚኖ ለብር ወይም ለመቁኑን እየተጫወቱ ነበር፡፡ አባ አርሴኒ ካረፉበትአልጋ አጠገብ የተሰበሰቡ እስረኞች በመንግሥት ላይ ያላቸውን አመለካከት ርእሰ-ጉዳይ በማድረግኃይለኛ ክርክር አደረጉ፡፡ በ15 ደቂቃዎች ውስጥ 20 የሚሆኑ ሰዎች ወደ ክርክሩ ተቀላቀሉና ክርክሩጦፈ፡፡ አንዱ የአንዱን ንግግር በማቋረጥ ሥጋት ጨመረ፡፡ ከተከራካሪዎች መካከል ቀድሞ የፓርቲአባል የነበሩ፤ ከልዩ ልዩ የሕይወት ተሞክሮዎች የተማሩ ሰዎች፤ በጣም ትቂት ቭላስቶቭትሲዎችናx1ሌሎችም ነበሩ፡፡ “እዚህ ያለነው ለምድነው? ለምንም! ፍትሕ የት አለ? ሁሉም መረሸን አለባቸው!”በማለት ፊታቸውን አኮሳትረው ይጮሁ፡፡ አራት ወይም አምስት የሚሆኑ ቀድሞ የፓርቲ አባልየነበሩ በነገሩ ባለስማማታቸው “አሳዛኝ ስሕተት እየተፈጸመ ነው” በማለት ገለጹ፡፡ እንደአበባላቸውከሆነ እየሆነ ያለው ሁሉ እራሱ ስታሊን በማያውቀው በትቂት ሠርጎ-ገቦች በመሞኘት የሚፈጸምመሆኑን ገለጹ፡፡
“የሩስያ ሕዝብ ግማሹ በእስር ቤት ታጉሮ ሳለ ተታለልን! አስተዳዳሪዎቹም እንዲደመሰሱታቀደ!” በማለት አንድ ድምፅ ጮኸ፡፡
ስታሊን አሳምሮ ያውቃል፣ የራሱ ትእዛዝ ነው፣” አለ ሌላዉ፡፡
ስታሊንን በመግደል አሲርሃል ተብሎ የተያዘው ከስረኞቹ አንዱ እጅግ በጣም በመበሳጨቱድምፁ ተቆራረጠ፡፡ ትቂት ቭላስቭትስኪዎች ማነኛውንም ሐሳብና በመቃወም ጮኹ፡፡
“እነዚያ የፓርቲ አባላት መሰቀል ወይም መረሸን አለባቸው!” አለ ሌላ አንድ ሰው፡፡ከ1917 ዓ/ም ጀምሮ ዋና የቮልሼቪክ ፓርቲ አባል የነበረ አንድ ሽማግሌ ሰው በመጀርመንጦር ሠራዊት ውስጥ ካገለገለ ሰው ጋር ተደባደበና በኃይል መሳደብ፡፡
“አንተ ባንዳ ነህ!” ብሎ ጮኸ፡፡ “መረሸን ነበረብህ፣ ነገር ግን በሕይወት እስካሁን አለህ! እኔራሴ እንዳተ ያሉትን ባንዳዎች እረሽናቸዋለሁ ወይም እሰቅላቸዋለሁ፡፡ እስካሁን ድረስ ወደናንተባለመዝቴ አዝናለሁ፡፡ ስሕተትም ፈጽሜያለሁ፣ ይሁን እንጂ አንተ ባንዳዉ በዚህ እስር ቤት ውስጥከኔ ጋር ትሞታለህ ብየ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
“እኔ ባንዳ ነኝ? እኔ የሶቭየትን መንግሥት ከሚደግፉት አንዱ ነኝ!” “ማለት ትችላለህ፣ ነገር ግን አንተም ባንዳ ነህ፣ ለዚህ ነው መንግሥት እዚህ እስር ቤትያመጣህ፡፡”
በርቀት የነበሩ ሰዎች ሳቁ፣ ሆኖም ግን ክርክሩ በሞቀ ሁኔታ ቀጠለ፡፡ አንድ ሰው ድንገት“አብያተ ክርስቲያናትን አውድመው ሃይማኖትን አጠፉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ሰው ካጠገቡ ቁጭ(1) ያሉትን አባ አርሴኒን አስታወሰና “ደህና፣ ፒዮትር አንድሬየቪች ንገረን፣ ባለሥልጣናቱን እንዴትታያቸዋለህ?” ሲል ጠየቀ፡፡
አባ አርሴኒ ዝም ብለው ክርክሩን ሲያዳምጡ ቆዩ፣ ነገር ግን አሁን ያለፍላጎታቸው ወደክርክሩ ጎትተው ከተቷቸው፡፡ አባ አርሴኒ ምን እንደሚመልሱ ግልጽ ነበር፡፡ በእስር ቤቱ ውስጥ ብዙየተሰቃዩ ሰው ስለነበሩ የአባ አርሴኒ ጓደኞች ተጨነቁ፡፡
በጂትሎቭስኪ የሚመሩት ቭላስቭትሲዎች ከሌላዉ እስረኛ ራሳቸውን አግለው እየኖሩ ነበር፡፡የሚፈሩት ምንም ነገር አልነበረም፤ በምን ምክንያት እንደተያዙ ያውቃሉ፣ የሕይወታቸው ፍጻሜምቅርብ እንደሆም ይገምታሉ፡፡ ከነርሱ አንዱ “እንግዲህ በል አፍስሰው ቄሴ!” አለ፡፡
አባ አርሴኒ ላፍታ ዝም አሉና “የጦፈ ክርክር ስለያዛችሁ ክርክሩ ወደ ጭቅጭቅ ተቀየረ፣ሊትቆጣጠሩት ወደማትችሉት ደረጃ ደረሰ፡፡ በእስር ቤት መኖር አስቸጋሪ እየሆነ በመምጣቱሁላችንም ፍጻሜያችን ምን እንደሚሆን እናውቃለን፡፡ ክርክሩም መራራ የሆነው ለዚህ ነው፡፡የማይረሸን ወይም በሕይወት የሚተርፍ የለም፡፡ ሁላችሁም ባለሥልጣናቱን፣ ትእዛዛቱንና ሰዎችንትዎነጅላላችሁ፤ ሌላውን ለማስቆጣት ጎትታችሁ ወደ ክርክሩ አስገባችሁኝ፡፡
“ኮሚኒስቶች ምዕመናንን አስረዋል፣ አብያተ ክርስቲያናትን ዘግተዋል፣ ሃይማኖትን ትተዋልብላችኋል፡፡ አዎ፣ ላዩን ሲታይ እውነት ይመስላል፤ ነገር ግን እስቲ በጥልቀት እንመልከተው፣ያለፉትን ጊዜያት በጥልቀት እንመልከት፡፡ ከኛ ከሩስያውያውን ሕዝቦች መካከል ብዙዎቹሃይማኖታቸውን ክደዋል፣ ባለፉት ዘመናት ውስጥ ለነበሩ አባቶች ክብር መሥጠት አቆሙ፡፡በመሆኑም ብዙ መልካምና ብርቅ ነገሮችን አጠናል፡፡ በስሕተት ጎዳና እየሄደ ያለ ማነው?ባለሥልጣናቱ ብቻ ናቸውን? አይደሉም፣ እኛም ራሳችን በስሕተት መንገድ ላይ ነን፣ ስለሆነምአሁን ራሳችን የዘራነውን እያጨድን ነው፡፡
“በምሁራኑ፣ በመኳንንቱ፣ በነጋዴዎችና በሲቪሉ ማኅበረ-ሰብ የተደረጉትን መጥፎምሳሌዎች እናስታውስ፡፡ እኛም በቤተ ክህነቱ ዘርፍ ያለን ሰዎች የበለጠ ክፉዎች ነበርን፡፡“የካህናቱ ልጆች አርቲስቶችና አብዮተኞች ሆኑ፣ የካህናቱ ቤተሰቦች አባቶቻቸው በየምክንያቱበመዋሸታቸው እምነት ስላጡባቸው ካህናቱን ከነሃይማኖታቸው ናቋቸው፡፡ ከአብዮቱ ረጅም ዓመታትአስቀድሞ ካህናቱ ለነፍስ ልጆቻቸው ታማኝ እረኞች አልነበሩም፡፡ ቅስና እንደማነኛውም የሙያ ዘርፍበመቆጠሩ ካህናቱ በሀልወተ-እግዚአብሔር የማያምኑና ከቤተ ክርስቲያን በሚገኘው ገንዘብ እየጠጡየመጠጥ ሱሰኞች ሆኑ፡፡
“ካገራችን ገዳማት መካከል አምስቱ ወይም ስድስቱ የክርስትና ማዕከሎች ነበሩ፤ የቫላምገዳም፣ ኦፕቲና ፑስቲን ከነታዋቂ መምህራኑ/ስተራርትሲx2 ፣ ዲቬዮቭስኪ ኮንቬንትና እንዲሁምየሳሮቭ ገዳም ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም ገዳማት አሁን እምነት-አልባ በመሆናቸው የሃይማኖተኛ መነኮሳትመገኛ ሳይሆኑ ተራ የማኅበረ-ሰብ መጠራቀሚያ ሆነዋል፡፡
“አሁን ሰዎች ከነዚህ ገዳማት ምን ይማራሉ? ምን ዓይነት ምሳሌ የሚሆን ነገርስ ተቀመጠ?“ልጆቻችንን በተገቢው መንገድ አላሳደግናቸውም፣ ጠንካራ የእምነት መሠረትአላስቀመጥንላቸውም፡፡ እንግዲህ ይህን ሁሉ ልብ በሉ! ለዚህ ነው ሰዎቻችን ፈጥነው ሁላችንንምየረሱን፣ ካህናቶቻቸውን ረስተዋል፣ እምነታቸውንና ቤተ ክርስቲያናቸውንም በመርሳት ለማፍረስቆርጠው ተነሡ፣ እንዲሁም የጥፋት ዘዴ በመቀመር ካህናቱ የጥፋት መሪዎች ሆኑ፡፡
“ይህን ሁሉ ልብ ካልነው ጣታችንን ወደባለሥልጣኖቻችን ብቻ አንቀስርም፣ ምክንያቱምየእምነት-አልባ ዘሮች ራሳችን ባዘጋጀነው አፈር ላይ ተዘሩ፡፡ ከዚያም እነዚያ ዘሮች ተራቡ፤ እናምመታሰርን፣ መሰቃየትን፣ የንጹሐንን ደም መፍሰስ አቆጠቆጡ፡፡ ይሁን እንጂ በሀገሬ ውስጥ የሆነውሁሉ ቢሆንም ዜጋዋ ነኝ፡፡ ካህን እንደመሆኔ መጠን ሀገራችንን የመጠበቅና የመርዳት ኃላፊነት(2):: እንዳለብን የነፍስ ልጆቼን እመክራለሁ፡፡ አሁን እየተፈጸመ ያለው መቆም አለበት፤ በፍጥነትመስተካከል ያለበት እጅግ ታላቅ ስሕተት ነው፡፡”
“ስለዚህ የኛዉ ቄሴም ኮሚ ሆንሃላ! አለ አንድ ሰው “ኮሚኒስት” የሚለውን ኮሚ ብሎበማሳጠር፡፡ ቅዱስ ትመስላለህ፣ ይሁን እንጂ አንተ በሁለት ቢላዋ የምትበላ አራጆ ነህ፣ ለካስ ቅስቀሳእያካሄድህ ነው! ለባለሥልጣናቱ እየሠራህ ነው!” አለና አባ አርሴኒን በመጥፎ ሁኔታ ገፍትሮከሚከራከረው ሕዝብ መከካከል አስወጣቸው፡፡
ክርክሩ በጦፈ ሁኔታ ቀጠለ፣ ነገር ግን ብዙ ሰዎች ቡድኑን እየተውት ወጡ፡፡
ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ትቂት እስረኞች አባ አርሴኒን መበቀል ጀመሩ፡፡ በምሸት ደበደቧቸው፣አንድ ሰው ባልጋቸው ላይ የፊኛዉን ፈሳሽ ለቀቀባቸው፣ ሌላዉም ደግሞ መቁኑናቸውንሠረቃቸው፡፡ እኛ የርሳቸው ጓደኞቻቸው ደግሞ ካጥቂዎቻቸው ለመታግ ሞከርን፡፡ ሆኖም ግን አጥቂቡድኖቹ አመለ-ብልሹዎች ስለነበሩ ማነኛውንም ጉዳት የማድረስ አቅሙ ነበራቸው፡፡ባንድ ምሸት ጆራ ግሪጎሬንኮ የሚባል ከኪየቭ የመጣ ሰው አባ አርሴኒን የቭላሶቭቲዎች መሪወደ ሆነው ጂሎቭስኪ ወሰዳቸው፣ ጂሎቭስኪ ካልጋዉ ላይ ተጋድሞ ከጓደኞቹ ጋር እያወራ ነበር፡፡“ቄሴ፣ ከኛ ወገን ነህን ወይስ ከኮሚኒስቶች? ለእስር ቤቱ ባለሥልጣናት እየሠራህ መሆኑንደርሰንብሃል፣ ኑዛዜ ትቀበልና አሳልፈህ ለነሱ ትሠጣለህ፡፡ አሁን ምን እንደምናደርግህ እኛ ብቻ ነንየምናውቅ፣ ትምህርት ሊሆንህ የሚችል ምት እንመታሃለን፡፡ እንሂድ ጆራ! በቅድሚያ ግን ቄሴየሚለውን እንስማ፡፡”
ጆራ ግሪጎሬንኮ በሁሉም ሰው ዘንድ የተጠላ ነበር፡፡ አጭር፣ ወፍራምና ትክሻዉ ሰፋ በማለቱአንገት የሌለው ይመስላል፣ ፊቱ ጠባሳ ስለበዛበት መልከ-ጥፉ ሲሆን በሆነ ባልሆነው የሐሰትፈገግታ ፈገግ ይላል፡፡ ይህ ተዳምሮ ሰውየውን አስቀያሚ አድርጎታል፡፡ ምንም እንኳን የቭላሶቭአባል በመሆኑ ብቻ በእስር ቤቱ ውስጥ ቢገኝም በጀርመን ሠራዊት ውስጥ በመረሸን ተግባር ላይየተሳተፈ ነው የሚል የሐሜት ወሬ ይወራበታል፡፡ አባ አርሴኒ በዕርጋታ ወደጂትሎቭስኪተመለከቱና “በሰዎች ሕይወት ላይ መወሰን የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ አንተ አይደለህም፡፡የአንተ ቡድን አባል አልሆንም፣” አሉት፡፡ ከዚያም ከጂትሎቭኪ በተቃራኒ ካልጋው ላይ ቁጭ አሉና“ልታስፈራራኝ አትሞክር፡፡ ለኡኡታ፣ ለድብደባና ለሞት ዛቻ ቤተሰቡ ነኝ፡፡ በዚህ ዓለም ላይየምኖረውን ጊዜና የእያንዳንዳችንን ዕድሜ በሚወስን በእግዚአብሔር ያለምንም ቅድመ-ሁኔታአምናለሁ፡፡ የምሞትበት ጊዜ አሁን ከሆነ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው፡፡ እኔም ሆንሁ አንተ ይህንመለወጥ አንችልም፡፡ ሁላችንም እንደሥራችን ሊፈረድብን ወደእግዚአብሔር ፍርድ መቅረባችንአይቀርም፡፡
“በእግዚአብሔርና በደጋግ ሰዎች መልካም ሥራ አምናለሁ፣ እስከመጨረሻዋ እስትንፋሴድረስ በዕርግጥም አምናለሁ፡፡ አንተስ? አምላክህ የት አለ? እምነትህስ የት አለ? ስለሚሳደዱትአሳዳጆች ብዙ ትናገራለህ፣ ነገር ግን እስካሁን ራስህ እያሳደድህ ነው፣ እያዋረድህና እየገደልህ ነው፡፡እጆችህን ተመልከት፣ በደም ተጨማልቀዋል!”
ጂትሎቭስኪ እጆቹን አነሣና በተለየ ሁኔታ አተኩሮ አያቸው፤ ከዚያም ወደአባ አርሴኒተመለከተ፡፡ እጆቹን ከጭኑ ላይ አሳረፋቸውና በጣቶቹ ሲጥጥ የሚል ድምፅ በፍጠር “ስለማላውቀውማነኛውም ነገር ለመናገር አትሞክር!” አለና አባ አርሴኒን እንደገና በጥልቀት ተመለከታቸው፡፡ግሪጎሬንኮ ከላይኛው ተደራቢ አልጋ ላይ ሆኖ “አርካዲ ሴሚዮኖቪች፣ ቄሴ በሃይማኖት በዐልየሚያስተምር ሰው ይመስላል፤ ለምን አሁን ገድለን አንገላገልም?” በማለት በብስጭት ተናገረ፡፡
“ዝም በል፣ ግሪንጎሬንኮ!” ሲለው መለሰና ጂትሎቭስኪ “ወደውስጥ ከማስገባታችን በፊትየሚለውን ሁሉ ይበል፡፡ ቄሶች ማነብነብ ሥራቸው ነው፣ ልክ እንደኮሞኒስት ካድሮዎች፣” አለ፡፡
አባ አርሴኒ ቀጠሉ፤ “አንድ ሰው አንድ ቀን አንተን ሃይማኖተኛ ነበረ አለኝ፣ ግን ለምንታምናለህ? ሰዎችን አሰቃይተህ የገደልህ በማን ስም ነው? ስለዶስቶቭስኪ--ስትናገር አስታውሳለሁ፣በጣም የምትወደው ደራሲና የሩስያውያን ነፍስ መሆኑን ተናግረሃል፤ “ዘ-ብራጊስ ካራማዞቭ”በተሰኘው መጽሐፉ የዞሲማን ቃለ-ምክር እጠቅሳለሁ፡፡ ከመሞቻ አልጋዉ ላይ ሆኖ በዙሪያዉከበውት ለነበሩ ሰዎች እንዲህ አለ፤ “ከሀድያንን፣ ክፋት የሚያስተምሩትን፣ ማቴሪያሊስቶችንናክፉዎችንም ሳይቀር አትጥሏቸው፣ ምክንያቱም ከእነርሱ መካከልም ትቂቶቹ በእውነት ርኅሩኆችአሉና፣ በተለይ ደግሞ በዘመናችን፡፡ የእግዚአብሔርን ሰዎች ውደዱ፡፡ እመኑና ታላቅ የእምነት ደረጃይኑራችሁ፡፡ ለሁሉም ሰዎች መልካም ሥሩ፣ ስቃዮቻቸውን በመሸከም ዕርዷቸው፡፡ እያንዳንዱ ሰውስለሕይወት እንደገና እንዲያስብና ስህተቱንም እንዲያርም ጊዜ አለው፣ ይህን ማድረግም ይገባዋል፡፡ይህን ከተናገሩ በኋላ አባ አርሴኒ ተነስተው ወደአልጋቸው አመሩ፡፡ ነገር ግን ግሪጎሬንኮከአልጋዉ ላይ ዘለለና አባ አርሴኒን አንገታቸውን አነቃቸው፡፡ በዚያ ቅጽበት በተሰበሰቡት ሰዎችመካከል አንድ ረጅምና ጠንካራ ሰውየ እየተጎማለለ ብቅ አለ፣ ይህ ሰው በእስር ቤቱ ውስጥ“መርከበኛዉ” በሚል ስም ይታወቃል፡፡ ኦዴሳ ላይ በፖለቲካ ምክንያት ተይዞ ለአስራ-አምስትዓመታት በዚህ እስር ቤት ውስጥ እንዲቆይ እስከተፈረደበት ጊዜ ድረስ በእርግትም መርከበኛ ነበር፡፡”ግዴለሽ፣ ደስተኛና ጥሩ ጀግና ሰው ነበር፣ እንደማናችንም በእስር ቤት ቢቆይም ጤናማ የሰውነትአቋሙን እንዳለ ነበር፡፡
መርከበኛዉን ከበው የሚመለከቱትን ሰዎች እየገፈተረ መጣና ግሪጎሬንኮን ያለማመንታትአነሣና በዕቃ እንደተሞላ ጆንያ ወደጂትሎቭስኪ ቡድን አባላት ወረወረው፡፡
“ስማ አንተ ምናምን! አሁን ሩስያ ውስጥ እንጂ ጀርመን ውስጥ አለመሆንህን ልታውቅይገባል!” አለና ወደጂትሎቭስኪ ዞሮ ያለማመንታት በኦዴስያኛ የአነጋገር ዘይቤ “የኔ ክቡር ሆይ፣ጓደኞችህን ፀጥ ብታሰኛቸው ይበጃሃል! ያለበለዚያ ማንቁርታችሁን እዘጋዋለሁ፡፡ ሁላችሁም ፀጥበሉ!”
የጂትሎቭስኪ ቡድን አባላት ተንቀጠቀጡ፤ ብዙ እስረኞችም መጡና አባ አርሴኒንናመርከበኛዉን ለማገዝ በተጠንቀቅ ቆሙ፡፡
መርከበኛዉ ወደግሪጎሬንኮ መጣና “ፒዮትር አንድሬየቪችን መንካት አትችልም! አንድ ነገር ቢሆኑእኔ በግሌ ስለእርሳቸው እገድላሃለሁ፣ ከመግደሌ በፊት ስስ ብልትህን መትቼ በመጣልእጫወትብሃለሁ፣” አለው፡፡ ከዚያም አባ አርሴኒን ጠራቸውና “ፒዮትር አንድሬቪች፣ እንሂድ! አሁንአስጨንቀናቸዋል፡፡ ለእርስዎ የተለየ አክብሮት አለኝ፡፡ በሰላም ደግመን እንደምንገናኝ ተስፋአደርጋለሁ፡፡”
በሦስት ሳምንታት ውስጥ ጆራ ግሪጎሬንኮ ወደሌላ እስር ቤት ተዛወረ፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮጂትሎቭስኪዎች ፀጥ አሉ፣ ለሰዎችም ከበሬታ ማሳየት ጀመሩ፡፡ ክርክሩ ግን እንደቀጠለ ነበር፣ አባአርሴኒ ግን ከዚያ ጊዜ ጀመሮ በክርክር መሳተፋቸውን አቆሙ፡፡
(1) ቭላሶቨትስ በጄነራል ቭላሶቭ ስር ይታዘዙ የነበሩ ሩስያውያውን ወታደሮች ሲሆኑ ከውጭ ሆነው ኮሚኒዝምን ለመዋጋትከጀርመን ጦር ሠራዊት ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ጦርነቱ በጀርመኖች ተሸናፊነት በመደምደሙ በመጨረሻ በጦር ቃል-ኪዳን ተባባሪሀገራት ወደሩስያ እንዲመለሱ ተደረገና ከሞላ-ጎደል ሁሉም ሲሰቀሉ የቀሩት ደግሞ ወደልዩ የሞት ካምፕ ተላኩ፡፡
(2) ስተራርትስ “ስታሬትዝ” ለሚለው ቃል የብዙ ቁጥር ሲሆን ትርጉሙ ሰዎች ሃይማኖታዊ ምክር ለማግኘት የሚሄዱበትታዋቂ መምህር ማለት ነው፡፡ የኦፕቲና ገዳም እንደነዚህ ዐይነት መምህራንን በማፍራት የታወቀ ነው፡፡
በመጀመሪያ ወደ እስር ቤት ስትገባ ቀናትን ትቆጥራለህ፣ ከዚያም ሳምንታትን፣ ከሁለትዓመታት በኋላ በሚመጣዉ ጊዜ የምታደርገው ሞትን መጠበቅ ብቻ ነው፡፡ አድካሚ የጉልበት ሥራ፣መራራ ረሐብ፣ እርስ በእርስ መናቆር፣ መደባደብ፣ ብርዱና ከቤተ-ሰብ መለየቱ ያደድቡህናየማይቀረውን ሞት ብቻ እንድታስብ ትሆናለህ፡፡ ስለዚህ አብዛኛዎቹ እስረኞች በስነ-ምግባር ረገድደካሞች የሚሆኑት፡፡
ለብዙዎቻችን የፖለቲካና ለሁሉም የወንጀለኛ እስረኞች ስሜታችን እንደ ሁኔታዉ ግራና ቀኝየሚዋልል ነበር፣ የአለቃው ቁጥጥር፣ የሚሠረቅ ዳቦ፣ እርስ በእርስ መናቆር፣ በተለይ በእስር ቤቱለተመደቡ እስረኞች የተመደበው እጅግ ከባድ የጉልበት ሥራ፣ ልዩዉ የቅጣት ክፍል፣ በረዶየሚሆኑ ጣቶች ወይም በጎረቤት የእስር ቤቱ ክፍሎች ውስጥ የሚሞቱት እስረኞች ስሜትንለመቀያየር ምክንያቶች ነበሩ፡፡ ሐሳብህ ሁሉ ተራና በእነዚህ ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ይሆናሉ፡፡ እጅግበጣም የአያሌዎቹ እስረኞች ሕልም እስከሚጠግቡ በልተው ለሁለት ወይም ለሦስት ሰዓታት ያህልመተኛት ወይም ግማሽ ሊትር ቮድካ አግኝተው ሁሉንም ጨልጠው እንደገና ሌላ ተጨማሪ ምግብቢሰለቅጡ በወደዱ ነበር፣ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ባዶ ምኞቶች ብቻ ነበሩ፡፡
እጅግ በጣም ትቂት የፖለቲካ እስረኞች በተቻላቸው መጠን ርኅሩኅ ሆነው ለመቆየት ሞከሩ፣ራሳቸውንም ከሌላዉ በመለየት፣ እርስ በእርስ በመደጋገፍና ራሳቸውን ወደ ተራ የወንጀለኛ እስረኞችዝቅ ላለማድረግ እየጣሩ ነበር፡፡ በተቻላቸው መጠን የእስር ቤቱ ደንብ በሚፈቅደው መሠረትራሳቸውን በማያዋርድ ሁኔታ ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከእስር ቤቱ የበረንዳ ማዕዘን ላይ ቆመውቃለ-ተናብቦ/ሌክቸር ያደርጋሉ፣ ግጥም ወይም አጭር ሳይንስ-ነክ ጽሑፍ ያነባሉ፣ አልፎ አልፎምየትም ባገኙት ብጣሽ ወረቀት ሳይቀር ማስታዎሻ ይጽፋሉ፡፡ በሆነ ርእሰ-ጉዳይ ላይ ሞቅ ያለ ክርክርይነሣል፣ ይሁን እንጂ እጅግ በጣም የሚጦፈው ፖለቲካን አስመልክቶ የሚደረገው ክርክር ነበር፡፡አልፎ አልፎ የወንጀል እስረኞችም ሳይቀር በክርክሩ ይቀላቀሉ ነበር፤ ፖለቲከኞች በፖለቲካ ረገድብዙም ፍላጎት አይታይባቸውም፣ ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ፍላጎቱ ነበራቸው፡፡ ሰዎች በስሜትየሚቃወሟቸውን በጥላቻ ይከራከሯቸው ነበር፡፡ አባ አርሴኒ በዚህ ክርከር ፈጽመው አይሳተፉም፡፡ነገር ግን ከዕለታት አንድ ቀን ያለፍላጎታቸው ተጎትተው ገቡ፡፡
ምንም ጊዜም እስረኞች ሐሳባቸውን ለመግለጽ ይፈራሉ፣ ይሁን እንጂ ወደሞቀ ክርክርውስጥ ሲገቡ ፍርሃት ሊያስከትል የሚችለውን ነገር ሁሉ ይረሱታል፡፡ በክርክሩ ከሚሳተፉት መካከልትቂቶቹ የአሰብሁትን መናገር ሳልችል ድምፄ ታፈነ፣” ይላሉ፡፡
እስረኞች ተቆጥረው የእስር ቤቱ በሮች ተቆለፉ፣ ከግድግዳዉ በስተጀርባ ነፋሱ እየነፈሰነበር፤ ግግሩ በረዶ መስኮቶችን እንዳይከፈቱ አደረጋቸው፣ ክፍሉ የታፈነና ዕርጥበት-አዘል ነበር፣ሆኖም ግን ውስጡ ሞቃት ነው፡፡ አምፖሎቹ ከሚፈለገው ከግማሽ በታች ብርሃናቸው መጠን ባነሰያበሩ ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ትካዜና ሐዘን እንዲኖር ያደርጋሉ፡፡ በመሆኑም ሰዎች ብቸኛ ይሆናሉ፡፡እስረኞቹ በአንድነት ተሰበስበው መነጋገር፣መከራከርና ያለፈውን ማስታወስ ጀመሩ፡፡ ወንጀለኛእስረኞች ካርድ ወይም እንዶሚኖ ለብር ወይም ለመቁኑን እየተጫወቱ ነበር፡፡ አባ አርሴኒ ካረፉበትአልጋ አጠገብ የተሰበሰቡ እስረኞች በመንግሥት ላይ ያላቸውን አመለካከት ርእሰ-ጉዳይ በማድረግኃይለኛ ክርክር አደረጉ፡፡ በ15 ደቂቃዎች ውስጥ 20 የሚሆኑ ሰዎች ወደ ክርክሩ ተቀላቀሉና ክርክሩጦፈ፡፡ አንዱ የአንዱን ንግግር በማቋረጥ ሥጋት ጨመረ፡፡ ከተከራካሪዎች መካከል ቀድሞ የፓርቲአባል የነበሩ፤ ከልዩ ልዩ የሕይወት ተሞክሮዎች የተማሩ ሰዎች፤ በጣም ትቂት ቭላስቶቭትሲዎችናx1ሌሎችም ነበሩ፡፡ “እዚህ ያለነው ለምድነው? ለምንም! ፍትሕ የት አለ? ሁሉም መረሸን አለባቸው!”በማለት ፊታቸውን አኮሳትረው ይጮሁ፡፡ አራት ወይም አምስት የሚሆኑ ቀድሞ የፓርቲ አባልየነበሩ በነገሩ ባለስማማታቸው “አሳዛኝ ስሕተት እየተፈጸመ ነው” በማለት ገለጹ፡፡ እንደአበባላቸውከሆነ እየሆነ ያለው ሁሉ እራሱ ስታሊን በማያውቀው በትቂት ሠርጎ-ገቦች በመሞኘት የሚፈጸምመሆኑን ገለጹ፡፡
“የሩስያ ሕዝብ ግማሹ በእስር ቤት ታጉሮ ሳለ ተታለልን! አስተዳዳሪዎቹም እንዲደመሰሱታቀደ!” በማለት አንድ ድምፅ ጮኸ፡፡
ስታሊን አሳምሮ ያውቃል፣ የራሱ ትእዛዝ ነው፣” አለ ሌላዉ፡፡
ስታሊንን በመግደል አሲርሃል ተብሎ የተያዘው ከስረኞቹ አንዱ እጅግ በጣም በመበሳጨቱድምፁ ተቆራረጠ፡፡ ትቂት ቭላስቭትስኪዎች ማነኛውንም ሐሳብና በመቃወም ጮኹ፡፡
“እነዚያ የፓርቲ አባላት መሰቀል ወይም መረሸን አለባቸው!” አለ ሌላ አንድ ሰው፡፡ከ1917 ዓ/ም ጀምሮ ዋና የቮልሼቪክ ፓርቲ አባል የነበረ አንድ ሽማግሌ ሰው በመጀርመንጦር ሠራዊት ውስጥ ካገለገለ ሰው ጋር ተደባደበና በኃይል መሳደብ፡፡
“አንተ ባንዳ ነህ!” ብሎ ጮኸ፡፡ “መረሸን ነበረብህ፣ ነገር ግን በሕይወት እስካሁን አለህ! እኔራሴ እንዳተ ያሉትን ባንዳዎች እረሽናቸዋለሁ ወይም እሰቅላቸዋለሁ፡፡ እስካሁን ድረስ ወደናንተባለመዝቴ አዝናለሁ፡፡ ስሕተትም ፈጽሜያለሁ፣ ይሁን እንጂ አንተ ባንዳዉ በዚህ እስር ቤት ውስጥከኔ ጋር ትሞታለህ ብየ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
“እኔ ባንዳ ነኝ? እኔ የሶቭየትን መንግሥት ከሚደግፉት አንዱ ነኝ!” “ማለት ትችላለህ፣ ነገር ግን አንተም ባንዳ ነህ፣ ለዚህ ነው መንግሥት እዚህ እስር ቤትያመጣህ፡፡”
በርቀት የነበሩ ሰዎች ሳቁ፣ ሆኖም ግን ክርክሩ በሞቀ ሁኔታ ቀጠለ፡፡ አንድ ሰው ድንገት“አብያተ ክርስቲያናትን አውድመው ሃይማኖትን አጠፉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ሰው ካጠገቡ ቁጭ(1) ያሉትን አባ አርሴኒን አስታወሰና “ደህና፣ ፒዮትር አንድሬየቪች ንገረን፣ ባለሥልጣናቱን እንዴትታያቸዋለህ?” ሲል ጠየቀ፡፡
አባ አርሴኒ ዝም ብለው ክርክሩን ሲያዳምጡ ቆዩ፣ ነገር ግን አሁን ያለፍላጎታቸው ወደክርክሩ ጎትተው ከተቷቸው፡፡ አባ አርሴኒ ምን እንደሚመልሱ ግልጽ ነበር፡፡ በእስር ቤቱ ውስጥ ብዙየተሰቃዩ ሰው ስለነበሩ የአባ አርሴኒ ጓደኞች ተጨነቁ፡፡
በጂትሎቭስኪ የሚመሩት ቭላስቭትሲዎች ከሌላዉ እስረኛ ራሳቸውን አግለው እየኖሩ ነበር፡፡የሚፈሩት ምንም ነገር አልነበረም፤ በምን ምክንያት እንደተያዙ ያውቃሉ፣ የሕይወታቸው ፍጻሜምቅርብ እንደሆም ይገምታሉ፡፡ ከነርሱ አንዱ “እንግዲህ በል አፍስሰው ቄሴ!” አለ፡፡
አባ አርሴኒ ላፍታ ዝም አሉና “የጦፈ ክርክር ስለያዛችሁ ክርክሩ ወደ ጭቅጭቅ ተቀየረ፣ሊትቆጣጠሩት ወደማትችሉት ደረጃ ደረሰ፡፡ በእስር ቤት መኖር አስቸጋሪ እየሆነ በመምጣቱሁላችንም ፍጻሜያችን ምን እንደሚሆን እናውቃለን፡፡ ክርክሩም መራራ የሆነው ለዚህ ነው፡፡የማይረሸን ወይም በሕይወት የሚተርፍ የለም፡፡ ሁላችሁም ባለሥልጣናቱን፣ ትእዛዛቱንና ሰዎችንትዎነጅላላችሁ፤ ሌላውን ለማስቆጣት ጎትታችሁ ወደ ክርክሩ አስገባችሁኝ፡፡
“ኮሚኒስቶች ምዕመናንን አስረዋል፣ አብያተ ክርስቲያናትን ዘግተዋል፣ ሃይማኖትን ትተዋልብላችኋል፡፡ አዎ፣ ላዩን ሲታይ እውነት ይመስላል፤ ነገር ግን እስቲ በጥልቀት እንመልከተው፣ያለፉትን ጊዜያት በጥልቀት እንመልከት፡፡ ከኛ ከሩስያውያውን ሕዝቦች መካከል ብዙዎቹሃይማኖታቸውን ክደዋል፣ ባለፉት ዘመናት ውስጥ ለነበሩ አባቶች ክብር መሥጠት አቆሙ፡፡በመሆኑም ብዙ መልካምና ብርቅ ነገሮችን አጠናል፡፡ በስሕተት ጎዳና እየሄደ ያለ ማነው?ባለሥልጣናቱ ብቻ ናቸውን? አይደሉም፣ እኛም ራሳችን በስሕተት መንገድ ላይ ነን፣ ስለሆነምአሁን ራሳችን የዘራነውን እያጨድን ነው፡፡
“በምሁራኑ፣ በመኳንንቱ፣ በነጋዴዎችና በሲቪሉ ማኅበረ-ሰብ የተደረጉትን መጥፎምሳሌዎች እናስታውስ፡፡ እኛም በቤተ ክህነቱ ዘርፍ ያለን ሰዎች የበለጠ ክፉዎች ነበርን፡፡“የካህናቱ ልጆች አርቲስቶችና አብዮተኞች ሆኑ፣ የካህናቱ ቤተሰቦች አባቶቻቸው በየምክንያቱበመዋሸታቸው እምነት ስላጡባቸው ካህናቱን ከነሃይማኖታቸው ናቋቸው፡፡ ከአብዮቱ ረጅም ዓመታትአስቀድሞ ካህናቱ ለነፍስ ልጆቻቸው ታማኝ እረኞች አልነበሩም፡፡ ቅስና እንደማነኛውም የሙያ ዘርፍበመቆጠሩ ካህናቱ በሀልወተ-እግዚአብሔር የማያምኑና ከቤተ ክርስቲያን በሚገኘው ገንዘብ እየጠጡየመጠጥ ሱሰኞች ሆኑ፡፡
“ካገራችን ገዳማት መካከል አምስቱ ወይም ስድስቱ የክርስትና ማዕከሎች ነበሩ፤ የቫላምገዳም፣ ኦፕቲና ፑስቲን ከነታዋቂ መምህራኑ/ስተራርትሲx2 ፣ ዲቬዮቭስኪ ኮንቬንትና እንዲሁምየሳሮቭ ገዳም ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም ገዳማት አሁን እምነት-አልባ በመሆናቸው የሃይማኖተኛ መነኮሳትመገኛ ሳይሆኑ ተራ የማኅበረ-ሰብ መጠራቀሚያ ሆነዋል፡፡
“አሁን ሰዎች ከነዚህ ገዳማት ምን ይማራሉ? ምን ዓይነት ምሳሌ የሚሆን ነገርስ ተቀመጠ?“ልጆቻችንን በተገቢው መንገድ አላሳደግናቸውም፣ ጠንካራ የእምነት መሠረትአላስቀመጥንላቸውም፡፡ እንግዲህ ይህን ሁሉ ልብ በሉ! ለዚህ ነው ሰዎቻችን ፈጥነው ሁላችንንምየረሱን፣ ካህናቶቻቸውን ረስተዋል፣ እምነታቸውንና ቤተ ክርስቲያናቸውንም በመርሳት ለማፍረስቆርጠው ተነሡ፣ እንዲሁም የጥፋት ዘዴ በመቀመር ካህናቱ የጥፋት መሪዎች ሆኑ፡፡
“ይህን ሁሉ ልብ ካልነው ጣታችንን ወደባለሥልጣኖቻችን ብቻ አንቀስርም፣ ምክንያቱምየእምነት-አልባ ዘሮች ራሳችን ባዘጋጀነው አፈር ላይ ተዘሩ፡፡ ከዚያም እነዚያ ዘሮች ተራቡ፤ እናምመታሰርን፣ መሰቃየትን፣ የንጹሐንን ደም መፍሰስ አቆጠቆጡ፡፡ ይሁን እንጂ በሀገሬ ውስጥ የሆነውሁሉ ቢሆንም ዜጋዋ ነኝ፡፡ ካህን እንደመሆኔ መጠን ሀገራችንን የመጠበቅና የመርዳት ኃላፊነት(2):: እንዳለብን የነፍስ ልጆቼን እመክራለሁ፡፡ አሁን እየተፈጸመ ያለው መቆም አለበት፤ በፍጥነትመስተካከል ያለበት እጅግ ታላቅ ስሕተት ነው፡፡”
“ስለዚህ የኛዉ ቄሴም ኮሚ ሆንሃላ! አለ አንድ ሰው “ኮሚኒስት” የሚለውን ኮሚ ብሎበማሳጠር፡፡ ቅዱስ ትመስላለህ፣ ይሁን እንጂ አንተ በሁለት ቢላዋ የምትበላ አራጆ ነህ፣ ለካስ ቅስቀሳእያካሄድህ ነው! ለባለሥልጣናቱ እየሠራህ ነው!” አለና አባ አርሴኒን በመጥፎ ሁኔታ ገፍትሮከሚከራከረው ሕዝብ መከካከል አስወጣቸው፡፡
ክርክሩ በጦፈ ሁኔታ ቀጠለ፣ ነገር ግን ብዙ ሰዎች ቡድኑን እየተውት ወጡ፡፡
ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ትቂት እስረኞች አባ አርሴኒን መበቀል ጀመሩ፡፡ በምሸት ደበደቧቸው፣አንድ ሰው ባልጋቸው ላይ የፊኛዉን ፈሳሽ ለቀቀባቸው፣ ሌላዉም ደግሞ መቁኑናቸውንሠረቃቸው፡፡ እኛ የርሳቸው ጓደኞቻቸው ደግሞ ካጥቂዎቻቸው ለመታግ ሞከርን፡፡ ሆኖም ግን አጥቂቡድኖቹ አመለ-ብልሹዎች ስለነበሩ ማነኛውንም ጉዳት የማድረስ አቅሙ ነበራቸው፡፡ባንድ ምሸት ጆራ ግሪጎሬንኮ የሚባል ከኪየቭ የመጣ ሰው አባ አርሴኒን የቭላሶቭቲዎች መሪወደ ሆነው ጂሎቭስኪ ወሰዳቸው፣ ጂሎቭስኪ ካልጋዉ ላይ ተጋድሞ ከጓደኞቹ ጋር እያወራ ነበር፡፡“ቄሴ፣ ከኛ ወገን ነህን ወይስ ከኮሚኒስቶች? ለእስር ቤቱ ባለሥልጣናት እየሠራህ መሆኑንደርሰንብሃል፣ ኑዛዜ ትቀበልና አሳልፈህ ለነሱ ትሠጣለህ፡፡ አሁን ምን እንደምናደርግህ እኛ ብቻ ነንየምናውቅ፣ ትምህርት ሊሆንህ የሚችል ምት እንመታሃለን፡፡ እንሂድ ጆራ! በቅድሚያ ግን ቄሴየሚለውን እንስማ፡፡”
ጆራ ግሪጎሬንኮ በሁሉም ሰው ዘንድ የተጠላ ነበር፡፡ አጭር፣ ወፍራምና ትክሻዉ ሰፋ በማለቱአንገት የሌለው ይመስላል፣ ፊቱ ጠባሳ ስለበዛበት መልከ-ጥፉ ሲሆን በሆነ ባልሆነው የሐሰትፈገግታ ፈገግ ይላል፡፡ ይህ ተዳምሮ ሰውየውን አስቀያሚ አድርጎታል፡፡ ምንም እንኳን የቭላሶቭአባል በመሆኑ ብቻ በእስር ቤቱ ውስጥ ቢገኝም በጀርመን ሠራዊት ውስጥ በመረሸን ተግባር ላይየተሳተፈ ነው የሚል የሐሜት ወሬ ይወራበታል፡፡ አባ አርሴኒ በዕርጋታ ወደጂትሎቭስኪተመለከቱና “በሰዎች ሕይወት ላይ መወሰን የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ አንተ አይደለህም፡፡የአንተ ቡድን አባል አልሆንም፣” አሉት፡፡ ከዚያም ከጂትሎቭኪ በተቃራኒ ካልጋው ላይ ቁጭ አሉና“ልታስፈራራኝ አትሞክር፡፡ ለኡኡታ፣ ለድብደባና ለሞት ዛቻ ቤተሰቡ ነኝ፡፡ በዚህ ዓለም ላይየምኖረውን ጊዜና የእያንዳንዳችንን ዕድሜ በሚወስን በእግዚአብሔር ያለምንም ቅድመ-ሁኔታአምናለሁ፡፡ የምሞትበት ጊዜ አሁን ከሆነ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው፡፡ እኔም ሆንሁ አንተ ይህንመለወጥ አንችልም፡፡ ሁላችንም እንደሥራችን ሊፈረድብን ወደእግዚአብሔር ፍርድ መቅረባችንአይቀርም፡፡
“በእግዚአብሔርና በደጋግ ሰዎች መልካም ሥራ አምናለሁ፣ እስከመጨረሻዋ እስትንፋሴድረስ በዕርግጥም አምናለሁ፡፡ አንተስ? አምላክህ የት አለ? እምነትህስ የት አለ? ስለሚሳደዱትአሳዳጆች ብዙ ትናገራለህ፣ ነገር ግን እስካሁን ራስህ እያሳደድህ ነው፣ እያዋረድህና እየገደልህ ነው፡፡እጆችህን ተመልከት፣ በደም ተጨማልቀዋል!”
ጂትሎቭስኪ እጆቹን አነሣና በተለየ ሁኔታ አተኩሮ አያቸው፤ ከዚያም ወደአባ አርሴኒተመለከተ፡፡ እጆቹን ከጭኑ ላይ አሳረፋቸውና በጣቶቹ ሲጥጥ የሚል ድምፅ በፍጠር “ስለማላውቀውማነኛውም ነገር ለመናገር አትሞክር!” አለና አባ አርሴኒን እንደገና በጥልቀት ተመለከታቸው፡፡ግሪጎሬንኮ ከላይኛው ተደራቢ አልጋ ላይ ሆኖ “አርካዲ ሴሚዮኖቪች፣ ቄሴ በሃይማኖት በዐልየሚያስተምር ሰው ይመስላል፤ ለምን አሁን ገድለን አንገላገልም?” በማለት በብስጭት ተናገረ፡፡
“ዝም በል፣ ግሪንጎሬንኮ!” ሲለው መለሰና ጂትሎቭስኪ “ወደውስጥ ከማስገባታችን በፊትየሚለውን ሁሉ ይበል፡፡ ቄሶች ማነብነብ ሥራቸው ነው፣ ልክ እንደኮሞኒስት ካድሮዎች፣” አለ፡፡
አባ አርሴኒ ቀጠሉ፤ “አንድ ሰው አንድ ቀን አንተን ሃይማኖተኛ ነበረ አለኝ፣ ግን ለምንታምናለህ? ሰዎችን አሰቃይተህ የገደልህ በማን ስም ነው? ስለዶስቶቭስኪ--ስትናገር አስታውሳለሁ፣በጣም የምትወደው ደራሲና የሩስያውያን ነፍስ መሆኑን ተናግረሃል፤ “ዘ-ብራጊስ ካራማዞቭ”በተሰኘው መጽሐፉ የዞሲማን ቃለ-ምክር እጠቅሳለሁ፡፡ ከመሞቻ አልጋዉ ላይ ሆኖ በዙሪያዉከበውት ለነበሩ ሰዎች እንዲህ አለ፤ “ከሀድያንን፣ ክፋት የሚያስተምሩትን፣ ማቴሪያሊስቶችንናክፉዎችንም ሳይቀር አትጥሏቸው፣ ምክንያቱም ከእነርሱ መካከልም ትቂቶቹ በእውነት ርኅሩኆችአሉና፣ በተለይ ደግሞ በዘመናችን፡፡ የእግዚአብሔርን ሰዎች ውደዱ፡፡ እመኑና ታላቅ የእምነት ደረጃይኑራችሁ፡፡ ለሁሉም ሰዎች መልካም ሥሩ፣ ስቃዮቻቸውን በመሸከም ዕርዷቸው፡፡ እያንዳንዱ ሰውስለሕይወት እንደገና እንዲያስብና ስህተቱንም እንዲያርም ጊዜ አለው፣ ይህን ማድረግም ይገባዋል፡፡ይህን ከተናገሩ በኋላ አባ አርሴኒ ተነስተው ወደአልጋቸው አመሩ፡፡ ነገር ግን ግሪጎሬንኮከአልጋዉ ላይ ዘለለና አባ አርሴኒን አንገታቸውን አነቃቸው፡፡ በዚያ ቅጽበት በተሰበሰቡት ሰዎችመካከል አንድ ረጅምና ጠንካራ ሰውየ እየተጎማለለ ብቅ አለ፣ ይህ ሰው በእስር ቤቱ ውስጥ“መርከበኛዉ” በሚል ስም ይታወቃል፡፡ ኦዴሳ ላይ በፖለቲካ ምክንያት ተይዞ ለአስራ-አምስትዓመታት በዚህ እስር ቤት ውስጥ እንዲቆይ እስከተፈረደበት ጊዜ ድረስ በእርግትም መርከበኛ ነበር፡፡”ግዴለሽ፣ ደስተኛና ጥሩ ጀግና ሰው ነበር፣ እንደማናችንም በእስር ቤት ቢቆይም ጤናማ የሰውነትአቋሙን እንዳለ ነበር፡፡
መርከበኛዉን ከበው የሚመለከቱትን ሰዎች እየገፈተረ መጣና ግሪጎሬንኮን ያለማመንታትአነሣና በዕቃ እንደተሞላ ጆንያ ወደጂትሎቭስኪ ቡድን አባላት ወረወረው፡፡
“ስማ አንተ ምናምን! አሁን ሩስያ ውስጥ እንጂ ጀርመን ውስጥ አለመሆንህን ልታውቅይገባል!” አለና ወደጂትሎቭስኪ ዞሮ ያለማመንታት በኦዴስያኛ የአነጋገር ዘይቤ “የኔ ክቡር ሆይ፣ጓደኞችህን ፀጥ ብታሰኛቸው ይበጃሃል! ያለበለዚያ ማንቁርታችሁን እዘጋዋለሁ፡፡ ሁላችሁም ፀጥበሉ!”
የጂትሎቭስኪ ቡድን አባላት ተንቀጠቀጡ፤ ብዙ እስረኞችም መጡና አባ አርሴኒንናመርከበኛዉን ለማገዝ በተጠንቀቅ ቆሙ፡፡
መርከበኛዉ ወደግሪጎሬንኮ መጣና “ፒዮትር አንድሬየቪችን መንካት አትችልም! አንድ ነገር ቢሆኑእኔ በግሌ ስለእርሳቸው እገድላሃለሁ፣ ከመግደሌ በፊት ስስ ብልትህን መትቼ በመጣልእጫወትብሃለሁ፣” አለው፡፡ ከዚያም አባ አርሴኒን ጠራቸውና “ፒዮትር አንድሬቪች፣ እንሂድ! አሁንአስጨንቀናቸዋል፡፡ ለእርስዎ የተለየ አክብሮት አለኝ፡፡ በሰላም ደግመን እንደምንገናኝ ተስፋአደርጋለሁ፡፡”
በሦስት ሳምንታት ውስጥ ጆራ ግሪጎሬንኮ ወደሌላ እስር ቤት ተዛወረ፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮጂትሎቭስኪዎች ፀጥ አሉ፣ ለሰዎችም ከበሬታ ማሳየት ጀመሩ፡፡ ክርክሩ ግን እንደቀጠለ ነበር፣ አባአርሴኒ ግን ከዚያ ጊዜ ጀመሮ በክርክር መሳተፋቸውን አቆሙ፡፡
(1) ቭላሶቨትስ በጄነራል ቭላሶቭ ስር ይታዘዙ የነበሩ ሩስያውያውን ወታደሮች ሲሆኑ ከውጭ ሆነው ኮሚኒዝምን ለመዋጋትከጀርመን ጦር ሠራዊት ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ጦርነቱ በጀርመኖች ተሸናፊነት በመደምደሙ በመጨረሻ በጦር ቃል-ኪዳን ተባባሪሀገራት ወደሩስያ እንዲመለሱ ተደረገና ከሞላ-ጎደል ሁሉም ሲሰቀሉ የቀሩት ደግሞ ወደልዩ የሞት ካምፕ ተላኩ፡፡
(2) ስተራርትስ “ስታሬትዝ” ለሚለው ቃል የብዙ ቁጥር ሲሆን ትርጉሙ ሰዎች ሃይማኖታዊ ምክር ለማግኘት የሚሄዱበትታዋቂ መምህር ማለት ነው፡፡ የኦፕቲና ገዳም እንደነዚህ ዐይነት መምህራንን በማፍራት የታወቀ ነው፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)