ኢሳት ለበርካታ ስዓት ስለ የታፈሱ የአዲስ አበባ «ወጣቶች» ዜና እና አስተያየት እያቀረበ ነው (https://www.youtube.com/watch?v=4KugoBLSfFY)።
እኔ እስካየሁት ድረስ ኢሳት አንዲት ደቂቃ ስለ መሰረታዊ ችግሩ ውይይት አላቀረበም። መሰረታዊ ችግሩ የአዲስ አበባ ህዝብ እና በመላው ኢትዮጵያ በኢትዮጵያዊነት የምናምነው የኢትዮጵያ ብሄርተኞች በበቂ ደረጃ አለመደራጀታችን ነው።
አስቡት… የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ አንዳች ይሄ ነው የሚባል ህዝብ ወኪል ተቋም የለውም! ይህ ነው ጉዱ።
ይህን ጉድ አምነን ወደ መፍትሄ ከመሄድ ወደ መደራጀት ከመሄድ ጊዜአችንን «በለቅሶ ፖለቲካ» እናጠፋለን። እንደ ክብር የሌለን ሰዎች የራሳችን ገበና ሳናስተካክል ሌሎችን «አትግዱን» ብለን 24 ሰዓት እንለምናለን። በራሳችን ድክመት ስለምናፍር ይመስለኛል ሁል ጊዜ ጣታችንን ወደ ሌሎች የምንጠቁመው። እነሱ ደግሞ እኛ እራሳችንን ካላልጎለበትን ምንም አያደርጉልንም።
አንድ ምሁራን እንዲህ ብልዋል፤ “When people realize things are going wrong, there are two questions they can ask. One is, ‘What did we do wrong?’ and the other is, ‘Who did this to us?’ The latter leads to conspiracy theories and paranoia. The first question leads to another line of thinking: ‘How do we put it right?’”
የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምሁራን እና ልሂቃን አሁንም «ማን ነው የሚያጠቃን» የሚለው ላይ ነን። በጃንሆይ ዘመን በ«አለመተባበር ብሽታችን» ምክንያት በየቀኑ ለዳኝነት ወደ ጃንሆይ እንሄድ ነበር። ከዛ አድሃሪ/ተራማጅ እየተባባልን ተገዳደልን። የተረፉት «አድሃሪዎቹም» ኢዲዩ መስርተው አብሮ መስራት አቅቷቸው ፈራረሱ። ማርክሲስቶቹ ከመተባበር እርስ በርስ ተፋጁ። ኢህአዴግ ስልጣን ሲይዝ እራሳችንን «ተቃዋሚ» ብለን ሰይመን ይሄ ነው የሚባል ተቋም ማደራጀት አቃተን። ወዘተ። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ደጋግሞ መውደቅ ረዥም ታሪክ ነው። ግን አሁንም ይህን ድምከት ላይ ከማተኮር ይልቅ ሌሎችን እባካችሁን አድኑን ብለን እንለምናለን!
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label victim mentality. Show all posts
Showing posts with label victim mentality. Show all posts
Tuesday, 16 October 2018
Thursday, 11 October 2018
መልዕክት ለኢሳቶች…
አቤቱታ፤ ማማረር፤ ማልቀስ፤ complaining ህዝብን ተስፋ እንዲቆርት ያደርጋል። ይህ ከኢሳት ተዕልኮ የሚጻረር ነው።
እንደ አንድ ተራ ዜጋ ምክሬ እንዲህ ነው፤ ስለ ችግሮች ለ10 ደቂቃ ካወራችሁ ስለ መፍትሄ እና አማራጭ መንገዶች ለ20 ደቂቃ ተወያዩ። አዋጪው መንገድ ይህ ይመስለኛል።
እንደ አንድ ተራ ዜጋ ምክሬ እንዲህ ነው፤ ስለ ችግሮች ለ10 ደቂቃ ካወራችሁ ስለ መፍትሄ እና አማራጭ መንገዶች ለ20 ደቂቃ ተወያዩ። አዋጪው መንገድ ይህ ይመስለኛል።
Tuesday, 18 September 2018
ኦኤምኤንን ከመክሰስ ሌላ ሚዲያ አቋቁመን እንብለጠው
በርካታ ጽሁፎቼ ስ«ለሃላፊነት» መውሰድ ነው። የሰው ልጅ ችግሮች ሲያጋጥሙን ሌሎችን ከመውቀስ እኛ ምን ብናደርግ ነው፤ ምን ብንሳሳት ነው፤ ምን ቀድሞ ዝግጅት ባናደርግ ነው ብለን እራሳችንን መጠየቅ አለብን። በዚህ አካሄድ ብቻ ነው ችግሮቻችንን መፍታት የምንችለው።
ሌሎችን መውቀሱ ዋጋ የለውም። ለምን ብትሉ ችግርን የሚፈጥሩ ሰዎች አውቀው የሚያደርጉት ከሆነ የኛ እነሱን መውቀስ በሃሪና ተግባራቸውን አይቀየርም። ይቀየራሉ ብለን ስንጠብቅ ችግሮቻችንን እያባባሱ ይቀጥላሉ! እኛ እየተጠቃን እንቀጥላለን። በራሳችን ያለን መተማመን እየቀነሰ ይሄዳል። የሰለባ አስተሳሰብ (victim mentality) እና የዝቅተኝነት መንፈስ (inferiority complex) እያደረግን እየጠነከረብን እንሄዳለን። አሉንታዊ እና ብሶታዊ ሰዎች እንሆናለን።
ግን ችግር ሲያጋጥመን ሃላፊነት ወስደን ምን ብናደርግ ባናደርግ ነው ይህ ችግር ያጋጠመን ካልን እራሳችንን የችግሩ መፍትሄ እናደርጋለን። እራሳችንን እናጎለብታለን (empower)። ችግሩን ሰፋ አድርገን እናያለን። ኃይል እንዳለን ይገባናል እና በራሳችን እንድንተማመን (confidence) ያደርገናል። አዎንታዊ እርምጃዎች ወስደን ከችግራችን እራሳችንን እናወጣለን። ደግሞ ችግር እንዳይገጥመን ደግሞ እራሳችንን እናጠነክራለን። ለደህንነታችን ሌሎችን መለመን እንደማያስፈልገን ይገባናል ስለዚህም በማንነታችን በተገቢው እንኮራለን።
በቅርቡ በቡራዩ እና ዙርያ በተከሰተው የጎሳ ማጥፋት (ethnic cleansing) ክስተት በርካቶች ኦኤምኤን ተለቪዥን ጣብያን እንደ አንድ ጥፋተኛ ከሰዋል። ኦኤሜን ላይ የሚቀርቡ ተንታኞች የዘር ማጥፋት ቅስቀሳ ስለሚያደርጉ ነው አንዱ ምክንያት እንደዚህ አይነት ክስተት የሚከሰተው ይባላል። ኦኤምኤን ነው ችግራችን እና ይዘጋ ወይንም እስከሚስተካከል ይታገድ ይባላል።
ጥሩ ነው። አጥፊ አጥፊ ነው ተብሎ መንግስትን ህግን አስከብሩ ማለትም የዘር ማጥፋት ቅስቀሳን አቁሙ ማለት ተገቢ ነው። ግን በዚ ላይ ብቻ ማተኮር እራስን አቅመ-ቢስ ማድረግ ነአ ማዋረድ ነው። አንዴ መንግስት ተነግሯል፤ መንግስት ያውቃል፤ ይበቃል። ኦኤምኤንን ደጋግሞ መክሰስ ኦኤምኤንን ማጎልበት ነው። በኛ ላይ ብዙ ኃይል አለህ እና ጫና መፍጠር ትችላለህ ማለት ነው። እኛ የአንተ ሰለቦች ነን ብሎ ማለት ነው። ይህ አካሄድ ኦኤምኤንን ያጎለብታል እኛን ደግሞ አቅመ-ቢስ ያደርጋል። የሰለባ እና የዝቅተኝነት ስሜት እንዲአድርብን ያደርጋል። በዋናነቱ ደግሞ ችግሩ እንዲቀጥል እንዲባባስ ያደርጋል።
መሆን ያለበት አንዴ መልዕክታችንን ለመንግስት ካስተላለፍን በኋላ እና ለህዝቡ የኦኤምኤንን ጥፋት ካገለጽን በኋላ ወደ ራሳችን ስራ መግባት ነው። 10% ጊዜአችን ስለ ኦኤምኤን እውነቱን መናገር ካጠፋን 90% ጊዜአችንን እራሳችን በራሳችን መፍትሄ በማግኝነት ነው ማድረግ ያለብን።
በዚህ በሚዲያ የዘር ማጥፋት ጉዳይ ምንድነው እኛ ማድረግ የምንችለው? ብዙ ነገሮች አሉ ግን አንዱ ቀላሉ ጠንካራ የኦሮምኛ ሚዲያ ማቋቋም ነው። ይህን ነው ኢሳት ረዥም ዓመታት በፊት የመከረው ግን ይህ ሙከራ አቅሙ እጅግ ደካማ ነው። ስለዚህ ያልንን አቅም (resources) ሰብስበን ኦኤምኤንን የሚበልጥ ሚዲያ በማቋቋም መስራት አለብን። ይህን ካደረግን እና ከተሳካ ግማሹ ችግር ይጠፋል። ስለ ኦኤምኤን ማልቀስ ይቀራል። ይህ አካሄድ አሉታዊ ከመሆን አዉንታዊ ያደርገናል።
ሁሉ ጉዳዮቻችንን በዚህ መልኩ ብናያቸው ጥሩ ይመስለኛል። ጣት ከመጠቆም እራስን ማየት እና እራስን አጎልብቶ መፍትሄ በራስ ባግኘት። እንዲህ አይነት አስተሳሰብ ቢኖረን ኖሮ ስንት ያለፍንባቸው ችግሮች አይኖሩም ነበር። በጥቂት ድጋፍ ያለው ህወሓትም አንገዛም ነበር! ስለዚህ የአስተሳሰብ ለውጥ ላይ እናተኩር፤ ከህጻንነት ወደ ሃላፊነት የምንወስድ አዋቂዎች እንቀየር።
ሌሎችን መውቀሱ ዋጋ የለውም። ለምን ብትሉ ችግርን የሚፈጥሩ ሰዎች አውቀው የሚያደርጉት ከሆነ የኛ እነሱን መውቀስ በሃሪና ተግባራቸውን አይቀየርም። ይቀየራሉ ብለን ስንጠብቅ ችግሮቻችንን እያባባሱ ይቀጥላሉ! እኛ እየተጠቃን እንቀጥላለን። በራሳችን ያለን መተማመን እየቀነሰ ይሄዳል። የሰለባ አስተሳሰብ (victim mentality) እና የዝቅተኝነት መንፈስ (inferiority complex) እያደረግን እየጠነከረብን እንሄዳለን። አሉንታዊ እና ብሶታዊ ሰዎች እንሆናለን።
ግን ችግር ሲያጋጥመን ሃላፊነት ወስደን ምን ብናደርግ ባናደርግ ነው ይህ ችግር ያጋጠመን ካልን እራሳችንን የችግሩ መፍትሄ እናደርጋለን። እራሳችንን እናጎለብታለን (empower)። ችግሩን ሰፋ አድርገን እናያለን። ኃይል እንዳለን ይገባናል እና በራሳችን እንድንተማመን (confidence) ያደርገናል። አዎንታዊ እርምጃዎች ወስደን ከችግራችን እራሳችንን እናወጣለን። ደግሞ ችግር እንዳይገጥመን ደግሞ እራሳችንን እናጠነክራለን። ለደህንነታችን ሌሎችን መለመን እንደማያስፈልገን ይገባናል ስለዚህም በማንነታችን በተገቢው እንኮራለን።
በቅርቡ በቡራዩ እና ዙርያ በተከሰተው የጎሳ ማጥፋት (ethnic cleansing) ክስተት በርካቶች ኦኤምኤን ተለቪዥን ጣብያን እንደ አንድ ጥፋተኛ ከሰዋል። ኦኤሜን ላይ የሚቀርቡ ተንታኞች የዘር ማጥፋት ቅስቀሳ ስለሚያደርጉ ነው አንዱ ምክንያት እንደዚህ አይነት ክስተት የሚከሰተው ይባላል። ኦኤምኤን ነው ችግራችን እና ይዘጋ ወይንም እስከሚስተካከል ይታገድ ይባላል።
ጥሩ ነው። አጥፊ አጥፊ ነው ተብሎ መንግስትን ህግን አስከብሩ ማለትም የዘር ማጥፋት ቅስቀሳን አቁሙ ማለት ተገቢ ነው። ግን በዚ ላይ ብቻ ማተኮር እራስን አቅመ-ቢስ ማድረግ ነአ ማዋረድ ነው። አንዴ መንግስት ተነግሯል፤ መንግስት ያውቃል፤ ይበቃል። ኦኤምኤንን ደጋግሞ መክሰስ ኦኤምኤንን ማጎልበት ነው። በኛ ላይ ብዙ ኃይል አለህ እና ጫና መፍጠር ትችላለህ ማለት ነው። እኛ የአንተ ሰለቦች ነን ብሎ ማለት ነው። ይህ አካሄድ ኦኤምኤንን ያጎለብታል እኛን ደግሞ አቅመ-ቢስ ያደርጋል። የሰለባ እና የዝቅተኝነት ስሜት እንዲአድርብን ያደርጋል። በዋናነቱ ደግሞ ችግሩ እንዲቀጥል እንዲባባስ ያደርጋል።
መሆን ያለበት አንዴ መልዕክታችንን ለመንግስት ካስተላለፍን በኋላ እና ለህዝቡ የኦኤምኤንን ጥፋት ካገለጽን በኋላ ወደ ራሳችን ስራ መግባት ነው። 10% ጊዜአችን ስለ ኦኤምኤን እውነቱን መናገር ካጠፋን 90% ጊዜአችንን እራሳችን በራሳችን መፍትሄ በማግኝነት ነው ማድረግ ያለብን።
በዚህ በሚዲያ የዘር ማጥፋት ጉዳይ ምንድነው እኛ ማድረግ የምንችለው? ብዙ ነገሮች አሉ ግን አንዱ ቀላሉ ጠንካራ የኦሮምኛ ሚዲያ ማቋቋም ነው። ይህን ነው ኢሳት ረዥም ዓመታት በፊት የመከረው ግን ይህ ሙከራ አቅሙ እጅግ ደካማ ነው። ስለዚህ ያልንን አቅም (resources) ሰብስበን ኦኤምኤንን የሚበልጥ ሚዲያ በማቋቋም መስራት አለብን። ይህን ካደረግን እና ከተሳካ ግማሹ ችግር ይጠፋል። ስለ ኦኤምኤን ማልቀስ ይቀራል። ይህ አካሄድ አሉታዊ ከመሆን አዉንታዊ ያደርገናል።
ሁሉ ጉዳዮቻችንን በዚህ መልኩ ብናያቸው ጥሩ ይመስለኛል። ጣት ከመጠቆም እራስን ማየት እና እራስን አጎልብቶ መፍትሄ በራስ ባግኘት። እንዲህ አይነት አስተሳሰብ ቢኖረን ኖሮ ስንት ያለፍንባቸው ችግሮች አይኖሩም ነበር። በጥቂት ድጋፍ ያለው ህወሓትም አንገዛም ነበር! ስለዚህ የአስተሳሰብ ለውጥ ላይ እናተኩር፤ ከህጻንነት ወደ ሃላፊነት የምንወስድ አዋቂዎች እንቀየር።
Friday, 10 August 2018
ጠ/ሚ አብይ አህመድ፤ የድሮ ሰው
ዓመት በፊት ማንኛውም ኢትዮጵያዊን ምን አይነት የፖለቲካ ለውጥ ትፈልጋለህ ቢባል፤ «ዴሞክራሲ፤ ነፃነት፤ ፍትህ፤ እኩልነት» ይል ነበር። ጠ/ሚ አብይ ስልጣን ሲይዙ እንደዚህ አይነት መልእክቶች እና መፈክሮች ነበር የሚጠበቅባቸው። ግን እሳቸው «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅር ማለት» አሉ። መንፈሳዊ መረጋጋትን ከፖለቲካ መረጋጋት አስቀደሙ። ይህን የድሮ ሰው ብቻ ነው የሚለው፤ የዘመኑ ሰዎች ምን ማለት እንደሆነም ሊገባን ያስቸግረናል።
ጠ/ሚ አብይ የፖለቲካ ለውጡን ሲጀምሩ በሀገራችን መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እንዴት እንደሚያመጡ ይነግሩናል ብለን ሁላችንም እንጠብቅ ነበር። በነዚህ ጉዳዮች ሲናገሩ ግን እኛ ካሰብነው አልፎ ሄዱ። እሳቸው እንኳን ለኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጥሎም ለጠቅላላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን እና የሚያስተምር መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እናመጣለን አሉ! እኛ ስለሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ነው ያሰብነው። በዛሬ ዝቅተኛ ሞራላችን ከሀገራችን ውጭ ምሳሌ መሆን እንደምንችል በፍጹም አናስብም። ጠ/ሚ አብይ ግን ዛሬ የጊዜያዊ ድክመቶች ቢኖራትም ኢትዮጵያ የአፍሪካ መሪ ናተና ይህንን ተእልኮዋን አንረሳም ብቻ ሳይሆን እናሟላለን አሉ። እንዲህ ሲሉ 60 ዓመት በፊት የነበሩ ጀግና የኢትዮጵያ ልሂቃን የማዳምጥ መሰለኝ!
ጠ/ሚ አብይ አብዛኞቻቸው ትንተናቸውን የሚጀምሩት የኢትዮጵያ ታሪክ እና ወግ በመጥቀስ ነው። ለምሳሌ ስለ «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅርታ» ሲያወሩ ወጋችን ነው ብለው ነው። ታሪካችን ጥላቻ፤ ጦርነት፤ እና ቂም በደምብ እንዳለበት አልተሳኑም ግን የታሪክ እና ወጋችን የመጨረሻ ግብ እና ፍጻሜ ፍቅር፤ ሰላም እና ይቅርታ እንደሆነ ያውቃሉ። በድክመታችን ላይ ሳይሆን በጥሩ ጎናችን ያቶኩራሉ። በዚህ ዘመን ማን እንዲህ ይላል? በዚህ ዘመን ብዙዎቻችን በዝቅተኛ መንፈስ የተሞላን ስለሆነን ከታሪክ እና ወጋችን ጥሩ ነገር አይታየንም። ግን ጠ/ሚ አብይ ታሪክ እና ወጋቸውን በሚገባው በእውነተኛ ፍቅር ነው የሚያዩት።
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ሁላችንም የጠበቅነው ጠ/ሚ አብይ መንግስት ካሁን ወድያ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገባ ያደርጋሉ ነው። ምናልባትም ይህን በይፋ ለህዝብ ይናገራሉ ነው። ግን እሳቸው እንደገና ከጠበቅነው አልፈው ቤተ ክርስቲያንን ነፃ መተው ብቻ ሳይሆን ወደ መርዳት ገቡ! መንግስት ላበላሸው ሃላፊነት አለበት ማስተካከል አለበት ብለው በሲኖዶሶቹ እርቅ እንዲኖር ምኞታቸውን ተናገሩ። መናገር ብቻ ሳይሆን ስልጣናቸውን እንደ ህሊና ግፊት በመጠቀም እርቁ እንደፈጸም አስተዋጾ አደረጉ። ጭራሽ ካልሆነ እግራችሁ ላይ ወድቄ እንድትታረቁ እለምናችኋለሁ አሉ! ማናችንም ይህን አልጠበቅንም።
ጠ/ሚ አብይ ለሀገራችን ባህላዊ ሃይማኖቶች ታላቅ ክብር አላቸው። እኛ የዘመኑ ሰዎች እንዚህን መዋቅሮች ከፖለቲካ ውጭ የሆኑ ኋላ ቀር ነገሮች ይመስሉናል። እሳቸው ግን ለሀገራችን ደህንነት እና ጤንነት አስፍላጊ እና መሰረታዊ እንደሆኑ ይገባቸዋል። እነሱን ትቶ ኢትዮጵያዊነት በአሸዋ የተመሰረተ ቤት እንድሆነች ያውቃሉ ይናገራሉ ያስተምራሉ። እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልሂቃኖቻችን ድሮ ነው የጠፋው።
ጠ/ሚ ዱባይ ሄደው ከአረብ ህብረት መሪ ጋር ሲወያዩ አረቡ ልንረዳችሁ አስበናል ምናልባትም ትምሕርት ቤቶች በኢትዮጵያ ለማቋቋም እያሰብን ነው አሉ። ጠ/ሚ አብይ እሺ አላሉም። ወይንም ጥሩ ነው ግን የኤኮኖሚ ኢንቬስትሜንት ይሻለናል አላሉም። እናንተ እምነታችሁን እያጣችሁ ስለሆነ እኛ አረብኛ ተምረን ሃይማኖትን መልሰን እናስተምራችኋለን አልዋቸው (https://www.youtube.com/watch?v=b3GUI1rD9-M)! እዩ በራሳቸው እና በሀገራቸው ምን ያህል እንደሚተማመኑ። ማናችን በዚህ ዘመን ያለነው ኢትዮጵያዊ እንደዚህ እናስባለን? ይህ የጠ/ሚ አብይ ንግግር ኢትዮጵያን በትክክለኛ በሚገባት ቦታ የሚያስቀምጥ ነው። እውነትም ነው። ግን ስንቶቻችን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልባችን ይገባን ይሆን?
ጠ/ሚ አብይ መንግስታቸው ለፈጸማቸው በደሎች በቡድናቸው በኢህአዴግ ስም ሳይሆን በግላቸው ይቅርታ ጠይቀዋል። ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው በራሱ የሚተማመን ነው (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post.html)። በራሱ የማይተማመን ሰው ወይንም የዝቅተኛ መንፈስ ያለው ሰው ይቅርታ ማለት ድክመቱን ለሁሉም የሚገልጥ ይመስለዋል። ጠ/ሚ አብይ ግን ትንሽ ይቅርታ ሳይሆን ለኢህአዴግ ኃጢአት በሙሉ ግዙፍ ይቅርታ ጠየቁ።
ከዚም አልፎ ከተለያዩ በአንድ ወቅት እንደ ጠላት የሚቆጠሩ ሰዎች ጋር በሂሊና ነፃነት ይገናኛሉ ይወያያሉ። ከኢሳያስ አፈዎርቂ፤ አብዴል እል-ሲሲ፤ ግንቦት ሰባት፤ ታማኝ በየነ፤ ጀዋር መሃመድ፤ የተለያዩ የህወሓት ሹማምንት ወዘተ በሰላም ተገናኝተው በህዝብ ፊት አብሮ ይቀርባሉ። ከነዚህ ጋር አብሮ መታየቴ እና መወያየቴ ማንነቴን በግምት ያስገባዋል እና አጉል እተቻለሁ ብለው አያስቡም። ይህም በራስ የመተማመን ምልክት ነው። ምንም አይበረግገዋቸውም። ከማንም ጋር መነጋገር እችላለሁ "on my own terms" ነው አስተሳሰባቸው።
ጠ/ሚ አብይ በራሳቸው የሚተማመኑት በሰው ልጅነታቸው ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካ አንጻር በኢትዮጵያዊነታቸው ሙሉ በሙሉ ስለሚኮሩ ነው። በዚህ በኩል የድሮ ሰው ናቸው። እንደ በምኒልክ ዘመን የነበሩት ከአውሮፓዊያን ጋር በእኩልነት ሳይ በበላይነት ስሜት የሚደራደሩ። እንደ በኃይለ ሥላሴ ዘመን ለኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ እንደሚደራደሩት አልፎ ተርፎ ለአፍሪካ የሚዋጉት። የሰለባነት አስተሳሰብ (victim mentality)፤ በዝቅተኝነት መንፈስ (inferiority complex)፤ በልመና፤ ሌሎችን መለመን ወይንም እንደ ሌሎች መሆን መፈለግ የለም። ይህ አስተሳሰብ ድንቅ ነው በአሁኑ ዘመን ከሀገራችን ብዙ የማይገኝ ነው። ግን ኢትዮጵያ እንደገና እንደዚህ አይነት እንደ ጠ/ሚ አብይ አይነቱን ሰው ማፍረት መቻሏ ተመስገን ነው። ሁላችንም የሳቸውን አስተሳሰብ (mindset) ያኑርብን። የሀገራችን ብጎ ህልውና ከዚህ ነው የምጀረውና።
ጠ/ሚ አብይ የፖለቲካ ለውጡን ሲጀምሩ በሀገራችን መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እንዴት እንደሚያመጡ ይነግሩናል ብለን ሁላችንም እንጠብቅ ነበር። በነዚህ ጉዳዮች ሲናገሩ ግን እኛ ካሰብነው አልፎ ሄዱ። እሳቸው እንኳን ለኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጥሎም ለጠቅላላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን እና የሚያስተምር መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እናመጣለን አሉ! እኛ ስለሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ነው ያሰብነው። በዛሬ ዝቅተኛ ሞራላችን ከሀገራችን ውጭ ምሳሌ መሆን እንደምንችል በፍጹም አናስብም። ጠ/ሚ አብይ ግን ዛሬ የጊዜያዊ ድክመቶች ቢኖራትም ኢትዮጵያ የአፍሪካ መሪ ናተና ይህንን ተእልኮዋን አንረሳም ብቻ ሳይሆን እናሟላለን አሉ። እንዲህ ሲሉ 60 ዓመት በፊት የነበሩ ጀግና የኢትዮጵያ ልሂቃን የማዳምጥ መሰለኝ!
ጠ/ሚ አብይ አብዛኞቻቸው ትንተናቸውን የሚጀምሩት የኢትዮጵያ ታሪክ እና ወግ በመጥቀስ ነው። ለምሳሌ ስለ «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅርታ» ሲያወሩ ወጋችን ነው ብለው ነው። ታሪካችን ጥላቻ፤ ጦርነት፤ እና ቂም በደምብ እንዳለበት አልተሳኑም ግን የታሪክ እና ወጋችን የመጨረሻ ግብ እና ፍጻሜ ፍቅር፤ ሰላም እና ይቅርታ እንደሆነ ያውቃሉ። በድክመታችን ላይ ሳይሆን በጥሩ ጎናችን ያቶኩራሉ። በዚህ ዘመን ማን እንዲህ ይላል? በዚህ ዘመን ብዙዎቻችን በዝቅተኛ መንፈስ የተሞላን ስለሆነን ከታሪክ እና ወጋችን ጥሩ ነገር አይታየንም። ግን ጠ/ሚ አብይ ታሪክ እና ወጋቸውን በሚገባው በእውነተኛ ፍቅር ነው የሚያዩት።
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ሁላችንም የጠበቅነው ጠ/ሚ አብይ መንግስት ካሁን ወድያ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገባ ያደርጋሉ ነው። ምናልባትም ይህን በይፋ ለህዝብ ይናገራሉ ነው። ግን እሳቸው እንደገና ከጠበቅነው አልፈው ቤተ ክርስቲያንን ነፃ መተው ብቻ ሳይሆን ወደ መርዳት ገቡ! መንግስት ላበላሸው ሃላፊነት አለበት ማስተካከል አለበት ብለው በሲኖዶሶቹ እርቅ እንዲኖር ምኞታቸውን ተናገሩ። መናገር ብቻ ሳይሆን ስልጣናቸውን እንደ ህሊና ግፊት በመጠቀም እርቁ እንደፈጸም አስተዋጾ አደረጉ። ጭራሽ ካልሆነ እግራችሁ ላይ ወድቄ እንድትታረቁ እለምናችኋለሁ አሉ! ማናችንም ይህን አልጠበቅንም።
ጠ/ሚ አብይ ለሀገራችን ባህላዊ ሃይማኖቶች ታላቅ ክብር አላቸው። እኛ የዘመኑ ሰዎች እንዚህን መዋቅሮች ከፖለቲካ ውጭ የሆኑ ኋላ ቀር ነገሮች ይመስሉናል። እሳቸው ግን ለሀገራችን ደህንነት እና ጤንነት አስፍላጊ እና መሰረታዊ እንደሆኑ ይገባቸዋል። እነሱን ትቶ ኢትዮጵያዊነት በአሸዋ የተመሰረተ ቤት እንድሆነች ያውቃሉ ይናገራሉ ያስተምራሉ። እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልሂቃኖቻችን ድሮ ነው የጠፋው።
ጠ/ሚ ዱባይ ሄደው ከአረብ ህብረት መሪ ጋር ሲወያዩ አረቡ ልንረዳችሁ አስበናል ምናልባትም ትምሕርት ቤቶች በኢትዮጵያ ለማቋቋም እያሰብን ነው አሉ። ጠ/ሚ አብይ እሺ አላሉም። ወይንም ጥሩ ነው ግን የኤኮኖሚ ኢንቬስትሜንት ይሻለናል አላሉም። እናንተ እምነታችሁን እያጣችሁ ስለሆነ እኛ አረብኛ ተምረን ሃይማኖትን መልሰን እናስተምራችኋለን አልዋቸው (https://www.youtube.com/watch?v=b3GUI1rD9-M)! እዩ በራሳቸው እና በሀገራቸው ምን ያህል እንደሚተማመኑ። ማናችን በዚህ ዘመን ያለነው ኢትዮጵያዊ እንደዚህ እናስባለን? ይህ የጠ/ሚ አብይ ንግግር ኢትዮጵያን በትክክለኛ በሚገባት ቦታ የሚያስቀምጥ ነው። እውነትም ነው። ግን ስንቶቻችን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልባችን ይገባን ይሆን?
ጠ/ሚ አብይ መንግስታቸው ለፈጸማቸው በደሎች በቡድናቸው በኢህአዴግ ስም ሳይሆን በግላቸው ይቅርታ ጠይቀዋል። ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው በራሱ የሚተማመን ነው (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post.html)። በራሱ የማይተማመን ሰው ወይንም የዝቅተኛ መንፈስ ያለው ሰው ይቅርታ ማለት ድክመቱን ለሁሉም የሚገልጥ ይመስለዋል። ጠ/ሚ አብይ ግን ትንሽ ይቅርታ ሳይሆን ለኢህአዴግ ኃጢአት በሙሉ ግዙፍ ይቅርታ ጠየቁ።
ከዚም አልፎ ከተለያዩ በአንድ ወቅት እንደ ጠላት የሚቆጠሩ ሰዎች ጋር በሂሊና ነፃነት ይገናኛሉ ይወያያሉ። ከኢሳያስ አፈዎርቂ፤ አብዴል እል-ሲሲ፤ ግንቦት ሰባት፤ ታማኝ በየነ፤ ጀዋር መሃመድ፤ የተለያዩ የህወሓት ሹማምንት ወዘተ በሰላም ተገናኝተው በህዝብ ፊት አብሮ ይቀርባሉ። ከነዚህ ጋር አብሮ መታየቴ እና መወያየቴ ማንነቴን በግምት ያስገባዋል እና አጉል እተቻለሁ ብለው አያስቡም። ይህም በራስ የመተማመን ምልክት ነው። ምንም አይበረግገዋቸውም። ከማንም ጋር መነጋገር እችላለሁ "on my own terms" ነው አስተሳሰባቸው።
ጠ/ሚ አብይ በራሳቸው የሚተማመኑት በሰው ልጅነታቸው ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካ አንጻር በኢትዮጵያዊነታቸው ሙሉ በሙሉ ስለሚኮሩ ነው። በዚህ በኩል የድሮ ሰው ናቸው። እንደ በምኒልክ ዘመን የነበሩት ከአውሮፓዊያን ጋር በእኩልነት ሳይ በበላይነት ስሜት የሚደራደሩ። እንደ በኃይለ ሥላሴ ዘመን ለኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ እንደሚደራደሩት አልፎ ተርፎ ለአፍሪካ የሚዋጉት። የሰለባነት አስተሳሰብ (victim mentality)፤ በዝቅተኝነት መንፈስ (inferiority complex)፤ በልመና፤ ሌሎችን መለመን ወይንም እንደ ሌሎች መሆን መፈለግ የለም። ይህ አስተሳሰብ ድንቅ ነው በአሁኑ ዘመን ከሀገራችን ብዙ የማይገኝ ነው። ግን ኢትዮጵያ እንደገና እንደዚህ አይነት እንደ ጠ/ሚ አብይ አይነቱን ሰው ማፍረት መቻሏ ተመስገን ነው። ሁላችንም የሳቸውን አስተሳሰብ (mindset) ያኑርብን። የሀገራችን ብጎ ህልውና ከዚህ ነው የምጀረውና።
Subscribe to:
Posts (Atom)