ለመጀመርያ ጊዜ በአማራ ስም ፋንታ በኢትዮጵያ ስም ብትደራጁ አይሻልም ወይ ብዬ የአማራ ብሄርተኞችን ስጠይቅ ያገኘሁት መልሶች (ስድቦቹን ትተን) አስገራሚ ነበር። ምናልባት 80% ስለ አማራ ላይ ባለፉት 27/40 ዓመት የደረሰበት በደል እና ጭቆና ነው። የአማራ ህዝብ ጥቅም ይበልጥ የሚከበረው በአማራነት በመደራጀት ነው ወይንም በኢትዮጵያዊነት በሚለው ዙርያ ከመወያየት ፋንታ ስለ አማራ መጨቆን የጭቆና ቆጠራ ውስጥ ገባን። ይህን ስል አማራው አልተጨቆነም ማለቴ አይደለም ከሌሎች ይልቅ በመንግስት ብቻ ሳይሆን በግለ ሰብ እና በቡድን በአማራነቱ ተጭቁኗል «መጤም» እየተባለ በትውልድ ሀገሩ ባይተዋር ሆኗል። ይህ ሁሉም የሚያቀው ነው። ግን ይህ በፍፁም የአማራ ማንነት መግለጫ መሆን የለበትም። ላስረዳ…
እንደገባኝ ይህ የ27 ዓመት ጭቆና የዛሬው የአማራ ማንነት መሰረት ሆኗል። እስቲ ስለ አማራ እና አማራነት ንገረኝ ሲባል የዘመኑ አማራ ላለፉት አመታት «እጅግ የተጨቆነ፤ የተበድለ፤ የተፈናቀለ፤ የተዋረደ፤ ባሁሉ የተሰደበ፤ ማንነቱ የተገፈፈ» ወዘተ ነው የሚለው። የድሮ አማራ ይህንን ቢሰማ እጅግ ግራ ነበር የሚገባው። ማን ነው አማራ ምንድነው አማራነት ብለህ የድሮ አማራን ብትጠይቀው 3000 ዓመት ታሪክ ያለው፤ ሃይማኖት ያለው፤ ስልጣኔ ያለው፤ የአፍሪካ ቁንጮ፤ የሰው ልጅ ቁንጮ፤ ፍርሃ እግዚአብሔር ወዘተ ነው የሚለው! ልዩነቱን አያችሁ። አማራ በወጉ መሰረት እራሱን የሚሰይመው ማንነቱን የሚገልጸው በአዎንታዊ መንገድ ነው። ዛሬ ግን እድሜ ለረዥም ዓመት ጫና እና የጎሳ ብሄርተኝነት እና የማርክሲዝም ፕሮፓጋንዳ አማራው ማንነቱን ስቷል።
የዛሬ አማራ የበታችነትን ስሜት (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_30.html) መቀበል ብቻ ሳይሆን የማንነቱ መሰረት ያደረገው ይመስላል። የሰለባ አመለካከት (victim complex)፤ የበታችነት ስሜት (inferiority complex) አጥቅቶናል። እንደ ጥቁር አሜሪካኖች ወይንም ሌሎች በጭቆና ምክንያት ማንነታቸውን ሙሉ በሙሉ ለ«ጭቁን ነው ማንነቴ» የሚለው አስተሳሰብ እራሳችንን ሰጥተናል።
በራሳችን መተማመን እና መኩራት ቀርቷል። ጣልያን ለአምስት ዓመት ኢትዮጵያ ውስጥ ቆይቶ ተጭቁነናል ተገዝተናል ብለን አናውቅም። የድሮ አማራ ምንም ያህል ቢጭቆን እራሱን «ተጨቋኝ ነኝ» ብሎ አይሰይምም። ጦርነት ላይ ነኝ ነው የሚለው። እንደ አያቶቼ አሸንፋለው ነው የሚለው። እንጂ እጁን ለበታችነት ስሜት አይሰጥም ምን እንደሆነም አያቅም። ለዚህ ነው እስከ ዛሬ ጣልያን ገዝቶናል አንልም። ውግያ ላይ ነበርን ነው የምንለው። ይህ ነበር የድሮ እና ትክክለኛ ተውፊተኛ የአማራ ስለራሱ ማንነት አስተሳሰብ።
ዛሬ ግን ይህ ባለመሆኑ ብዙ አማራ በተለይ ወጣቱ «ጭቁን ብሄረሰብ» ነኝ የሚለው አስተሳሰብ አምኖበት ውጦታል (internalize) ተዋህዶታል። ስለዚህ ይመስለኛል የ«አማራ ብሄርተኝነት» ድሮ ታይቶ የማይተወቀው ዛሬ እንደዚህ መነሳት የጀመረው። በጎሳ ብሄርተኝነት የማናምነው ወንድሞች እና እህቶች ይህ የአማራ ብሄርተኝነት ፖለቲካ ለአማራ ህዝብ ያዋጣል ወይ በሚለው እንነጋገር ስንል ብዙ ጊዜ ስሜታዊ መልስ እና ስድብ ነው የሚጠብቀን። ምክንያቱ የአማራ ብሄርተኛውን ማንነት ጥያቄ ውስጥ ስላደረግን ነው። ማንነቱ «ጭቁን አማራ» ሆኗል። አንድ ሰው ይህ ነው ማንኔቴ ብሎ ከሰየመ አልፎ ተርፎ ቁስል ያለው ከሆነ በዚህ ዙራይ መወያየት አይችልም። ውይይቱ በሃሳብ ሳይሆን በማንነት ስለሆነ በዚህ መደራደር የለም። ስሜት እና ቁጣ ብቻ ነው።
ይህ ክስተት እነ ሻዕቢያ፤ ህወሓት፤ እና ኦነግ ሲመሰረቱ አይተነዋል። ወደነዚህ የሚያዘንብሎ ሰዎችን ድሮ ስናናገር አንዴ እንዲሁም እንዴት ማንነቴን በጥያቄ መልክ ታቀርበዋለሁ ብለው ይናደዱ ነበር። በማንነት ድርድር የለም ይሉ ነበር። መገንጠል አይበጅም ኢትዮጵያዊ ናችሁ ወዘተ አይነት ነበር በፍፁም መስማት ብቻ ሳይሆን ስለዚህ መነጋገርም አይፈልጉም። አንዴ ማንነት ከተቀየረ በአጭር ጊዜ ምንም ማድረግ አይቻልም።
ስለዚህ አሁን ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ብዙ በተለይ ልጅ የሆኑ አማራ እህት እና ወንድሞቻችን ባለፈው 27 ዓመት የጎሰኝነት፤ ፀረ አማራ፤ ማርክሲዝም ፕሮፓጋንዳ ቶሞልተው የአማራ ማንነታቸው ተቀይሯል። «ጭቁን» ነኝ ብለው አምነዋል። ለዚህ ጭቆና መልሱ ወደ «አማራነት» ከ«ኢትዮጵያዊነት» ማስቀደም ነው ብለው አምነዋል። ይህን በሰላም መተቸት ማንነትን መተቸት ሆኗል።
ጉዳዩ እንደዚህ ባይሆን እና የበታችንነት እና የ«ጭቁን» አስተሳሰብ ባይህኖር መርሰረታዊ ጥያቄውን በአማራ ስም ነው ወይም በኢትዮጵያ ስም ነው መደራጀት የሚበጀን መወያየት እንችል ነበር። አሁን ግን ለብዙዋች ውይይት አቻልም ስሜት ይነካልና ማንነትን ይነካልና።
አንድ ማረግ የምንችለው የአማራ ባህል እና ወግ በትክክሉ ማስተማር ነው። የአማራ 3000 ዓመት ታሪክ በራሱ መኩራት እና መተማመን ነው። ፍርሃት የለውም። እንደ ጠ/ሚ አብይ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_10.html) ማንም አይነት ሰውን አቅፎ ይዞ እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አምኖ ወደ ትክክለኛ መንገድ ማምጣት ነው ባህላችን። ወደዛ ለመመለስ እንጥራ። መሰረታዊ ማንነቱን ያጣ ህብረተሰብ ይወድቃል።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label በራስ መተማመን. Show all posts
Showing posts with label በራስ መተማመን. Show all posts
Friday, 17 August 2018
Friday, 10 August 2018
ጠ/ሚ አብይ አህመድ፤ የድሮ ሰው
ዓመት በፊት ማንኛውም ኢትዮጵያዊን ምን አይነት የፖለቲካ ለውጥ ትፈልጋለህ ቢባል፤ «ዴሞክራሲ፤ ነፃነት፤ ፍትህ፤ እኩልነት» ይል ነበር። ጠ/ሚ አብይ ስልጣን ሲይዙ እንደዚህ አይነት መልእክቶች እና መፈክሮች ነበር የሚጠበቅባቸው። ግን እሳቸው «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅር ማለት» አሉ። መንፈሳዊ መረጋጋትን ከፖለቲካ መረጋጋት አስቀደሙ። ይህን የድሮ ሰው ብቻ ነው የሚለው፤ የዘመኑ ሰዎች ምን ማለት እንደሆነም ሊገባን ያስቸግረናል።
ጠ/ሚ አብይ የፖለቲካ ለውጡን ሲጀምሩ በሀገራችን መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እንዴት እንደሚያመጡ ይነግሩናል ብለን ሁላችንም እንጠብቅ ነበር። በነዚህ ጉዳዮች ሲናገሩ ግን እኛ ካሰብነው አልፎ ሄዱ። እሳቸው እንኳን ለኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጥሎም ለጠቅላላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን እና የሚያስተምር መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እናመጣለን አሉ! እኛ ስለሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ነው ያሰብነው። በዛሬ ዝቅተኛ ሞራላችን ከሀገራችን ውጭ ምሳሌ መሆን እንደምንችል በፍጹም አናስብም። ጠ/ሚ አብይ ግን ዛሬ የጊዜያዊ ድክመቶች ቢኖራትም ኢትዮጵያ የአፍሪካ መሪ ናተና ይህንን ተእልኮዋን አንረሳም ብቻ ሳይሆን እናሟላለን አሉ። እንዲህ ሲሉ 60 ዓመት በፊት የነበሩ ጀግና የኢትዮጵያ ልሂቃን የማዳምጥ መሰለኝ!
ጠ/ሚ አብይ አብዛኞቻቸው ትንተናቸውን የሚጀምሩት የኢትዮጵያ ታሪክ እና ወግ በመጥቀስ ነው። ለምሳሌ ስለ «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅርታ» ሲያወሩ ወጋችን ነው ብለው ነው። ታሪካችን ጥላቻ፤ ጦርነት፤ እና ቂም በደምብ እንዳለበት አልተሳኑም ግን የታሪክ እና ወጋችን የመጨረሻ ግብ እና ፍጻሜ ፍቅር፤ ሰላም እና ይቅርታ እንደሆነ ያውቃሉ። በድክመታችን ላይ ሳይሆን በጥሩ ጎናችን ያቶኩራሉ። በዚህ ዘመን ማን እንዲህ ይላል? በዚህ ዘመን ብዙዎቻችን በዝቅተኛ መንፈስ የተሞላን ስለሆነን ከታሪክ እና ወጋችን ጥሩ ነገር አይታየንም። ግን ጠ/ሚ አብይ ታሪክ እና ወጋቸውን በሚገባው በእውነተኛ ፍቅር ነው የሚያዩት።
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ሁላችንም የጠበቅነው ጠ/ሚ አብይ መንግስት ካሁን ወድያ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገባ ያደርጋሉ ነው። ምናልባትም ይህን በይፋ ለህዝብ ይናገራሉ ነው። ግን እሳቸው እንደገና ከጠበቅነው አልፈው ቤተ ክርስቲያንን ነፃ መተው ብቻ ሳይሆን ወደ መርዳት ገቡ! መንግስት ላበላሸው ሃላፊነት አለበት ማስተካከል አለበት ብለው በሲኖዶሶቹ እርቅ እንዲኖር ምኞታቸውን ተናገሩ። መናገር ብቻ ሳይሆን ስልጣናቸውን እንደ ህሊና ግፊት በመጠቀም እርቁ እንደፈጸም አስተዋጾ አደረጉ። ጭራሽ ካልሆነ እግራችሁ ላይ ወድቄ እንድትታረቁ እለምናችኋለሁ አሉ! ማናችንም ይህን አልጠበቅንም።
ጠ/ሚ አብይ ለሀገራችን ባህላዊ ሃይማኖቶች ታላቅ ክብር አላቸው። እኛ የዘመኑ ሰዎች እንዚህን መዋቅሮች ከፖለቲካ ውጭ የሆኑ ኋላ ቀር ነገሮች ይመስሉናል። እሳቸው ግን ለሀገራችን ደህንነት እና ጤንነት አስፍላጊ እና መሰረታዊ እንደሆኑ ይገባቸዋል። እነሱን ትቶ ኢትዮጵያዊነት በአሸዋ የተመሰረተ ቤት እንድሆነች ያውቃሉ ይናገራሉ ያስተምራሉ። እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልሂቃኖቻችን ድሮ ነው የጠፋው።
ጠ/ሚ ዱባይ ሄደው ከአረብ ህብረት መሪ ጋር ሲወያዩ አረቡ ልንረዳችሁ አስበናል ምናልባትም ትምሕርት ቤቶች በኢትዮጵያ ለማቋቋም እያሰብን ነው አሉ። ጠ/ሚ አብይ እሺ አላሉም። ወይንም ጥሩ ነው ግን የኤኮኖሚ ኢንቬስትሜንት ይሻለናል አላሉም። እናንተ እምነታችሁን እያጣችሁ ስለሆነ እኛ አረብኛ ተምረን ሃይማኖትን መልሰን እናስተምራችኋለን አልዋቸው (https://www.youtube.com/watch?v=b3GUI1rD9-M)! እዩ በራሳቸው እና በሀገራቸው ምን ያህል እንደሚተማመኑ። ማናችን በዚህ ዘመን ያለነው ኢትዮጵያዊ እንደዚህ እናስባለን? ይህ የጠ/ሚ አብይ ንግግር ኢትዮጵያን በትክክለኛ በሚገባት ቦታ የሚያስቀምጥ ነው። እውነትም ነው። ግን ስንቶቻችን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልባችን ይገባን ይሆን?
ጠ/ሚ አብይ መንግስታቸው ለፈጸማቸው በደሎች በቡድናቸው በኢህአዴግ ስም ሳይሆን በግላቸው ይቅርታ ጠይቀዋል። ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው በራሱ የሚተማመን ነው (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post.html)። በራሱ የማይተማመን ሰው ወይንም የዝቅተኛ መንፈስ ያለው ሰው ይቅርታ ማለት ድክመቱን ለሁሉም የሚገልጥ ይመስለዋል። ጠ/ሚ አብይ ግን ትንሽ ይቅርታ ሳይሆን ለኢህአዴግ ኃጢአት በሙሉ ግዙፍ ይቅርታ ጠየቁ።
ከዚም አልፎ ከተለያዩ በአንድ ወቅት እንደ ጠላት የሚቆጠሩ ሰዎች ጋር በሂሊና ነፃነት ይገናኛሉ ይወያያሉ። ከኢሳያስ አፈዎርቂ፤ አብዴል እል-ሲሲ፤ ግንቦት ሰባት፤ ታማኝ በየነ፤ ጀዋር መሃመድ፤ የተለያዩ የህወሓት ሹማምንት ወዘተ በሰላም ተገናኝተው በህዝብ ፊት አብሮ ይቀርባሉ። ከነዚህ ጋር አብሮ መታየቴ እና መወያየቴ ማንነቴን በግምት ያስገባዋል እና አጉል እተቻለሁ ብለው አያስቡም። ይህም በራስ የመተማመን ምልክት ነው። ምንም አይበረግገዋቸውም። ከማንም ጋር መነጋገር እችላለሁ "on my own terms" ነው አስተሳሰባቸው።
ጠ/ሚ አብይ በራሳቸው የሚተማመኑት በሰው ልጅነታቸው ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካ አንጻር በኢትዮጵያዊነታቸው ሙሉ በሙሉ ስለሚኮሩ ነው። በዚህ በኩል የድሮ ሰው ናቸው። እንደ በምኒልክ ዘመን የነበሩት ከአውሮፓዊያን ጋር በእኩልነት ሳይ በበላይነት ስሜት የሚደራደሩ። እንደ በኃይለ ሥላሴ ዘመን ለኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ እንደሚደራደሩት አልፎ ተርፎ ለአፍሪካ የሚዋጉት። የሰለባነት አስተሳሰብ (victim mentality)፤ በዝቅተኝነት መንፈስ (inferiority complex)፤ በልመና፤ ሌሎችን መለመን ወይንም እንደ ሌሎች መሆን መፈለግ የለም። ይህ አስተሳሰብ ድንቅ ነው በአሁኑ ዘመን ከሀገራችን ብዙ የማይገኝ ነው። ግን ኢትዮጵያ እንደገና እንደዚህ አይነት እንደ ጠ/ሚ አብይ አይነቱን ሰው ማፍረት መቻሏ ተመስገን ነው። ሁላችንም የሳቸውን አስተሳሰብ (mindset) ያኑርብን። የሀገራችን ብጎ ህልውና ከዚህ ነው የምጀረውና።
ጠ/ሚ አብይ የፖለቲካ ለውጡን ሲጀምሩ በሀገራችን መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እንዴት እንደሚያመጡ ይነግሩናል ብለን ሁላችንም እንጠብቅ ነበር። በነዚህ ጉዳዮች ሲናገሩ ግን እኛ ካሰብነው አልፎ ሄዱ። እሳቸው እንኳን ለኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጥሎም ለጠቅላላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን እና የሚያስተምር መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እናመጣለን አሉ! እኛ ስለሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ነው ያሰብነው። በዛሬ ዝቅተኛ ሞራላችን ከሀገራችን ውጭ ምሳሌ መሆን እንደምንችል በፍጹም አናስብም። ጠ/ሚ አብይ ግን ዛሬ የጊዜያዊ ድክመቶች ቢኖራትም ኢትዮጵያ የአፍሪካ መሪ ናተና ይህንን ተእልኮዋን አንረሳም ብቻ ሳይሆን እናሟላለን አሉ። እንዲህ ሲሉ 60 ዓመት በፊት የነበሩ ጀግና የኢትዮጵያ ልሂቃን የማዳምጥ መሰለኝ!
ጠ/ሚ አብይ አብዛኞቻቸው ትንተናቸውን የሚጀምሩት የኢትዮጵያ ታሪክ እና ወግ በመጥቀስ ነው። ለምሳሌ ስለ «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅርታ» ሲያወሩ ወጋችን ነው ብለው ነው። ታሪካችን ጥላቻ፤ ጦርነት፤ እና ቂም በደምብ እንዳለበት አልተሳኑም ግን የታሪክ እና ወጋችን የመጨረሻ ግብ እና ፍጻሜ ፍቅር፤ ሰላም እና ይቅርታ እንደሆነ ያውቃሉ። በድክመታችን ላይ ሳይሆን በጥሩ ጎናችን ያቶኩራሉ። በዚህ ዘመን ማን እንዲህ ይላል? በዚህ ዘመን ብዙዎቻችን በዝቅተኛ መንፈስ የተሞላን ስለሆነን ከታሪክ እና ወጋችን ጥሩ ነገር አይታየንም። ግን ጠ/ሚ አብይ ታሪክ እና ወጋቸውን በሚገባው በእውነተኛ ፍቅር ነው የሚያዩት።
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ሁላችንም የጠበቅነው ጠ/ሚ አብይ መንግስት ካሁን ወድያ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገባ ያደርጋሉ ነው። ምናልባትም ይህን በይፋ ለህዝብ ይናገራሉ ነው። ግን እሳቸው እንደገና ከጠበቅነው አልፈው ቤተ ክርስቲያንን ነፃ መተው ብቻ ሳይሆን ወደ መርዳት ገቡ! መንግስት ላበላሸው ሃላፊነት አለበት ማስተካከል አለበት ብለው በሲኖዶሶቹ እርቅ እንዲኖር ምኞታቸውን ተናገሩ። መናገር ብቻ ሳይሆን ስልጣናቸውን እንደ ህሊና ግፊት በመጠቀም እርቁ እንደፈጸም አስተዋጾ አደረጉ። ጭራሽ ካልሆነ እግራችሁ ላይ ወድቄ እንድትታረቁ እለምናችኋለሁ አሉ! ማናችንም ይህን አልጠበቅንም።
ጠ/ሚ አብይ ለሀገራችን ባህላዊ ሃይማኖቶች ታላቅ ክብር አላቸው። እኛ የዘመኑ ሰዎች እንዚህን መዋቅሮች ከፖለቲካ ውጭ የሆኑ ኋላ ቀር ነገሮች ይመስሉናል። እሳቸው ግን ለሀገራችን ደህንነት እና ጤንነት አስፍላጊ እና መሰረታዊ እንደሆኑ ይገባቸዋል። እነሱን ትቶ ኢትዮጵያዊነት በአሸዋ የተመሰረተ ቤት እንድሆነች ያውቃሉ ይናገራሉ ያስተምራሉ። እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልሂቃኖቻችን ድሮ ነው የጠፋው።
ጠ/ሚ ዱባይ ሄደው ከአረብ ህብረት መሪ ጋር ሲወያዩ አረቡ ልንረዳችሁ አስበናል ምናልባትም ትምሕርት ቤቶች በኢትዮጵያ ለማቋቋም እያሰብን ነው አሉ። ጠ/ሚ አብይ እሺ አላሉም። ወይንም ጥሩ ነው ግን የኤኮኖሚ ኢንቬስትሜንት ይሻለናል አላሉም። እናንተ እምነታችሁን እያጣችሁ ስለሆነ እኛ አረብኛ ተምረን ሃይማኖትን መልሰን እናስተምራችኋለን አልዋቸው (https://www.youtube.com/watch?v=b3GUI1rD9-M)! እዩ በራሳቸው እና በሀገራቸው ምን ያህል እንደሚተማመኑ። ማናችን በዚህ ዘመን ያለነው ኢትዮጵያዊ እንደዚህ እናስባለን? ይህ የጠ/ሚ አብይ ንግግር ኢትዮጵያን በትክክለኛ በሚገባት ቦታ የሚያስቀምጥ ነው። እውነትም ነው። ግን ስንቶቻችን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልባችን ይገባን ይሆን?
ጠ/ሚ አብይ መንግስታቸው ለፈጸማቸው በደሎች በቡድናቸው በኢህአዴግ ስም ሳይሆን በግላቸው ይቅርታ ጠይቀዋል። ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው በራሱ የሚተማመን ነው (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post.html)። በራሱ የማይተማመን ሰው ወይንም የዝቅተኛ መንፈስ ያለው ሰው ይቅርታ ማለት ድክመቱን ለሁሉም የሚገልጥ ይመስለዋል። ጠ/ሚ አብይ ግን ትንሽ ይቅርታ ሳይሆን ለኢህአዴግ ኃጢአት በሙሉ ግዙፍ ይቅርታ ጠየቁ።
ከዚም አልፎ ከተለያዩ በአንድ ወቅት እንደ ጠላት የሚቆጠሩ ሰዎች ጋር በሂሊና ነፃነት ይገናኛሉ ይወያያሉ። ከኢሳያስ አፈዎርቂ፤ አብዴል እል-ሲሲ፤ ግንቦት ሰባት፤ ታማኝ በየነ፤ ጀዋር መሃመድ፤ የተለያዩ የህወሓት ሹማምንት ወዘተ በሰላም ተገናኝተው በህዝብ ፊት አብሮ ይቀርባሉ። ከነዚህ ጋር አብሮ መታየቴ እና መወያየቴ ማንነቴን በግምት ያስገባዋል እና አጉል እተቻለሁ ብለው አያስቡም። ይህም በራስ የመተማመን ምልክት ነው። ምንም አይበረግገዋቸውም። ከማንም ጋር መነጋገር እችላለሁ "on my own terms" ነው አስተሳሰባቸው።
ጠ/ሚ አብይ በራሳቸው የሚተማመኑት በሰው ልጅነታቸው ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካ አንጻር በኢትዮጵያዊነታቸው ሙሉ በሙሉ ስለሚኮሩ ነው። በዚህ በኩል የድሮ ሰው ናቸው። እንደ በምኒልክ ዘመን የነበሩት ከአውሮፓዊያን ጋር በእኩልነት ሳይ በበላይነት ስሜት የሚደራደሩ። እንደ በኃይለ ሥላሴ ዘመን ለኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ እንደሚደራደሩት አልፎ ተርፎ ለአፍሪካ የሚዋጉት። የሰለባነት አስተሳሰብ (victim mentality)፤ በዝቅተኝነት መንፈስ (inferiority complex)፤ በልመና፤ ሌሎችን መለመን ወይንም እንደ ሌሎች መሆን መፈለግ የለም። ይህ አስተሳሰብ ድንቅ ነው በአሁኑ ዘመን ከሀገራችን ብዙ የማይገኝ ነው። ግን ኢትዮጵያ እንደገና እንደዚህ አይነት እንደ ጠ/ሚ አብይ አይነቱን ሰው ማፍረት መቻሏ ተመስገን ነው። ሁላችንም የሳቸውን አስተሳሰብ (mindset) ያኑርብን። የሀገራችን ብጎ ህልውና ከዚህ ነው የምጀረውና።
Subscribe to:
Posts (Atom)