Showing posts with label media. Show all posts
Showing posts with label media. Show all posts

Wednesday, 27 March 2019

ብራቮ ኤልቲቪ!

እንደዚህ ተቃራኒ አስተያየቶች አብሮ ማምጣት በጣም አስፈላጊ ነው። ነጣጥሎ ቃለ ምልልስ መስጠት ገንቢ አይደለም፤ ትችት እና እሮሮ ብቻ ነው የሚሆነው። አሁን ግን የሀገር ግንባታ ጊዜ በመሆኑ ሃሳብ በሰላሰል እና መፈጨት አለበት። ቀጥሉበት!

Thursday, 11 October 2018

መልዕክት ለኢሳቶች…

አቤቱታ፤ ማማረር፤ ማልቀስ፤ complaining ህዝብን ተስፋ እንዲቆርት ያደርጋል። ይህ ከኢሳት ተዕልኮ የሚጻረር ነው።

እንደ አንድ ተራ ዜጋ ምክሬ እንዲህ ነው፤ ስለ ችግሮች ለ10 ደቂቃ ካወራችሁ ስለ መፍትሄ እና አማራጭ መንገዶች ለ20 ደቂቃ ተወያዩ። አዋጪው መንገድ ይህ ይመስለኛል።

Tuesday, 25 September 2018

ግንቦት 7 የህዝብ ግንኙነቱን ያጎልብት

ግንቦት 7 የ«ኢትዮጵያዊ ብሀርተኝነት» ዋናው (እክካሁን) የፖለቲካ ድርጅት በመሆኑ ለሀገራችን ህልውና ታላቅ ሚና መጫወት ይኖርበታል። ግን የሚገባውን ሚና ለመጫወት አንድ አንድ ድክመቶቹን ማስተካከል ይኖርበታል።

በሰሞኑ የእውን (real)፤ የዜና እና ማህበራዊ ሚዲያ ግርግር የግንብቶ 7 የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ድክመቶች ጎልተው የታዩ ይመስለኛል። ድክመቶቹ፤

1. ምንም መልዕክት አያስተላልፍም
2. መልዕክቶች ካስተላለፈም ከተለያዩ ሰዎች ዥንጉርጉር የሆኑ መልዕክቶች ናቸው
3. የሚመጡት መልዕክቶች የድርጅቱን አላማ የሚያደናቅፉ ናቸው
4. አጄንዳ መሪ ከመሆን አጄንዳ ተከታይ ይመስላል (instead of setting the agenda, always in reaction mode)

1. በአሁኑ ዘመን ማንኛውም የለህዝብ አስተያየት የሚያገባው ተቋም ለህዝብ መልዕክቶች ቶሎ ብሎ ማሰራጨት አለበት። በኦነግ አቀባበል ግርግር፤ በቡራዩ ክስተት፤ በአዲስ አበባው የህዝብ አፈሳ ወዘተ ግንቦት 7 በፍጥነት አጫጭር የሆኑ የድርጅቱን አስተያየት እና ግብ የሚያንጸባርቁ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ነበረበት ግን አላደረገም። ባለማድረጉ ህዝብ ለመረጃ ወደ ሌሎች ምንጮች እንዲሄድ አድርጓል። ሌሎች ደግሞ በደስታ የማይሆን ፕሮፓጋንዳ ለህዝቡ ያንሰራጫሉ። ይህ ለግንቦት 7 አደጋ ነው።

2. ግንቦት 7 የሚያንስተላለፉት መልዕክቶች ደግሞ የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ እኔ ያነበብቋቸው ከአንዳርጋቸው ጽጌ እና ከነአምን ዘለቀ ትንሽ ተመሳሳይ የሆኑ አለ። ግን ደግሞ ሙሉነህ እዮኤል ስለ ስልክ ጠለፋ የሚያተኩር መልዕክት አስተላለፈ። አንድ official መልዕክት ሊኖር ይገባ ነበር ከዛ ሌሎቹ ያንን ቴማ የሚከተሉ መሆን ነበረበት። ለምሳሌ ዋና ቴማ «ስራችንን በደምብ እየሰራን ነው ተረጋግቶ ስራችንን መቀጠል ነው» ከሆነ ሁሉም መልዕክቶች ይህንን ማንጸባረቅ አለባቸው።

3. የሙሉነህ እዮኤል መልዕክት ጥሩ ነገሩ የድርጅቱ አመራር የተሰሩትን የግንቦት 7 አባላትን ጠየቁ የሚለው ነው። ግን ስለ ስልክ ጠለፋ ያስተላለፈው መልዕክት ከግንቦት 7 አላማ ተጻራሪ ይመስለኛል። አሁን የግንቦት 7 ዋና ስራ አቅም ግንባታ (capacity building) የሆነ ይመስለኛል። ድጋፍ፤ አባላት፤ ገንዘብ እና የሰው አቅም ማጎልበት ነው። ለዚህ ደግሞ ሰውዉ እንዲረጋጋ እና ፖለቲካውን እንዳይፈራ ማድረግ ያስፈልጋል። ሁሉን የጊዜያዊ ክስተቶች (short term events) በቀላሉ እንደወሰዱ እና ከዋና አላማ እንዳያዘናጉ ማድረግ ነው ያለበት። ለምሳሌ ስለ ስልክ ጠለፋ፤ መንግስት ስልክን እንደሚጠልፍ የታወቀ ነው። በተለይም የተቃዋሚ ስልኮችን። ግንቦት 7 ሀገር ውስጥ ሲገባ ይህንን ጠንቅቆ ያውቃል። ገና በርካታ የነባር ኃይል ደጋፊዎች አሉ በመንግስቱ። እነሱም አዲሶቹም ለድህንነት እና ፖለቲካቸው የስልክ ጠለፋን ይፈልጉታል። ስለዚህ የተቃዋሚ ስልክ ተጠለፈ ብሎ መአስደንገጥ አያስፈልግም። ይህ ህዝብን ያስፈራራል መፍራቱ ደግሞ ከግንቦት 7 ፍላጎት የሚጻረር ነው። ግንቦት 7 ከሁሉም ነገር በላይ ዛሬ ህዝቡ ፖለቲካን እንዳይፈራ እና ከሱ ስር እንዲሳተፍ ነው የሚፈልገው። «የሁሉም ስልክ ይጠለፋል እንኳን የነኦነግ ስልክም ተጠለፈ» ማለት ነው። አሁን ወደ ስራችን እንመለስ ነው።

4. ምንም አዲስ ወይንም አስደናቂ ዜና ባይኖርም ግንቦት 7 በየቀኑ የሚዲያ አጄንዳ የሚመራ መልዕክት ማስተላለፍ አለበት። በተለይም ስለ ሰላም፤ ፍቅር፤ መደራጀት፤ ስብሰባ፤ አቅም ግንባታ ወዘተ። እንደዚህ አይነት አካሄድ ግንቦት 7 በህዝቡ እምኔታ እንዲያገኝ ይረደዋል (it breeds familiarity and trust)። ይህ ደግሞ አባላት እና አቅም ለመሰብሰብ አስፈላጊ ነው።

Saturday, 15 September 2018

ህዝብ ፉት የፒለቲካ ውይይቶች ዛሬውኑ ይጀመሩ

ማሳሰብያ፤ ኢቢሲ በአስቸቋይ ተከታታይ የፖለቲካ ውይይቶችን አሁኑኑ ማዘጋጀት መጀመር አለበት።

1. «ፖለቲከኞቻችን» እራሳቸውን ህዝብ ፉት ማጋለጥ አለባችው። ዙርያ ጥምጥም ቀርቶ ማንነታቸውን ማየት አለብን።

2. አቋሞቻቸውንም ከመደበቅ ይልቅ ማስፈትሽ አለባቸው።

3. ፖለቲከኞቻችን ከዝግ በር ኋላ ለማሰብ 27 ዓመት ተሰጥተዋል። ያጡት ይሄን ሳይሆን የህዝቡን ሃሳብ እና ዝንባሌን ማወቅ ስለሆነ አሁኑኑ ህዝብ ፉት ይቅረቡ።

4. መጀመርያ ፕሪግራም እንቅረጽ ማለት ተገቡ አይደለም። ይህ ሂደት ፕሪግራም እንዱቀርጹ ይረዳቸዋል ያስፈልጋቸዋልና።

5. ህዝቡ ውይይትን ይልመድ። እንደ ቅንጅት ጊዜ የአንድ ወር ውይይት ሳይሆን የዓመት ዓመታት ነው የሚያስፈልገን።

6. ፖለቱከኞቻችን በሆዳቸው ውስጥ የደበቁት በተለይ ጸንፈኛ ሃሳቦች ይታዩ። ስለ ምኒልክ ሃኡልት፤ ባንዲራ፤ የጊሳ አስተዳደር፤ ጎሰኝነት፤ ጨቋኝ ተጨቋ፤ እንዴት አብረው እንደሙሰሩ ወይንም እንደሙፋጁ ይጠየቁ። ይጋለጡ ይታወቁ።

7. የሚከሰሱት እራሳቸውን ከማስረዳት እድሉ ይሰጣቸው ሳይሰሹ ይጠቀሙበት።

8. ጎሳዬን ወክዬ እደራደራለሁ የሚለውን እስቱ የመደራደር አቅሙን እንይ። ወይንም የመጋጨት አቅሙን።

9. ፖለቲከኞቻችን በዚህ መልኩ ለረዥም ጊዙእ ሳይፈተሹ ምርጫ ከተጠራ ታላቅ አደጋ ይጠብቀናል።