አሳፋሪና አገር አፍራሽ ታሪካችንን እንዳንደግም ነው ይህን ጽሁፍ የምጽፈው። ታሪክ እንደመዘገበው ከኢህአዴግ ውጭ ያለነው ምሁራን፤ ፖለቲከኞችና ብዙሃን በፖለቲካ ረገድ ቁም ነገር ለማድረግ እድል ባጋጠመን ቁጥር እልዳችንን አበላሽተናል። በተደጋጋሚ ጊዜ ለአገራችን የፖለቲካ መስተካከል ከኢህአዴግም ይበልጥ እንቅፋት ሆነን ተገኝተናል። ይህን ደፍሬ መናገር የምችል ይመስለኛል።
አንዱ የድክመታችን ምክንያት ተልዕኮአችንን አለማወቃችን ወይም መርሳታችን ነው። ተልዕኮአችን የአገር ፖለቲካ ግንባታ ነው እንጂ የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአገር ፖለቲካ ስርዓት ግንባታ ሲባል ሁላችንም ስለ ህገ መንግስትን ማርቀቅ ነው የምናስበው። ግን ከዚህ ህገ መንግስት ማርቀቅ ስራ በፊት የልብ ለልብ መተዋወቅ፤ በተወሰነ ደረጃ መተማመን፤ መግባባትና መስማማት ያስፈልጋል። እነዚህ ለአገር ግንባታ የፖለቲካ ድርድር ቀድሞ ሁኔታዎች ናቸውና። አለነዚህ ማንኛውም በወረቀት ያለ ህግ፤ ምንም አይነት ወርቅ የሆነ ህግ ቢሆነም፤ በስራ ሊተገበር አይችልም።
ቀጥሎ በነዚህ ተመስርቶ ህገ መንግስትና ሌሎች የርዓይና የህግ ሰነዶች ይደነገጋሉ። ቅራኔ ወይም አለመግባባት ካለ በህግ መሰረት ይፈታል ህጉ ደግሞ በቂ ካልሆነ ያለው መተማንና ስምምነት ለፍትህ ይረዳል። የአገር የፖለቲካ ግንባታ ሂደት እንደዚህ ነው መሆን ያለበት።
የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የሚጀምረው የፖለቲካ ስረዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚመጣው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋም ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን ያንጸባርቃሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችላል ግን ምንም አይገነባም። እርግጥ መተማመንንና ውይይትን ይጎዳል ግን ከምርጫው በኋላ የደረሰውን ጉዳት ይጠግኑና የአገር ማስተዳደር ስረአቸውን ይጀምራሉ። ይህ ነው በተለምደው የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።
የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የፖለቲካ ስርዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚከተለው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋ ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን እያንጸባርቁ ይወዳደራሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችል ይሆናል ግን አገርን አይገነባም ይጎዳልም። ሰልዚህም ነው ውድድሩ ምርጫው ካለፈ አሸናፊዎቹ ውድድሩ ያደረሰውን ንዴት፤ ቂምና ጉዳት ይጠግን ዘንድ ትሸናፊዎቹንም መላው የአገሪቷን ህዝብ አንድ የሚያረግ እርቃዊ ንግግርና ተግባር የሚአደርጉት። ይህ ነው በተለምዶ የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።
ስለዚህ አገርን መገንባትና የፖለቲካ ውድድር የተለያዩ ባህሪያት፤ ተግባራትና ልምድ ያስፈልጋቸዋል። የአገር ግንባታ ሂደት እንደ መተማመን፤ ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ ቅራኔን መፍታት፤ ውይይት ወዘተ አይነቱ ባህሪያትና ልምዶች ያስፈልጉታል። የፖለቲካ ውድድር ግን ክርክር፤ ውድድር፤ ፉክክር፤ መካሰስ፤ ህግና ስረዓትን ዳር ዳሩን መጣስ፤ ወዘተ አይነቱን ልምዶች ያካትታል። በአገር ግንባታ ሂደት መካከል እነዚህን የፖለቲካ ውድድር ባህሪያትና ልምዶች ይዘን ከገባን አገርን መገንባት ሳይሆን ማፍረ ነው የምናደርገው።
ለዚህ ደግሞ በርካታ ታሪካዊ ምሳሌዎች አሉን። እስቲ ወደ 15 ዓመታት ወደ ኋላ ተመልሰን የ«ተቃዋሚ» ምሁራን፤ ጋዜጠኛና ፖለቲከኞች እያደረጉ፤ እየተናገሩ፤ እየጻፉ ምን እንደነበር እናስታውስ። ስራቸውን ባጭሩ ለመግለጽ «እርስ በርስ መበላላት» ማለት ይቻላል! ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ ከሚተቹት ይበልጥ እርስ በርስ ነበር የሚፋጁት። ጋዜጣ ላይ ቁም ነገር ሳይሆን ስድብና የመንደር ወሬ ነበር የሰፈነው። ከሞላ ጎደል ስራቸው 90% አፍራሽ 10% ገምቢ ነበር። ስለዚህም ነው ተቃዋሚው ጎራ ምርጫ '97 በግንቦት ሆኖ እሰከ የካቲት አካባቢ የትብብር መዋቅሮች ያላደራጀው! ለዚህም ነው ከምርጫው በኋላ ተቃዋሚዎች በቀላሉ የተበታተኑት። በበፊቱ ዓመታት እዱሉ እያለን ቅስ ብለን በትብብር ጉዳይ ተወያይቶ ትብብርን ከመፈጸምና ጠንካራ መሰረት የሆነ መዋቅርን ከመገንበት እንደ ምርጫ ተዋዳዳሪዎች እየተሰዳደብን ዋልን። ችግር ሲመጣ ለመቋቋም አቅሙ አልነበረንም። እርስ በርስ ተፋጅተን አለቅን። የግንባታ ስራ ያልተሰራባቸው ቅንጅትና ህብረት በቀላሉ ፈረሱ። የፖለቲካ መዋቅር ግንባታንና የፖለቲካ ውድድርን መለየት ያልቻሉትም ከፖለቲካ ወጡ። የህዝብም ትዝብት አደረባቸው።
በርካታዎቻችን በምዕራብ የሚዲያ ዜና፤ ትምህርትና ፕሮፓጋንዳ ስላደግን የነዚህ አገራት ፖለቲካ ስናይ ፖለቲካ እንደዛ መሆን እንዳለበት ይመስለናል። የናየው ደግሞ የፖለቲካ ውድድራቸውን ነው። ክርክሩን፤ ዘለፋውን፤ ስድቡን፤ ሴራውን ወዘተ። እኛም እንደነሱ ማድረግ እንወዳለን መሰለኝ። ግን ኢትዮጵያ ያለችበት ቦት፤ ለረዥም ዓመታት ያለችበት ቦታ፤ ገና የአገር ፖለቲካ ግንባታ ላይ ናት። ብዙሃኑም ልሂቃኑም የፖለቲካ መደቦቻችን እስካሁን በእምነት የተመሰረተ አገራቷን ምን መምሰል አለበት የሚል ሰፊ ስምምነት ላይ አልደረስንም። አሁንም ያለው ዋና ስራችን የህ ነው። አዎን ህገ መንግስት አለን ግን ሰፊው ርአይና ስምምነት የለንም። ነገ ኢህአዴግ ከስልጣን ቢወርድም ይህ ስምምነቱ ስለሌለ ሁከትና አብዮት ይከተላል።
በዚህ ምክንያት ሁላችንም፤ ምሁራን፤ ብዙሃን፤ ፖለቲከኛ፤ የመንግስት ሰራተኛ፤ ወዘተ ትኩረታችን ወደ አገር ግንባታ መቀየር አለበት። ይህ ማለት ከታች የተጠቀሱትን ለአገር ግንባታ አስፈላጊ የሆኑትን ብሃሪያት፤ ተግባሮችና ልምዶች ከራሳችን ጋር መዋሃድና በዚህ አስተሳሰብ ወደ ፊት መራመድ።
ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ መተማመን፤ በስነ ስረዓት መነጋገር፤ ውይይት፤ ቅራኔን መፍታት።
የሚቀጥለው ጊዜ አንድ ሰውን ወይም ቡድንን መዝለፍ ወይም መስደብ ካሰኘን ቆመን እናስብ። የፖለቲካ ውድድር ውስጥ አይደለንም። እንደዚህ አይነቱ ባህሪያት ታሪካችን እንደሚያረጋግጠው ሁላችንንም ጠርጎ ገደል ውስጥ ያስገባል አገራችንን ያፈርሳል። በሰላም እየተከባበርን እየተማመንን ነው መወያየት ያለብን። ይህ የሁላችንንም ጥቅም ያስከብራልና። ይህንን ብቻ ተግባራዊ ካደረግን አለ ምንም ጥርጣሬ ታላቅ አገር እንገነባለን ጠላት የምንላቸውም ምንም ሊጎዱንም አይችሉም።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ስምምነት. Show all posts
Showing posts with label ስምምነት. Show all posts
Tuesday, 20 February 2018
Tuesday, 8 November 2016
የሲኖዶሱ ጉዳይ በ2009
2009/2/29 ዓ.ም.
(2016/11/8)
እንደሚታወቀው
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን
ሁለት የተወጋገዙ ሲኖዶሶች አላት፤ በኢትዮጵያ
ያለው ሲኖዶስና ስደተኛው ሲኖዶስ። ይህ ሁኔታ
የተፈጠረው ኢህአዴግ ስልጣን ሲይዝ የቤተ
ክርስቲያናችን ፓትሪያርክ አቡነ መርቆርዮስ
በመሰደዳቸው ነው። ስለ መሰደዳቸው ሁኔታ
በዛን ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበሩት አቶ
ታምራት ላይኔ ከመንበር እንዲወርዱ ያዘዝኩት
እኔ ነኝ ብለው እንደመሰከሩ ይታወሳል። ምንም
ቢሆን በአቡነ መርቆርዮስ መሰደድና በአቡነ
ጳውሎስ መሾም መካከል ጳጳሳቱ የመንግስት
ጫና አድሮባቸው እንደነበረ ግልጽ ነው። ሆኖም
መንግስት በቤተ ክርስቲያን ላይ ጫና ሲያደርግ
ይህ የመጀመርያ ጊዜ አልነበረም። በደርግ
ጊዜም እንዲሁ ነበር፤ በኃይለ ሥላሴም፤ ከዛም
በፊትም በነግስታቱ ዘመን የቤተ ክርስቲያን
አገልጋዮች ጳጳሳቶችዋ ይህ ፈተና ሁልጊዜ
ዪደርስባቸው ነበር። ሆኖም የዛሬው ክፍፍል
ምንጭ ይሄው የመንግስት ጫና በሲኖዶሱ ላይ
በመሆኑ ነው።
ታድያ
መፍትሄው ምንድነው?
እንደሚታወሰው
በሲኖዶሶቹ መካከል እርቅ ለማምጣት በተለያየ
ጊዜ ግለሰቦችም፤ ሽማግሌዎችም፤ እንዲሁም
የቤተ ክርስቲያን ሃላፊዎች ሞክረዋል።
አንዳንዱም ሙከራ ጥሩና ያልተጠበቀ የማቀራረብ
ውጤቶችን አሳይተዋል። ግን እስካሁን ጉዳዩ
አልተቋጨም።
በዚህ
ጽሁፍ የጉዳዩን ጠቅላላ ይዞታ አልተችም፤
ጉዳዩና የእርቅ ስራው እጅግ ከባድና ውስብስብ
ናቸውና። በዚህ ጽሁፍ ከጉዳዩ አንዱን ንብርብር
ለመላጥ ነው የምሞክረው፤ ይህ ደግሞ ሲኖዶስ
ሊሰደድ ይችላል ወይ የሚለው ጥያቄ ነው።
ይህን
ጉዳይ ለዘብ ባለ መንገድ ከታየ ስምምነት ላይ
እንደሚደረስና ችግሩም መፍትሄ አንደሚያገኝ
እርግጠኛ ነኝ። ነገር ግን አክራሪ አስተያየቶች
ናቸው የሰፈኑት። እነዚህ «ሲኖዶስ
ሊሰደድ አይችልም»
እና
«መንግስት
ሲኖዶስ ላይ ጫና ካደረገ ፓትሪያርኩ ግድ
መሰደድ አለባቸው ስለዚህ ሲኖዶሱ ውጭ ይሆናል
ማለት ነው»
የሚሉት
ናቸው።
በመጀመሪያ
በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በማንም የኦርቶዶክስ
ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ሲኖዶስ መንቀሳቀስ
አይችልም የሚል ህግ የለም፤ ሊኖርም አይችልም።
ጣልያን ኢትዮጵያን ወርራ ከአንድ በስተቀር
ጳጳሳቱን በሙሉ ረሽና ቢሆን እኚህ አንድ
የቀሩት ጳጳስ ተሰደው ቤተ ክርስቲያኑን ካሉበት
ቢመሩ ህገ ወጥ ነው?
በፍጹም።
ግን ዋናው ጥያቄ ህገ ወጥ ነው ወይ ሳይሆን
ክርስቲያናዊ አይደለም ወይ?
ቤተ
ክርስቲያን በዚህ መንገድ እራስዋን ማዳንና
በጎቿን መጠበቅ አለባት። አንዳንድ ሁኔታ
መሰደድን ያስገድዳልም ይመክራልም።
እነዚህ
ሁኔታዎች ምን እንደሆኑ አስቀድሞ አይታወቅም፤
ጊዜው ሲደርስ ሁኔታው ተጠንቶ ነው መወሰን
የሚቻለው። ለዚህም ነው ከላይ ስለ ሲኖዶስ
መሰደድ ቤተ ክርስቲያናዊ ህግ ሊኖር አይችልም
ያልኩት። እንደ ሁኔታው፣ እንደ አደገኛነቱና
እንደ አስፈላጊነቱ ውሳኔው ይለያያል።
ለዚህ
እውነታ ጥሩ ምሳሌው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ሲኖዶስ
በ1910
በሩሲያ
ኮምዩኒስት አብዮት ምክንያት መሰደዱ ነው።
የሶቪዬት ኮምዩኒስት መንግስት በቤተ ክርስቲያንዋ
ላይ ያደረሰው ጥቃት እጅግ ከባድ በመሆኑ
ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ካህናትና አማኞች
በህሊናም ቢሆን ለማሰብ ያስቸግራል። በመቶ
ሺዎች የሚቆጠር ያህል ካህናት ናቸው በተለያየ
መንገድ የተገደሉት። ሌሎቹ በሞት እስር ቤቶች
ታሰሩና አብዛኞቻቸው ሞቱ።
በዚህ
ሁኔታ በ1913
የሩሲያ
ኦርቶዶክስ ፓትሪያርክ ቅዱስ ቲኾን ቤተ
ክርስቲያንዋ ታላቅ ችግር ላይ መሆንዋንና
የሶቪዬት መንግስት ካህናት እየገደሉ የራሱን
ካድሬዎች ካህን አድርጎ ወደ ቤተ ክርስቲያን
እያስገባ እንደሆነ ተገንዝበው በውጭ ያሉት
የተሰደዱት ጳጳሳት እራሳቸውን እንዲያስተዳደሩ
አዘዙ። ያሉበትን ሁኔታም ለመገምገምና ይህ
ውሳኔ ላይ ለመድረስ ሶስት አመት ፈጀባቸው።
ሲኖዶሱ፣ ማለትም ጳጳሳቱ በመንግስት ቁጥጥር
ስር እንደሆኑ ሲያውቁ ነው ፓትሪያርኩ ውጭ
ላሉት ጳጳሳት ካሁን ወዲያ በኛ መተማመን
አትችሉምና እራችሁን ቻሉ ያሏዋቸው።
ሆኖም
የውጩ ፓትሪያርክ ወዲያው አልተሾመም።
ፓትሪያርክ ቲኾን ከተሰዉ (አሁን
ቅዱስ ቲኾን ናቸው)
በኋላና
የሩሲያ (ሞስኮብ)
ሀገረ
ስብከት ከመጠን በላይ የካድሬ ግዛት ሲሆን
የውጭ ሲኖዶሱ ፓትሪያርክ ሾመ። ከዛ ቀጥሎ
እስከ 1999
የሩሲያ
የውጭ ሲኖዶስ (ROCOR)
እና
የሞስኮብ ሲኖዶስ ተለያይተው እንዲሁም ሲወጋገዙ
ቆዩ።
በ1999
ሁለቱ
ሲኖዶሶች ተታረቁ። የውጭ ሲኖዶሱ ከማን ጋር
ነው የትታረቀው፤ የሩሲያው ሲኖዶስ በካድሬ
የሞላ አልነበረምን ብላችሁ እያሰባችሁ ይሆናል።
በሚገርም ሁኔታ ካድሬ ያልሆኑ ታላላቅ
አባቶችና መነኮሳት አንገታቸውን ደፍተው
ከፖለቲካ ራሳቸውን አርቀው እየታሰሩ
እየተፈቱ እየተደበቁ የሶቪዬት ኮምዩኒስት
ዘመንን ያሳለፉ
ነበሩ።
አንዳንዶቹ ጭራሽ ራሳቸውን እንደ ካድሬ
አስመስለው ሌሎች ወንድሞቻቸው ካህናትን
ክጥቃት የመጠበቅ ስራ ይዘው ነበር። አሁንም
በሀገራችን በኢትዮጵያ
ከጳጳሳቱና ሀገረ ስብከቱ የካድሬ መንፈስ፤
የካድሬ ብቻ ሳይሆን ሲብስ የተራ ሙስናና
ሐጥያት መንፈስ፤
ቢኖርም ከዛ መካከል እጅግ ብፁ የሆኑ አገልጋዮች
እንዳሉ እናውቃለን። ካድሬ የሚባሉት ውስጥም
እንደሁላችንም ከራሳቸው ጋር እየተሟገቱ
ንስሀ እየገቡ እየወደቁ
እየተነሱ የሚኖሩ አሉ። በሩሲያም ሲኖዶስ
እንዲሁ ስለነበር
ነው እርቅ ላይ
ሊደርሱ የቻሉት።
በተዘዋዋሪ
በዚህ በሩሲያ ታሪክ ሌላ አስደናቂ ሁኔታ
ተፈጥሮ ነበር። በሁለተኛ የአለም ጦርነት
ጀርመኖቹ ለተወሰነ ጊዜ ምእራብ የሶቪዬት
ህብረትን ተቆጣጥረው የሩሲያ ኦርቶዶክስ
ሀገረ ስብከት የተዘጉትን በሺህ የሚቆጠሩ
ቤተ ክርስቲያኖችን እንደገና እንዲከፍት
ፈቀዱ። ከግድያ የተረፉት እውነተኛ የሆኑት
ካህናት ይህን ነፃነት ተጠቅመን ህዝቡን
እናገልግል ወይስ የሀገራችን ወራሪ የሰጠንን
ነፃነት ለክርስቶስም ቢሆን ልንጠቀምበት
አይገባም በሚለው ጥያቄ ልባቸው ተከፋፍሎ
ነበር። ምእመናኑ ሃይማኖቱ እጅግ ጠምቷቸው
ስለነበር በርካታ ካህናት ወደ ቤተ ክርስቲያኖቻቸው
ተመልሰው አገለገሉ። ጦርነቱ ሲይበቃም የሶቬት
መንግስት እንደዚህ አይነት ካህናትን እንደጠበቁት
እስር ቤት ላካቸው ወይም ረሸናቸው። (ስለዚህ
ታሪክ «ካህኑ»
የሚባለውን
የሩሲያ ፊልም እንድታዩ እጋብዛችኋለው፤
እጅግ አስተማሪ ነው።)
የሩሲያ
ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የመሰደድ ታሪክ
የሚያሳየን የሲኖዶስ መሰደድ ጉዳይ እንደ
በርካታ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ጉዳዮች
«ጥቁርና
ነጭ»
አይደለም።
እንዲህ ቢሆን ይሰደዳል እንዲህ ቢሆን አይሰደድም
የሚል አስቀድሞ ሁሉንም ሁኔታ የሚያካትት
ህግ የለም። እንደ ሁኔታው ነው ውሳኔ የሚወሰነው።
ታድያ
በኢትዮጵያ በ1983
የነበረው
ሁኔታ አቡነ መርቆርዮስ የሲኖዶስ መንበራቸውን
ይዘው እንዲሰደዱ ያስገድዳቸው ነበር?
ይህ
ጥያቄ እውነት ወይ ውሸት የለውም፤ እንደ
እያንዳንዱ ሰው አመለካከት ነው። አዎን
መንግስት በጳጳሳቱ ላይ ጫና እያደረገ ነው
ግን ያን ያህል ስላልሆነ መሰደድ አያስገድድም፤
ጳጳሳቱ ጫናውን ሊቋቋሙ ይገባል ማለት ይቻላል።
ወይም ጫናው የቤተ ክርስቲያኑን መሰረት
አናግቶታልና በነፃነት ምእመናኑን ለማገልገል
ሲኖዶሱ ከሀገር ውጭ መሆን ነበረበት ማለት
ይቻላል። ሁለቱም አስተያየቶች ያስኬዳሉ።
ከዚህ
መማር የምንችለው ታላቅ ትምህርት ሁሉም ነገር
እንደ ሃይማኖት ዶግማ ወይም ቀኖና ማየት
የለብንም። በነዚህ ታሪኮች አንድ እውነት
ብቻ ነው ያለው። ስለሆነም እነዚህን የመሰሉ
ችግሮችን እንደ ዶግማ እና ቀኖና እንደ
አስፈላጊነቱ የማይሻሻሉ አድርገን ማየት
የለብንም። ከሃይማኖታችን መሰረተ ትምህርትና
ስርዓት በቀር ሌላውን ጉዳይ በሙሉ በትህትና
ነው ማየት ያለብን። አቋሞቻችንንም በትህትና
መያዝና ሃሳቦቻችንን መቀየር መቻል አለብን።
ጥሩ ክርስቲያን አንድ አምላክ እግዚአብሔርን
እንጂ ሃሳቡን፣ የሚከተለውን ርዕዮት አለም፤
ወይንም አቋሙን አያመልክም።
በመጨረሻ
አንደ
ልጠቅስ
የምፈልገው ነገር
አለ፤ ሁለቱ
ሲኖዶሶቹ
ቢታረቁ
ለሀገራዊ እርቅ ሰላምና የመንፈሳዊ ደስታና
መረጋጋት ታላቅ ድል ይሆናል። በዛሬው
ኢትዮጵያ ህዝቡ ያጣው መሪ
ነው የሚባለው እውነት ነው። ልጄ ሲያድግ እንደ
ከሌ ቢሆንልኝ የሚባል መሪ በየትኛውም በመንግስትም
በሃይማኖትም በመሃበራዊም ዘርፍ የለም።
ከግዥ መደቡ ጥሩ ምሳሌ የሚባልና
የሚደነቅ የለም፤
ጭራሽ
ህዝቡ ሙስናና ተመሳሳይ መትፎ ስነ መግባር
ውስጥ ሲገባ መሪዎቻችንም ያደረጉታልና
ለምን እኛም
አናደርገውም እያለ
ነው። ስለዚህ እንደ ሲኖዶስ እርቅ አይነቱ
ዜና
ከቤተ
ክርስቲያን መሪዎች ቢመጣ
ለህዝባችን ታላቅ ምሳሌና
ለሀገራዊ እርቅ ታላቅ ድል ነው የሚሆነው።
ይህ
እርቅን
ለማምጣት ደግሞ በሃይማኖታዊም
በፖለቲካውም አቅጣጫ ቢታይ ከባድ ያልሆነ
ጥቅሙ ከጉዳቱ እጅግ ከፍ ያለ ነግር
ነው።
ከሌሎች ጉዳዮች ይልቅ
ብዙም ከባድ አይደለም።
እግዚአብሔር
ይህንን እርቅ
ለማድረስ
ልቦናውን ይስጠን።
Thursday, 27 October 2016
One Response to the ODF's “Our Common Future: A Proposal”
2009/2/17
(Ethiopian calendar)
2016/10/27
(European calendar)
(pdf)
[Note:
An Amharic version of this post will appear sometime!]
It
was with great pleasure that I read the Oromo Democratic Front's
(ODF)
discussion
paper “Our Common Future: A Proposal.” It has been a long time
since I read a
constructive and inviting paper from an Ethiopian political party, a
paper inviting us to do work rather than mire ourselves in
sloganeering and pity. I commend the ODF for their initiative, and my
aim here is to answer their invitation for a response to their
proposal. I am but an individual commentator, a mere layman
representing no one but myself, but I hope that my comments do the
proposal
some justice. I shall make my comments on the ideas in the proposal
based on the order they were presented in the paper.
I
fully agree with
the ODF that
a “country-wide
consensus” on Ethiopia is indeed urgently required, but
it has been urgently required for 22 years.
The
last 'consensus', the 1994 FDRE constitution was in my opinion too
radical and not consultative enough, and so we've been waiting for a
better one ever since. However,
such
consensuses are not created overnight, or in a conference or two. It
takes years
of discussion and deliberation to develop positions, let alone
agreements on such a complicated matter as a country's political
structure. It is remarkable that the Ethiopian opposition in all its
forms has for 25 years hardly made any progress in this matter. We
seem to be discussing the same issues over and over again, with the
same confrontational zero-sum
mindset as in the past. So we would all do well to heed what the ODF
recommends and begin work immediately on this “country-wide
consensus”.
Next,
the proposal frames the current political problem as one between two
opposing sides – the current regime as one side and those wanting a
“unitary
nation” as the other. It implies that
“core
Oromo demands” have
been
“sidestepped” or ignored in this debate. This
framing is, to put it bluntly, wholly inaccurate. First, though I'm
sure there are many that wish for a unitary nation, that is no
federal system whatsoever, they form a small minority. To illustrate
this, consider the official position of Kinijit and its successor
parties in this regard, which was to maintain the current (federal)
constitution
as it is for the foreseeable future, and past that, amend it as per
its own provisions! What
kind of amendment it would be was not
decided,
but there were many proposals, ranging
from
language-based federalism, which would be almost the same as the
current arrangement but simply replacing the concept of ethnicity
with language, to
federalism with states with redrawn boundaries removing
ethnicity entirely.
None
of this makes for a centralized
“unitary
nation” -- it
is at the very least federalism of some sort.
Given
Kinijit's large constituency as shown by its electoral victory, this
is the majority position, not that of a “unitary nation”.
Second,
unless I am mistaken, the main “core Oromo demand” is that the
current constitution actually be respected
rather than the EPRDF and TPLF in particular using its extrajudicial
power to exercise undue influence. This demand is not sidestepped and
has
not been sidestepped in the debate in
any way since all sides that have significant constituencies affirm
the current constitution as
a political reality, whether they like it or not.
I
would like to note here that if anything is being sidestepped it is
the core demands of the Ethiopian nationalists, since the status quo
already fulfils a large portion of the “Oromo demands”, which is
a multinational state! The status quo has already brought Ethiopia,
constitutionally speaking, from one extreme to the other extreme.
There is no possible going further! Thus Oromo demands in this regard
have been exceedingly fulfilled, save for the actual implementation
portion.
Other
demands, such as Oromiffa becoming an official federal language are
also supported by all major constituencies. All
this to say that talk about the “unitary nation” constituency is
a red herring, and therefore presenting the current regime and the
“unitary nation” constituency as the poles in the debate is
incorrect.
Instead,
the debate is multipolar, perhaps too multipolar. If we consider
Oromia as one constituency, we have in Oromia a spectrum all the way
from Ethiopian nationalists to soft Oromo nationalists to hardline
Oromo nationalists. These factions themselves have a lot to sort out
in terms of simply agreeing to disagree, let
alone being able to unite into one constituency.
Then
we have the Ethiopian nationalist constituency, which includes
perhaps most of Amhara region, but also that large disenfranchised
group of non-Amhara Ethiopians and mixed Ethiopians who consider
themselves not to be ethnic nationalists. This constituency is the
one that voted for Kinijit, and since its diversity means that it
does not have ethnicity as a binding material, so to speak, it is an
extremely fractious constituency. The inability of this constituency
to “avoid
the hair-splitting type of exchanges” and other dysfunctional
traits in order to reach a basic consensus has, in my opinion,
been the main reason for Ethiopia's current troubles and will end up
being the ruin of the nation(s).
Third,
there is the EPRDF,
which though
it has internal divisions is certainly the most united and coherent
constituency. As the ODF proposal says, the EPRDF is convinced, or
tries to convince itself, that there is no alternative to it. Well,
we
must admit that there is some
truth in this, and the ODF proposal is proof of this in that it
clearly outlines divisions in Ethiopian politics that have nothing to
do with the EPRDF. We all know that were the EPRDF to vanish today,
as the proposal implies,
there is no consensus among the rest of us, so there would be
anarchy. However, the lack of a consensus amongst the opposition has
not stopped the EPRDF from the
increasing
“social rejection” that
the proposal speaks of.
Indeed, if we look to the past, both the Haile Selassie and Dergue
regimes fell into some sort of anarchy, not into a ready opposition.
So a weak opposition is no guarantee of long life for the EPRDF –
it is only a guarantee of a hard fall. Thus the EPRDF had better
start doing something to actually aid the opposition to develop
rather than persecuting it.
Next,
I would like to comment on the ODF conviction that the current
constitution – Ethiopia as a multinational state – was
“unavoidable”, implying that it is Ethiopia's destiny and natural
state. Of course, it is the conviction of us Ethiopian nationalists
(non ethnic nationalists) that Ethiopia as a multinational state, let
alone being its natural state, is an unstable state ripe
for conflict.
Here we agree to disagree, but
as I stated above, as was Kinijit's official position, most
Ethiopian nationalists
accept political reality and work within the current constitution. I
would just like to add that talk of inevitability of the
multinational state completely ignores other factors in Ethiopia's
recent political past, including pseudo-feudalism, communism, and the
Cold War, all of which are not ethnicity and yet have played a
significant role in forming today's political reality. Ignoring these
factors is I think a misreading of history that affects our
perception of current political reality.
Now
on to the numbered sections of the ODF proposal. The first, about the
benefits of non-violent versus armed struggle is a case well made and
there is little to argue about here. We
agree to disagree with those who favour armed struggle! I
would just like to add a point about 'democracy'
however,
as the document states that one
thing all Ethiopian movements agree on is
the
goal of democracy. What
we laymen think of us democracy is one man one vote, which
immediately excludes group rights, especially huge group rights such
as ethnic rights. Our problem is precisely that we do not agree with
what democracy means and we cannot agree until we come to a general
consensus about what our country should look like – in other words
its constitution not only as it is formally written, but its
spirit. So the term democracy becomes, I believe, a distraction as we
work on the “country wide consensus” that this proposal advocates
for. If we keep talking about democracy, we'll end up with the same
problem as the Egyptian Arab Spring movement, which upon
realizing that what it thought was democracy ended up empowering the
Muslim Brotherhood a little too much
decided it didn't want democracy after all.
The
second section, on the divisive role of Ethiopian history, is
excellent. I
completely agree that short of some
sort of miracle, we are going to have to learn
to agree
to disagree about Ethiopian history. I actually think that reasonable
people can agree on a set of unbiased facts about Ethiopian history –
that's not the main problem. The problem is that we all
interpret these facts with our own
political
lens. Let's
take the simple example of the concept of the Oromo nation. The Oromo
in Ethiopia have at various times in history formed various nations,
perhaps even a single nation, been an integral part as an ethnic
group, not a nation, of the Ethiopian nation as we know it,
assimilated into and assimilated other groups, invaded and have been
invaded, terrorized and have been terrorized, etc. Most
reasonable people would agree on this set of facts. I
interpret this history as the Oromo being one of the ethnic groups in
Ethiopia while others interpret this as the Oromo nation being
distinct from what it calls Ethiopia, as having had various
interactions with Ethiopia, but as a nation unto itself. Same facts,
different interpretations, but these differences have major
implications on building the “country-wide consensus”.
The
good thing is that if
we “can agree to disagree with different readings” of Ethiopian
history, then we can take history out of the Ethiopian
nationalism vs ethnic nationalism debate, and this would greatly help
unfog the debate. The debate then will simply be about political
position rather than history, grievance, etc. This kind of
development is would not be new – the example of Canada and Quebec
is a case in point. The history of Canada is simple and
well-documented – there's not much to argue about its contents.
Quebec nationalists interpret
the history as that of a Quebec nation invaded and with
a right to
independence, while others view the history as a competition between
two North American colonialists which one party won and is a fait
accompli. Same facts, different interpretations. But the only
important fact here is that Quebec nationalists want independence
today, regardless of history, and the opposite side wants a single
Canada, regardless of history. It is current political competition
that drives the debate.
The
third section on self-determination is also excellent in that it
nicely breaks down a large idea – ethnic self determination in the
context of Ethiopia – into smaller principles that are much easier
to discuss and come to agreement on. I agree with all the premises
as
they apply
in
this context. (I disagree with “being an Oromo was officially
portrayed as antithetical to being an Ethiopian”, but that's not
one of the principles, just
an aside.) However, there is more to go – it is a bare minimum, not
surprisingly, as this is proposal is just a starting point. One
can
agree with all the premises, as
I do,
yet disagree on
their political interpretation,
as
I do with the interpretation of the ODF.
Finally,
the fourth and fifth sections dealing with the zero sum attitudes
in Ethiopian politics, particularly as it relates to demonizing
opponents and lacking empathy. The proposal makes it clear that in
order to properly learn from the past, we have to empathize not
only with current opponents but with
past actors and understand why they did what they did. If we do so,
we will realize that there was and in the case of the EPRDF there
is
some good that they have done, and these should be built
upon, rather than everything having to be torn down and built up
again.
I
completely agree with these thoughts. The
zero sum mentality means for a complete absence of introspection,
which in turn means continual conflict. With a little bit of empathy
and introspection, much of the current conflict would be easily
transformed. I think
Ethiopians have to start giving the saying 'a people get the
government they
deserve' much more weight than we currently do. As
I am fond of saying, much of the reason Ethiopia today has an
ethnic-based constitution that Ethiopian nationalists do not like
(but accept!) is because Ethiopian
nationalists committed political suicide over the two decades
before the new constitution was formed, so that they were unable to
be at the table. Yet we Ethiopian nationalists continue to blame the
EPRDF for it, as
if the EPRDF could suddenly reverse its cherished ideology and
take a huge political risk once
in power! Unfortunately, it is
this
focus on continually
blaming the
EPRDF for
everything that has kept us unable
to fix our own problems and
therefore kept us weak and inept.
In
conclusion, I think the ODF proposal is an excellent document that
all stakeholders in Ethiopian politics should read, discuss, and
build upon.
However, let us reflect on why previous such attempts, such as
Medrek, for example, have stuttered and failed, and learn from those
mistakes. Also, let us ask ourselves where the other stakeholders are
while the grassroots, leaderless, is up in arms.
Subscribe to:
Posts (Atom)