Showing posts with label የትግሬ አድሎ. Show all posts
Showing posts with label የትግሬ አድሎ. Show all posts

Thursday, 30 August 2018

የአጥንት ቆጠራ ወይንም የአድሎ ማስተካከያ?

ጃዋር መሃመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሱ እና ለሌሎች ያቀረበለት የሠራተኞቹ ጎሳ ሰነድ (https://www.facebook.com/Jawarmd/posts/10104092557488783) አሳይቶናል።

ጥሩ ነው። ይህ ጉዳይ በኢትዮጵያ ፖለቲካ መነሳቱ አይቀርም እና መወያየቱ ጠቃሚ ነው።

ሆኖም ይህ ሰነድ የተሟላ አይደለም። የሠራተኞቹ ብሄርን ነው ወይንም የትውልድ ወይንም የመኖርያ ክልልን ነው የሚያሳየው ግልጽ አይደለም። የተጻፉት ክልሎች ናቸው፤ «ሌላ»፤ «ደቡብ ክልል»፤ «ኦሮሞ ክልል»፤ «አማራ ክልል» እና «ትግራይ ክልል» ነው።

ግን ይህን አይተን ሠራተኞቹን በመጡበት ክልል ነው ያስቀመጧቸው ለማለት ይከብደናል ሌሎች ክልሎች በተለይ አዲስ አበባ ክልል ስለሌሉበት! «ክልል» ብለው ጻፉት እንጂ «ብሄር» ማለታቸው ነው ከሆነ ደግሞ ለምን እንደዛ አላሉትም ማለት ይቻላል። አየር መንገዱ ሠራተኛ ሲቀጥር ብሄሩን እንደ መረጃ ያስቀምጠዋል ወይ የሚለው ጥያቄም ይነሳል።

ስለዚህ ስለዚህ ሰነድ ከመወያየታችን በፊት ሙሉ መረጃ ያስፈልጋል። ያንን ከአየር መንገዱ ወይንም ከአቶ ጃዋር (ነግረውት ከሆነ) ካላገኘን ዋጋ የለውም።

ግን በጠቅለል ያለ መልኩ ስለ «ኮታ» (በጎሳ፤ በጾታ ወይንም በመደብ የሥራ ወይንም የትምሕርት እድል መመደብ) ያለኝን አመለካከት ልግለጽ… ጠቃሚ ከሆነ። ይህ አካሄድ አደገኛ እና ህዝብን የሚያከፋፍል መሆኑ ምንም ጥያቄ የለውም። የግጭት ምንጭ መሆኑ ኢትዮጵያም የትም የታየ ነው።

ሆኖም አድሎ የትም ቦታ ያለ ነገር ነው። ኦሮምያ ያደገች አማርኛ በደምብ የማትችል ሴት ለአየር መንገድ የአስተናጋጅ ስራ ስትወዳደር በአማርኛ ጉድለቷ ትቸገራለች። ብቁመቷም ልትቸር ትችላለች። ምናልባት በተፈጥሮ ሳቂታ ከሰው ጋር በቀላሉ የምትግባባ ላትሆን ትችላለች። መልኳም «እስከዚህ» ሊሆን ይችላል። ወዘተ። ብዚህ ዓለም «እኩልነት» የለም። የሰው ልጅ አብዛኛውን ማንነቱን ይወርሳል በትንሹ ነው የራሱ ሚና ያለበት።

እንዲህ ሆኖ መንግስት ወይንም ሌላ ተቋማት እኩልነት ውየን "fairness" ለማምጣት ጣልክቃ ገብተው ኮታ ቢጠቀሙ ይጠቅማል ወይ? እኔ የሚሻለኝ መሰረታዊ ችግሮቹ ላይ ብናተኩር ነው። የቋንቋ ችግር ካለ ይፈታ። የአድሎ ችግር ካለ ይፈታ። ቁጥር ላይ ማተኮሩ ወይንም ኮታ እንዳ አንድ መሳርያ መጠቀሙ ጉዳቱ ከጥቅሙ ያይላል ብዬ ነው የምገምተው።

ይህን ለማየት ለጀዋር ጽሁፍ የቀረቡትን አስተያየቶችን ማየት ይበቃል! ጉድ ነው ግን ያልተጠበቀ አይደለም። እስቲ ጉዳዩን ሰክን ብለን እናስብበት። በደመነፍስ አንግባበት።

በመጨረሻ ስለ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ትግሬ ብቻ ሆኗል የሚለው ዘፈን አንድ ነገር ብል ደስ ይለኛል። ትግሬዎች አላግባብ ተቀጥረው ይሆናል ቢሆንም አይገርምም እንደማንኛውም መስሪያቤት አየር መንገዱም ብዙ ሰው የሚቀጥረው በትውውቅ ነው። በህወሓት አገዛዝ ዘመን ይህ የትውውቅ ድር (network) ወደ ትግሬዎች ማዳላቱ ምንም አይገርምም። መሰረታዊ ችግሩ የህወሓት አገዛዝ ነው እንጂ ትግሬዎች አለአግባብ መቀጠራቸው አይደለም። መሰረታዊው ችግር ከተፈታ ሌላውም ይፈታል።

እኔ የትግሬ አድሎ አለ ብዬ ማልቀስ ድሮም ወድጄ አላውቅም (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/04/blog-post_16.html)። ማልቀስ እና ማማረር ሽንፈት ነው የበታችነት እና የዝቅተኝነት ስሜትን (inferiority complex) ያዳብራሉ። ሃላፊነት-ቢስ ያደርጋሉ። ሰውን ተግባራዊ ስራ ከመስራት ወሬ ብቻ እንዲሆን ያደርጋል። Empower ከማድረግ disempower ያደርጋል። ይህን ችግር አንድ በደንብ የሚያሳየን ነበር አሁንም ህወሓት ከስልጣን ከወረደ በኋላ ሰዎች ስለ ትግሬ አድሎ በማሰብ ጊዜአቸውን ሲያባክኑ ነው። ወይንም ስለ በረከት ስምዖን ሲያወሩ። አዎ ሰው ቅስለኛ ነው ግን ክብሩንም ያጣ ይመስለኛል።

Sunday, 28 January 2018

ትግሬዎች እየተጠቁ ነው?

ይህንን ታሪክ ደጋግመን አይተነዋል ብቻ ሳይሆን አሳልፈነዋል። የጎሳ ፖለቲካ በአገራችን ጎልቶ መታየት ከጀመረ ወዲህ፤ ከነጀብሃ፤ ሻብያ፤ ህወሓትና ደርግ ዘመን ጀምሮ የተደጋገመ ታሪክ ነው። በነጻነት ወይም ፍትህ ወይም «መብት» ጥያቄ ይኖራል። የሚጣሉት ጎራዎች በጥያቄው ላይ ከማተኮር ጉዳዩን ወደ ጎሳን ወይም ዘርን ያዞሩታል። ለጎሳ ጥል ምክንያት ይጠቀሙበትና የነጻነት ወይም ፍትህ ወይም መብት ጥያቄው ቀርቶ የጎሳ ውግያ ይሆናል። ጎሰኝነትን እንደ መሳርያ ይጠቀሙበታል አገርን ያጠፉበታል። (ይህን ስል በመጀመሪያ የተነሱት ጥያቄዎች መሰረተ ቢስ ነበሩ ማለቴ አይደለም ወይም በጎሳ ወይም ቋንቋ ዙርያ ችግር አልበረም አልልም። ሆኖም ጎሳ እንደ መሳርያ መጠቀም አላስፈላጊና ጎጂ ነበር፤ አሁንም ነው።)

ዛሬ በኢትዮጵያዊያን ብዙሃን በትግራይ ቅሬታ መኖሩ የማይካድ ነገር ነው። ዲያስፖራ የሚኖር ካልሆነ የትም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ይህን ሃቅ በየቀኑ የሚያየውና የሚኖረው ነው። ይህ በትግሬዎች ላይ ያለው ቅሬታ ደግሞ በተቃዋሚ ወይም «ፀረ ሰላም ሃይሎች» የተቀሰቀሰ አይደለም። (ተቀዋሚዎች ምንም ለመቀስቀስ አቅሙም ትብብሩም የላቸውምና።) ከሊስትሮው እስከ ሃብታም ነጋዴው እስከ የቤት እመቤቷ እስከ ካህኑ እስከ ተማሪው ይህንን የቅሬታ ስሜት አለው። ያሳዝናል ግን ያለ ነገር ነው። የጎሳ ጉዳይ ሳይሆን የፖለቲካ ጉዳይ ነው መሆን የነበረበት፤ ሰውዉ ስለትግሬ ሲአማርር «ተውዉ፤ ገዥ መንግስቱ ሌላ ፖለቲካ ስለማይፈቅድ ብቸኛ ስልጣን ስለያዘ ነው ግፍ የበዛው» ብዬ ለማስረዳት ብሞክር ማንም አይሰማም። ሰውዉ በትግሬ በላይነት አምኖ ሌላ ነገር አይሰማም።

መንግስትንም ያስጨነቀው ይህ ነው። ከመሪ ወይም ተቃዋሚ መደብ ሳይሆን የብዙሃኑ የህዝቡ ብሶት እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው መንግስት ለውጥ ለህልውናው ግድ እንደሆነ አምኖ እርስ በርሱ የሚወያየው።

በዚህ ሁኔታ ትግሬዎች አለ አግባብ ተጥቅተዋል ገና ሊጠቁም ይችላሉ። ጥያቄ የለውም። (እዚህ መጥቀስ የምፈልገው ግን እድሜ ለብዙሃኑ ታሪካዊ ዝንባሌ ጎሰኝነት እንደ የ27 ዓመታት የኢህአዴግ ፕሮፓጋንዳ ያህል አያጠቃውም። ሆኖም ያለውም መጠን ችግር ነው።) ግን ይህ ፍግ መቆም አለበት፤ ትግሬ መጠቃት የለበትም ብሎ መጮህ ምን ዋጋ አለው? ማን ይሰማናል? ከላይ እንደጠቀስኩት ህዝቡ ትግሬዎች አንደኛ ዜጋ ናቸው ሌሎቻችን ሁለተኛ ዜጋ ነን ብሎ ደምድሟል። አይደለም የፖለቲካ ጉዳይ ነው፤ አማራ ክልል ጭቋኙ አማራ ነው ኦሮሚያ ጮቋኙ ኦሮሞ ነው ብንል አልሰሙንም አሁንም አይሰሙንም።

ስለዚህ መፍትሄው ከተቃዋሚ ወይም «ኢሳት» ወዘተ እጅ አይደለም። መፍትሄው ከመንግስት ብቻ ነው መምጣት የሚችለው። መንግስት ዙሪያ ያለነው በሙሉ ሃይላችን መንግስት የሚያስፈልገውን ለውጦች እንዲያመጣ መግፋት አለብን። በተለይ ለተጋሩ መጠቃት ዋናው መፍትሄ የመንግስት የጎሰኝነት አቋምና ፕሮፓጋንዳውን መቀየር ነው። በህዝቡ ልብ የ26 ዓመታት የጎሳ ስሜት በመሸርሸር ነው ያሉትን ቅሬቴዎች ከጎሳ ወደ ፖለቲካ መቀየር የሚቻለው።

አንድ ነገር መርሳት የለብንም። ይህንን ትጠንቅቃችሁ እንድታነቡ ብትህትና እጠይቃለሁ። የኢህአዴግ አቋም፤ በእርግጥ አብዛኛው የተማሪዎች የፖለቲካ ንቅናቄ አቋም፤ የኢትዮጵያ የፖለቲካ መሃበራዊና ኤኮኖሚ ቅሬታዎችና ችግሮች በጎሳ የተመሰረቱ ናቸው ነው። ይህ ነው የኢህአዴግ አቋም። ጭቆና አለ? የጎሳ ችግር ነው። እኩልነት የለም? የጎሳ ችግር ነው፡ ድህነት አለ? የጎሳ ችግር ነው። የጎሳውን ችግር ከፈታን ሁሉም ይፈታል። ታድያ ዛሬ ህዝቡ ችግራችን በሙሉ በትግሬ የበላይነት ምክንያት ነው ካለ በትክክል የኢህአዴግን አቋም ነው የሚያንጸባርቀው ማለት አይደለምን?! የጎሳ ፖለቲካ እንዴት አደገኛ እንደሆነው አያችሁ። ትግሬዎች ደግሞ መልሳቸው የምንጠቃው በኢህአዴግ ብቸኛ ስልጣን በመያዝ ሳይሆን በትሬነታችን ነው ብለው ይመልሳሉ። ምን ይደረግ፤ ችግሩን ወደ ጎሳ በማውረድ አብሮ ገደል መግባት ነው።

ስለዚህ ብእራችንንና ድምጻችንን አቅመ ቢስ የሆኑት ትቃዋሚና «አክቲቪስት» ላይ ከማባክን መንግስት አቋሙን እንዲቀይር ብለን እናሳምነው። መንግስት የሃሳብ እርዳታ ያስፈልገዋል። የ40 ዓመት ጣኦት የሆነ ርዕዮተ ዓለሙን መቀየር እጅግ ከባድ ነውና መንገዱም በጥንቃቄ የተአሰበበትና የታቀደ መሆን አለበት።

በትግሬ በትግሬነቱ የሚደርስበት ጭቆና ይውደም! የሚያወድመው ግን የኢህአዴግ የውስጥ ለውጥ ነው።

Monday, 10 October 2016

የትግሬ አድሎ

2009/1/29 .. (2016/10/9)

(pdf)

ፖሊሱን ምንድነው የሚያበሳጭህ ብዬ ስጠይቀው እንደዚህ ይለኛል«አድሎው በዛ፤ እድገት «ለነሱ ሰው» ብቻ ነው፤ ምርጥ ቦታ «ለነሱ»የማይፈለግ ስራ ለሌላው። አይን ያወጣ ነው እኮ! ሰዉ እጅግ መሮታል»

ለመንግስት እቃ የሚያቀርብ ነጋ እንደዚሁ ብሎ ይነግረኛል«ኮንትራቶች አገኛለሁ። ግን ምርጥ ኮንትራቶች «ለነሱ» ብቻ ነው። ጊዜ ቢያሳልፉም ጥራት ቢያጎሉም ምንም አይባሉም እንደ በፊቱ አይደለም፤ አሁን አይን ያወጣ ሆኗል፤ ሰ በጣም ተናዷልና ሁኔታው ያስፈራል»

ባለ ሀብቱም እንደዚሁ አይነት እሮሮ ያሰማኛል«አዎ ደህና መሬት ማግኘት ለሁ ግን ምርጥ ቦታዎቹ «ለነሱ» ሰው ነው። አንድ ቆንጆ ቦታ አግንቼ ከፍተኛውን ብር ተጫርቼ «ለነሱ» ተሰጠ። እጅግ ተበሳጭቻለሁ። አይን ውጣ አድሎ ነው» ይለኛል። በተዘዋዋሪ ይህ ባለ ሀብት ከ ፓርቲው ጋር በሚያስፈልገው ደረጃ ግንኙነት አለው

የዩኒቨርሲቲ ተማሪውም ከትንሽ ውይይት በኋላ ወደዚሁ አርእስት የገባል። «የነሱ» ተማሪዎች የሚያገኙትን እርዳታ ብታይ። ትርፍ ትምህርታዊ ምክር፤ ሳምፕል ፈተናዎች፤ ከነሱ አስተማሪዎች በትርፍ ግዜ እርዳታ» ዝምብሎ ከማማረር ለምን እናንተም እንደዚህ አታረጉም ብዬ ጠይቀዋለሁጥያቄዬን ያልፈዋል፤ ስለ «እነሱ» ነው ማውራት የሚፈልገው

«እነሱ» ማን እንደሆኑ ሁላችንም እናውቃለን። አዎ በትክክሉ ለመናገር የኢህአዴግ አባላትና አደርባዮቻቸው ናቸው። ግን ሰ«እነሱ» ሲል ባጭሩ ትግሬዎች ማለቱ ነው፤ አድሎ ሲል የትግሬ አድሎ ማለቱ ነው።

እውነቱን ለመናገር የትግሬ አድሎ ገርሞኝም አያቅም። የመንግስታችን አወቃቀር ይህን አድሎ የሚያስከትል ነውየአንድ ፓርቲ አገዛዝ ነው ያለንፖለቲካ ተቀናቃየለም አይፈቀድምም። እንኳን የነፃ ምርጫ ከፊል ነፃ ምርጫ የለም። በዚህ አይነት «አውራ ፓርቲ» አገዛዝ ሁልግዜ ለፓርቲ አባላትና አደርባዮቻቸው ከፍተ አደሎ ይኖራል። በደርግ ዘመን ለኢሳፓ አባላት አድሎ አልነበረም? በኃይለ ስላሴ ዘመን ከቤተ መንግስት ግንኙነት ያላቸው የተሻለ ያገኙ አልነበረም? የዛሬውም እንደዚህ ነው።

ይህን ሃሳብ ስናገር አብዛኛው አዳማጭ ይገረመዋል«የዛሬው አድሎ ግን በዘር ነው እኮ» ይሉኛል። አዎን የዘር አድሎ ነው ግን ህይ የዘር አድሎ፤ ማለት የትግሬ አድሎ፤ መኖሩ ልንገረም አይገባም። ሁላችንም የኢህአዴግ ታሪካዊ አመጣጥን እናውለን። ከመጀመሪያው ህውከኢህአዴግ ከፍተኛ ኃይል ያለው ፓርቲ ነበር ዛሬም ነው፤ ቶር ስራዊቱንና በተለይ ደህንነቱን እንደሚቆጣጠር እናውቃለን። ደግሞ በአንድ ግንባር ወይም ፓርቲ አገዛዝ ከዛ ፓርቲ ውስጥ ኃይል ያለው ቡድን ይበልጥ ስና አድሎ ይታይበታል! ለምን ቢባል ሙስናና አድሎ ዋና የኃይል ማከማቸትና ማንጸባረቅ መንገድ ናችሀው። ምርጫ ወይም የፖለቲካ ውድድር ሰለሌለ ኃይል በዚህ መልኩ ነው የሚከማቸው። በአውራ ፓርቲ አገዛዝ ሌላ አካሄድ ሊኖር አይችልም

ይህ ሁሉ እያልኩኝ ሳለ ኔ አመለካከት የትግሬ አድሎ ካሉት የሀገራችን የፖለቲካና ህብረተሰባዊ ችግሮች ንሹ ነው። ለኢህአዴግ ግን ዋናው ችግ ነው! ይህ እንዴት ይሆናል? ለኔ ዋናው ችግር የአንድ ፓርቲ የልማት መንግስት አገዛዙ የህዝቡን የአንድነትና የህብረተሰባዊ መንፈስ እያጠፋ መሆኑ ነው። ከሌሎች ጽሁፎች እንደጠቀስኩት የኢህአዴግ መንግስት ለህዝቡ ያቀረበው ውል እንዲህ ነው፤ ልማት ሰጥሃለሁአንተ ደግሞ በልጣኔም ይሁን በሙስናዬ አትምጣብኝ። በዚህ ውል መሰረት ሰዎች ከመሬታቸው ይፈነቀላሉ። መሬታችሁ ለባለ ሀብት ይፈለጋል እየተባለ ሳንቲም ተሰተው ይባረራሉ፤ ክስ ላይ ባለስልጣኑ ወይም አደርባዩ ጥፋተና ቢሆንም ይረታል፤ ሰዎች ትንሽ ጸረ ኢህአዴግ ነበር ቢናገሩ ይታሰራ ህዝቡ ከፍርድ ቤት ፍትህ አያገኝም ጉቦ ካልሰጠ ውይም ወዳጅ ከሌለው ንብረቱን ስራውን ወዘተ ያጣ ይችላል። ለኔ እነዚህ ችግሮች ከትሬ አድሎ እጅግ የሚበልጡ ናቸው። ፍትህ፤ ነፃነት፤ ወዘተ አለመኖራቸው ነው ዋናው ችግር። ሁለተኛ ደረጃ ችግር የማንም አድሎ። ሶስተኛ ደረጃ ችገር የትግሬ አድሎ ነው

በተዘዋዋሪ ባለንጀራችን መሬቱን ሲቀማ፤ አለ አግባብ ሲታሰር፤ ፍትህ ሲያጣ፤ ወዘተ ማንኛችንም ዞር ብለን እንርዳህ አንለውም። አይዞህ ብለን የገንዘብም ወይም ሌላ ድጋፍ አንሰጠውምየራሳችንን ኑሮ፤ የራሳችንን«ልማት» ድርሻ እያሳደድን ባለንጀራችን እየተጎዳ ዝም እንላለንምንስት ላይ ጮኸን እንታሰር አደለም። እንርዳው፤ ግን አንረዳውም። ታላቁ ችግር ይህ ነው። እውነቱን ለመናገር ኢህአዴግን በስልጣን እስካሁን የጠበቀውም ይህ መንፈስ ነው።

ግን ይህ መሰረታዊ ችግር እያለ መንግስቱን የሚያናጋው የዘር ችግሩ ነው። ይህ የሰውን አስገራሚ ባህሪ ያሳያ። «ሀገሬን በዚህም በዛም አበላሽ ግን በዘሬ አትምጣብኝ! ጉቦኛና ዘራፊ ሁን ግን በዘር ስም አታድርገው!» እኛ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እንላለን። ያሳዝናል።

ይህን አውቆ ኢህአዴግ የዘራውን ነው የሚያጭደው። ግን ለሀገሪቷ ህልውና አይበጅም። እኛ የ«ትግሬ አድሎ» ሳይሆን ምንም አይነት «አድሎ»ን አንፈልግም ስንል ነው ሀገራችን የሰላም መንገድ የምትጀምረው።