Showing posts with label ፑቲኖቻችን የት አሉ. Show all posts
Showing posts with label ፑቲኖቻችን የት አሉ. Show all posts

Wednesday, 31 January 2018

ዳግም ጥሪ ለኢትዮጵያዊ ምሁራን

ውነቱን ለመናገር ጥሪው ለምሁራን ብቻ ሳይሆን ለሁሉም አቅም ላለው መሆን አለበት። መልካም ለውጥ ለኢትዮጵያ የሚመጣው ከነ ለማ መገርሳ፤ አቢይ አህመድና ገዱ አንዳርጋቸው አይነቱ ጋር አብሮ በመስራት ነው። እነዚህ ማድረግ የቻሉት ዋናና የተለየ ነገር ካለው መዋቀር ውስጥ ሆነው እንደ እባብም እንደ እርግብም ሆነው መስራትና መታገል ነው። አሁን ደግሞ የኛ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ጭብጨባና አጉል ሙገሳ ሳይሆን እርዳታ ነው እጅግ አንገብጋቢ ሆኖ የሚያስፈልጋቸው። የኢህአዴግን መርከብ ወደነሱ አቋም ለመምራት በርካታ አብረዋቸው የሚሰራ የሰው ሃይል ("critical mass") ያስፈልጋቸዋል። እርግጥ ኢህአዴግ ውስጥ ሌሎች የነሱ አይነት የፖለቲካ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ይኖራሉ። ነገር ግን ቁጥራቸው ለውጥ ለማምጣት በቂ አይደለም። ተጨማሪ የሰው፤ የሃሳብ፤ የሃይልና የአቅም ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።

ስለዚህ ፖለቲካ ውስጥ አልገባም፤ ኢህአዴግ ውስጥ አልገባም፤ ሀገር ውስጥ አልኖርም ወዘተ የምንለው በአስቸቋይ ስሜታዊነታችንን አሸንፈን ወደ ሀገር ወደ ፖለቲካ መዋቅር በተለያየ መስፈርት መጠጋት አለብን። «አደገኛ ነው» «ዋጋ የለውም» «አይሰራም» ትሉኛላችሁ? ብላችኋልም ለዓመታት። ግን እድሜ ለእነ ለማ መገርሳ ይህ አስተያየት ውድቅ እንደሆነ ተረጋግጧል። ብልህ ከሆንን፤ ጸንፈኛ ካልሆንን፤ ትህትና ካለን፤ የሃሳብ መቀየር አቅም ካለን፤ አብሮ መስራት ከቻልን ይቻላልም ይሳካል። ለችግራችንም መፍትሄ ይሆናል።

ይቻላል ብቻ ሳይሆን ምናልባትም ብቸኛ መንገዱ ይህ ከውስጥ መስራት ነው። ከመዋቅሩ ውጭ ወይም ይባስ ከሃገር ውጭ ሆኖ ደህና ለውጥ ማምጣት እንደማይቻል የርዥም ዓመታት መረጃ አለን። «ተቃዋሚ» የምንባለው ባለፉት 40 ዓመታት ታሪክ ምክንያት እጅግ እንደደከምንና አቅም እንዳጣን ይታወሳል። ስለዚህ ያንኑ የማይሰራ ዘዴ ከመሞከር፤ ጭንቅላታችንን ደጋግመን ከድንጋይ ግድግዳ ጋር ከማጋጨት ሌላ ደህና የመሳካት እድል ያለውን መንገድን መሞከር ተገቢ ነው። ይህ ደግሞ ካለው መዋቀር ውስጥ በዘዴ እንደነ ለማ መገርሳ መስራት ነው

ስለዚህ አቅም ያላችሁ ተሳተፉ። አትፍሩ። እራሳችሁን ሳታጋልጡ በአቅማችሁ ስርስራችሁ ግቡ። ካቃታችሁ ሽኩም ይበዛብኛል ካላችሁ ይሁን፤ ይህ ስራ ለሁሉም የሚሆን ያደለም። ግን ቢያንስ አይቻልም አትበሉ። እኔ አልችልም እንጂ ይቻላል በሉ። ተስፋ ቆራጭ አትሁኑ። እነ ለማ የጀመሩትን እናንተም መከተል ትችላላችሁ!

Saturday, 27 January 2018

እንሆ ፑቲኖቻችን!

አንድ አመት ተኩል ይሆናል ርእሱ «ፑቲኖቻችን የት አሉ» የሆነውን ጽሁፍ ከጻፍኩኝ። እንሆ በነ ለማ መገርሳ፤ አቢይ አህመድና ሌሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ይህንን የፑቲን ሚና ሲጫወቱ እናያለን። እንኳን ለዚህ አደረሰን!

ለማስታወስ ያህል የ«ፑቲን» ብዬ የሰየምኩት የፖለቲካ ሚና ባለው የፖለቲካ ሥርአት ውስጥ ሆኖ ውስጥ ለውስጥ በስውር ራሰን አለጊዜው ሳያጋልጥ ለውጥ ማምጣት ነው። የሩሲያው ቭዲሚር ፑቲንን ታሪክ ለማስታወስ ያህል አቋሙን በሚጠላው የድሮ አለቃው ቦሪስ ዬልትሲን መንግስት ይሰራ ነበር። አቋሙን በሞላ ጎደል ደብቆ እራሱንም የሱ አይነት አቋም ያላቸውን ባልደረቦቹንም ሰውሮ ውስጥ ለውስጥ ተደራጀና የአለቃው ዋና አጋዥ ሆነ። ዬልትሲን ከስልጣን ሲወርድ ጭራሽ ፑቲንን ሾመና እንደሚባለው «ሌላው ታሪክ ነው» ፑቲን የሩሲያን የፖለቲካ ሁኔታ በትክክሉ ገምቶት ነበር፤ እራሱን ከሥረዓቱ ውጭ አድርጎ ምንም አይነት ለውጥ ሊያመጣ እንዳማይችል ገብቶቶ በበር። ይገደል ነበር ወይም ከሀገር ይባረር ነበር። ሌሎችም የሱ አጋሮች ይህንን ተገንዝበው ውስጥ ሆነን በትዕግስት እራሳችንንም ንቅናቄያችንን አደራጅተን ጊዜው ሲደርስ በልጠን እንገኛለን ብለው ወሰኑ። እንዳሰቡት ሆነ።

እነ ለማ መገርሳም እንደዚህ ነው ያደረጉት። ጊዜው ሳይደርስ አጉል የፖለቲካ እርምጃ በመውሰድ ከጨዋታው ከሚፈነገሉ ቀስ ብለው አንገታቸውን ደፍተው ድራቸውንም የፖለቲካ ኃይላቸውንም አጎልብተው አሁን ትልቅ ሚና መጫወት የሚችሉበት ደረጃ ደረሱ። (ሌሎቻችን አክሩፈን ከስርአቱ ውጭ ሆነን ምንም ሳናደርግ እነሱንም ሳንረዳ።)

አሁንም ግን እነ ለማ እጅግ ከባድ መንገድ ነው የሚጠብቃቸው። መአት ተቃዋሚና ጠላቶች አሏቸው ከኢህአዴግ ውስጥ ከህወሓት ውስጥ ከኦህዴድም ውስጥ። ደጋፊዎቻቸውን ማብዛት ተቃናቃኞቻቸውን ማድከም ከባድ ስራ ነው የሚሆነው። ይበልጥ ደግሞ ዝም ያለውንና መሪ ቢስ የሆነውን ብዙሃኑን ማደራጀትና ወደ አንድ አቅጣጫ መምራት እጅግ ከባድ ስራ ነው። እግዚአብሔር ይርዳቸው፤ በነሱ ቦታ መሆን በፍጹም አልመኝም።

እዚህ ላይ ሁላችንም የኢትዮጵያ አንድነት፤ የአገር ብሄተኝነት ወዳጆች ችግራቸውንም አቅማቸውንም በትክክል እንድንረዳ ይገባል። በተፈጠረው ጉዳይ በሙሉ ዘራፍ ብለው አደገኛና ብልህ ያልሆን እርምጃ እንዲወስዱ አንጠብቅ። ያላቸውን የሃይልና የድጋፍ መጠን ያውቁታል። ጉዛዋአቸው ረዥም ነው፤ ማራቶን ነው እንጂ መቶ ሜተር ሩጫ አይደለም።

ለምሳሌ ያህል ወልዲያ በተፈጸመው ኢሰባዊ ድርጊት ተነስተው እነ ገዱ አንዳርጋቸው ይጩሁ ማለት ጥሩ ጥያቄ ቢሆንም ባይጮሁ ወይም እንደምንፈልገው ባይናገሩ አንበሳጭ። ትእግስት፤ ትእግስት። ከአንደኛ ወደ አራተኛ ማርሽ መሄድ አደገኛ ነው። እነዚህ ሰዎች በፓርቲዎቻቸው ያላቸውን ተሰሚነትና ኃይል ቀስ ብለው ያደራጁ። ከፍ ባሉ ቁጥር ይበልት ደፋር የሆነ እርምጃ መውሰድ ይችላሉ። ግን ደረጃውን አንድ በአንድ መውጣት አለባቸው። ልክ ፑቲን እንዳደረገው።

በመጭረሻ ላስታውሳችሁ የምወደው እነ ለማና ሌሎች በስልጣን ላይ ስለሆኑ የሚታዩ ቢሆንም ከነሱ በታች ብዙ የነሱን አቋም የሚጋሩ አሉ። አለነሱ ብቻቸውን ሊሰሩ አይችሉም ነበር። እነሱም እንደ እባብ ብለህ መሆን አለባቸው። ሌሎቻችንም ከኢህአዴግ ውጭ ያለነው እራሳችንን ገምግመን ውስጥ ገብተን ብንረዳቸው ይመረጣል።

Saturday, 6 May 2017

The ANDM Disconnect

During and after the 2016 protests, we often heard various ANDM officials claim that one of the main causes of unrest in Amhara State was the ‘disconnect’ between ANDM the party and the people of Amhara State. The people do not consider ANDM as having come from them, as being part of them, as wanting the same things that they want, as representing them, as standing up for their interests, etc. To put it simply, ANDM and the people of Amhara State are not of one mind nor of one heart.

This diagnosis of the unrest is, in my opinion is, not only correct, but perfect – it strikes at the very heart of the matter. Politics is best when a people are, among themselves, of one mind and heart, and when a people and its leadership are of one mind and one heart. Politics is at its worst when a people are divided amongst themselves and divided from their leadership. Division is the single biggest enemy of peaceful and prosperous politics and civil life.

Note that by division I don’t mean that there should not be differences. Differing ideologies, opinions, or even interests, to some extent, are natural. There almost ought to be differing ideologies, opinions, and interests. However, a people and leadership of one mind and one heart have a level of trust and understanding that allows them to handle these differences in an agreed upon peaceful and effective manner. So the differences do not end up resulting in division! The people and their leadership realize that at the end of the day, they have to live together and that therefore their basic interests are intertwined. They have to cooperate on basic issues and must not cross certain lines that lead to division. This is what being of one heart and mind is about.
So, yes, in Amhara State, there is division between the people and their leadership. ANDM is disconnected (was never really connected in the first place) from the people of Amhara State. What’s the consequence of this disconnect? Well, in general, it’s poor governance – ineffective government, corruption, injustice, etc. But specific to Ethiopia’s current political problems, the consequence is a disproportionately weak ANDM and Amhara State, and a disproportionately weak Ethiopian nationalism.

Is this a problem for the EPRDF as a whole? What’s wrong if ANDM is weak, if Amhara State is politically weak, and if Ethiopian nationalism is weak? There are those diehard fundamentalists in the EPRDF who do not see it as a problem. Their answer to every problem and situation is to stay the course because they have been in power for 26 years and they know what they are doing! For them, the 2016 protests are just another temporary setback which will be soon forgotten. But for forward thinking members of the EPRDF, who are well aware that the EPRDF has made numerous changes over its history, the 2016 protests indicate that significant changes are required for the EPRDF to continue in power. And one of these changes is that parties other than the TPLF – such as ANDM – have to shoulder their proper share of responsibility and exercise their proper share of power.

Why can’t the TPLF go it alone, so to speak, as it has for a quarter decade so far? The reason is that it is now clear that the vanguard party developmental state (10 years old) – which today is the EPRDF’s main policy and instrument of survival – and ethnic federalism (23 years old) and are incompatible. Not only incompatible, but a combustible combination – combustible enough to blow up the EPRDF’s hold on power. The EPRDF being a TPLF-led vanguard party, in other words with the TPLF holding most of the power and the other parties such as ANDM being junior partners, cannot sustain the developmental state because the resulting ethnic resentment will be too much handle. Therefore, ANDM (and OPDO and SEPDM etc.) need to have more weight in the EPRDF, so that the EPRDF is no longer a TPLF-led front, and thereby anti-TPLF and anti-Tigrean resentment will be slowly reduced. If ANDM and the others continue to be weak and estranged from its people, anti-TPLF resentment will continue increasing and the EPRDF’s hold on power will be weakened.

In order for ANDM to carry its weight in the EPRDF, it must be reconciled with the people of Amhara State. How can this be done? The first step would be for ANDM leadership to understand and accept that their political survival requires such reconciliation. The second is to bring about reconciliation via good governance and so make good governance the focus of their (perpetual!) mandate. Wait a minute – how is this possible? Corruption and favouritism are natural to the one party developmental state. All politicians in a developmental state have to have clients and networks and patronage, otherwise they will be unable to survive. As we have seen in Ethiopia, trying to achieve good governance is always a losing battle in a one party developmental state. Actually, let alone in Ethiopia, the Chinese Communist Party has for 40 years found it impossible to deal effectively with poor governance. Given this, how can ANDM bring about good governance?

The answer is that ANDM must first realize that 1) their survival is today very tenuous; 2) reconciling with the people of Amhara State their only hope for survival; and 3) given the current political reality in Ethiopia good governance is ANDM’s only way to bring about reconciliation. ANDM has no choice – in order to survive, it must reconcile with its people, and in order to reconcile, it must bring about good governance – peace, justice, transparency, no corruption, no favouritism, and a focus on aligning policy with the interests of the public.
What will the TPLF say about this? Will it not consider an ANDM united with the people of Amhara State as a threat? Will it not interfere in Amhara State? Let me say it clearly – the TPLF does not have a choice in the matter. If ANDM reconciles with its population – or simply just makes the decision to do so – there is nothing the TPLF can do about it. Unless there are federal issues at stake, the TPLF has to leave the management of Amhara State to ANDM. If it interferes, it is going to have to literally colonize Amhara State with Tigreans, something which it has not done to date and which it will not do, since this will result in a revolt it cannot control. Note that the EPRDF had a hard time controlling the 2016 revolt even though it was as much an anti-ANDM as anti-TPLF revolt. But if ANDM is one with the population, then the EPRDF would have to give in to ANDM’s wishes.

Let me add here that even today, the TPLF is not the direct cause of corruption, favouritism, injustice, etc. in Amhara State. The TPLF’s tentacles do not and more importantly cannot directly reach the local level. To put it simply, if the administrators of, say, Debre Marqos woreda, are corrupt and inefficient and do not represent the will of the people, this is a problem between them and the people, and a problem that can be fixed between them. The administrators are not from the TPLF, neither is their security from the TPLF. In most cases the administrators and the security apparatus are neighbours and relatives of the people of Debre Marqos. I use this example to illustrate that if ANDM and the people of Amhara State have the will, it is possible for ANDM to reconcile with the people of Amhara State. There will be no interference from the TPLF.

What will be the consequence of this reconciliation? It means that ANDM will have a significant increase in its political power. That is, it will be able to mobilize its people much more effectively than it can now, and this ability to mobilize is the basis of political power. This increase in political power will mean that ANDM will no longer be a junior partner in the EPRDF relative to the TPLF. This is the key to its survival. Again, understanding that this is the key to its survival is what should motivate it to change.

Will not the TPLF resist? Of course, there will be parts of the TPLF, the old guard, who will resist, but they will be unable to. Why? The TPLF is a minority whose dominance is solely a result of their unity and the disunity of the majority. Just a slight increase in the level of unity amongst the majority is enough to overcome any resistance some factions in the TPLF may try to put up. If ANDM and the people of Amhara State are reconciled, that is, if there is unity in Amhara State, the TPLF simply can no longer dominate. And many in the TPLF know this very well. In addition, note that, as I mentioned above, there is a part of the TPLF that wants to relinquish their dominance because it understands that this dominance is the biggest source of anti-EPRDF resentment and that if this dominance continues, both the TPLF and its Tigrean constituency will be at great risk. The problem is that they don’t see any political force, include ANDM and the other junior partners in the EPRDF, that is ready to take over the power that the TPLF relinquishes. But if ANDM does its job and becomes hand and glove with the people of Amhara State, then TPLF dominance will decrease in an orderly and stable manner, and in a roundabout way the survival of the EPRDF and TPLF will be reassured.

One Heart’ (‘And Lb’) should become the new slogan of ANDM. Everyone at all levels should be required so sign on to this. This is the only way for ANDM to repair the disconnect with the people of Amhara State and to become one with the people. This in turn is the only way ANDM can survive. Most importantly, this is key to the survival of the Ethiopian nation.

Monday, 29 August 2016

ፑቲኖቻችን የት አሉ?

2008/12/6 ዓ.ም. (2016/8/12)

የሶቪዬት ህብረት ከወደቀ ብኋላ ምእራቡ ዓለም በተለይ አሜሪካ ሩሲያኖችን እንረዳችኋለን፤ ኤኮኖሚአችሁ እንዲታደስና እንዲያድግ እንረዳችኋለን፤ ወደ ዓለም ኤኮኖሚ በቀላሉ እንድትቀላቀሉ እናደርጋለን፤ የቀዝቃዛ ጦርንነትን ለማፍረስ ስለተባበራችሁን ሩሲያ በጠቅላላ እንድትበለጽግ እናደርጋለን ብለው ቃላቸውን ሰጡ። ነገር ግን ቃላቸውን አጥፈው በሩሲያ ሀገር አፍራሽና ህዝብ ጎጂ የሆነ አመራርና መርህ በሀገሪቷ እንዲሰፍን ገፋፉ። በዚህ ምክንያት የሩሲያ ህዝብ የአስር ዓመት በላይ የስቃይ ዘመን አሳለፈ። ስቃይ ስል ህዝቡ ደህይቶ የሚበላውን ያጣበት፤ ወንጀልና ሽብርተኝነት የሰፈነበት፤ ህዝቡ ጤና አጥቶ የአማካኝ የህይወት እድሜ ከ70 ወደ60 የወረደበት፤ ሙስናና የማፊያ (ትብብር ወንጀል) ሥረዓት የሞላበት ሀገር ሆና ነበር ሩሲያ።

በዚህ የሩሲያ ስቃይ ዘመን የሀገሪቷ መሪ ፕሬዚደንት ቦሪስ ዬልትሲን ነበሩ። በ1991ዓ.ም. ከስልጣን በፈቃዳቸው ወረዱና ምክትላቸውን ቨላዲሚር ፑቲንን ፕሬዚደንት እንዲሆን ወከሉ። የዬልትሲን ደጋፊዎች የሆኑት በመንግስት አመራር ውስጥ የነበሩት ትላልቅ ባለ ሀብቶች የውጭ ሀገር «ንጂኦ» አንቀሳቃሾች የምዕራብ ሀገር መንግስታት ሁሉም ፑቲን በአስተሳብም በርዕዮት ዓለምም በእምነትም የዬልትሲን ተቃራኒ እንደሆነ ዓገር ወዳጅ እንደሆነ አልጠረጠሩም ነበር! በኢትዮጵያ ሁናቴ ለማምሳሰል ያህል መለስ ዜናዊ ይልቃል ጌትነትን ወይም ሌላ ተቃዋሚ ሾሙ እንደማለት ነው!

ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? እንዴት ዬልትሲንና ዙሪያቸው ያሉት መሪዎች ደጋፊዎች ባለሟሎችና የውጭ ሀገር መንግስታት የፑቲንን የእውነት ባህሪና አቋም አላወቁም? ምክንያቱ ቀላል ነው፤ ፑቲን እራሱን አላገለጠም። ማንነቱን በሚያስፈልገው መጠን ሰውሮ ነበር። ይልቁኑ በዬልትሲን መንግስት በተለያየ ቦታዎች ሲያገለግል ጎልማሳው ፑቲን በታታሪነትና በዓለቃን ማክበርና በተለይ ለዓለቃ ያለው ታማኝነት ነበር የሚታወቀው። ከአመራር ወስጥ ያሉትና ከየሀገሩ ገዥ የነበሩት ባለሃብቶች («የሩሲያ ቢሊዮኔሮች» የተባሉት) በደምብ ይግባባ ነበር። ከመጠን በላይ ብልጥም ፖሊቲካ የገባውም ነበር። በፍጹም አልተጠረጠረም!

ቨላዲሚር ፑቲን ፕሬዚደንትም ሲሆኑ የእውነት አቋሞቻቸውን ወድያው አላሳዩም። በመጀመርያ ስልጣናቸውን ቀስ በቀስ አጠናከሩ። ጓደኛ እንጂ ጠላት የማያፈራ መርህዎችን አራመዱ። አሸባሪዮችን አጠቁና የጦርሰራዊት የፖሊስና የጸጥታ ኃይሎችን ድጋፍ አረጋገጡ። ከምዕራብ ሀገሮች ጋር በጸረ ሽብርተኝነት ሩሲያ በደምብ እንድትተባር አደረጉና የምዕራብ መንግስታትንም ድጋፍ አገኙ። ከዚያ ቆይተው ፑቲን ስልጣናቸውን ካረጋገጡ በኋላ በዬልትሲን ዘመን በዝርፍያና በሙስና ያደጉት ባለሀብቶችን በማሳሰር በማሳመን ስልጣናቸውን ነጠቁ አጠፉ። እነዚህ እርምጃዎች የፑቲንን የህዝብ ድጋፍ መጠን በጣም እንዲልቅ አደረጉ (ስልጣን ከያዙ ጅምሮ ከ65 እስቀ 80 በመቶ ድጋር አላቸው)።

ከዬልትሲን ወደ ፑቲን የተካሄደው የሩሲያ ለውጥ ከሞላ ጎደል ሰላማዊ ነበር። እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚፈለገው ሰላማዊ፤ ማንም የማይጠቃበት፤ ሀገር የማይረበሽበት፤ ጥላቻ የማይሰፍንበት፤ ቅራኔ የምያሳንስና መግባባት ለዘብተኝነት መቻቻል የምያጠቃልል ለውጥ ነው።

እንደዚህ አይነት ለውጥ የሚመጣው ከዓብዮት ሳይሆን ከውስጣዊ ቀስ በቀስ የሚመጣ ለውጥ ነው። ለንደዚህ አይነት ለውት የነባር መንግስት ውስጥ በርካታ የለውጥ አጋሮች ያስፈልጋሉ፦ ፑቲኖች ያስፈልጋሉ! ሥርዓቱ ሲናጋ ውግያና ሁከት ለማምጣት ወደኋላ የማይሉ አክራሪዮች ስልጣን እንድይዙ ውይም በውሳኔ ላይ እንዲያመዝኑ ያደርጋል። ይህ እንዳይከሰት እነዚህ የውስጥ ለውጥ የሚፈልጉ ለዘብተኛ የሆኑት አስፈላጊ ናቸው። አክራሪውም በለዘብተኛው እንደተከበበ ሲያይ ግድ ይመለሳል።

ነገር ግን እንደዚህ ሰርጎ ገብተው የሚያገለግሉ ሰዎች የራሳቸውን ህልውና ለመጠበቅና ይበልጥ ረጅም አላማቸው እንዳይከሽፍ ብለው እራሳቸውን መደበቅ አለባቸው። እዚህ ላይ ብልጠት ያስፈልጋል። መሪዎቻቸውን መምሰል አለባቸው። አለጊዘው ስልጣናቸውና የስልጣን ድራቸውን በቂ ሳያስፋፉ ሳያጠነክሩ ጠንካራ አቋም መውሰድ የለባቸውም። እንደ ፑቲን ስያስፈልግ አንገታቸውን ደፍተው መኖር አለእባቸው። «እንደ እባብ ብልዖች እንደ ርግብ የዋሃን ሁኑ» ውይም «ዛሬ ህይወትን ካጡ ወደፊት መታግል አይቻልም» እንደሚባለው።

በዚህ ጊዜ ብዙሐናም «ተቃዋሚዎች»ም ብልህ መሆን አለባቸው። ከውስጥ የስውር ጠቃዎሚዎች በይፋ እየተሟገቱ በስውር መተባበር አለባቸው። አንድ ነገር ማስታወስ አለብን፤ ዋናው የኢትዮጵያ ፖሊቲካ ችግር የተሳትፎ ጉዳይ ነው። ህዝቡ መሪውን ሲጠላ ከመንግስት ወስጥ ከመሳተፍ ይርቃል። «ፖለቲካና ኮሬንቲ» የሚባለው ስሜት ያመዝናል። ይህ ማለት በርካታ የኢትዮጵያ ህዝብ ወገኑን ውይም የሃሳብ አጋሩን ከመንግስት ወስጥ የለም። በታችኞቹ የመንግስት አካሎችም እንደ ቀበሌና ወረዳ ለመሳትፍ አይፈልግም ቤተሰቡም ዘመዱም እንዲሳተፍ አይፈልግም። መንግስትን «ለሌሎች» ትቶት በብአድ እየተገዛ ነው። ይህ አስተሳሰብ ተገቢ የሆነ የታሪክ ምክንያት ቢኖረውም ትክክል አይደለምም እጅግ ጎጂም ነው። አለመሳተፍ አክራሪነትንና ዓብዮትን የሚጋብዝ ለዘብትኘትና ትብብርን ቦታ የሚያሳጣ አስተሳሰብ ነው።

«እንዴት ኢህአዴግ ውስጥ መስራት ይቻላል፤ ሕሊናን መሸጥ ወይም ጥቃትን መቀበል ያስፈልጋል» ሊባል ይችላል። ታድያ በሰሞኑን የጎንደር ተቃውሞ ላይ የኃይል እርምጃ እንዳይወሰድ ያደረጉት ማን ናቸው? አልፎ ተርፎ በኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ወስጥ ያሉት በዝቅተኛ የስልጣን ደረጃ ያሉት ወታደሮች በአብዛኛው ማናቸው ከየት ናቸውም? በየቀበለውና ወረዳ የሚያስተዳደሩት (ከትግራይ ክልል በስተቀር) ማናቸው? የታወቀው ኢህአዴግን ለቆ የወጣው ኤርሚያስ ለገሰ ማን ነው? አምባሳደር ሆኖ በግዞት ወደ ቱርኪ የተላኩት አቶ አያሌው ጎበዜ ማን ናቸው? ለነገሩ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ማናቸው? እነዚህ በሙሉ የለውጥ አጋሮች ወይም ሁኔታዎች ሲፈቅዱ የለውጥ አጋሮች ሊሆኑ የሚችሉ ናቸው!

መርሳት የለለብን የኢህአዴግ መንግስት የአናሳ መንግስት እንደሆነ ነው (በዚህ ካልተስማማን የህዝበ ድጋፍ አላቸው ብለን አመንን ማለት ነው!)። ኢህአዴግ መላ የኢትዮጵያን ህዝብን እንወክላለን ባይ ነው ግን ተቃዋሚዎችና በርካታ ህዝብ የትግራይ መንግስት ነው ብሎ ይከሰዋል። አናሳ ነው ብለን ከተቀበልን ማውቅ ያለብን አናሳ መንግስት ሀገርን መግዛት የሚችለው ሌላው ህዝብ ከፈቀደለትና በደምብ ከተባበረው ብቻ ነው! ኢህአዴግ እንደ ደርግ አለብልሃት በመጭፍለቅ ብቻ መግዛት አይችልም። ኢህአዴግ የሌላው አለመተባበር ውይም ከፖሊቲካ መራቅ ውይም በፈቃደኝነት መገዛት ያስፈልገዋል። ይህ ውነታን በግልፅ የሚያንጸባርቀው ኢህአዴግ ፓርቲውም ጦርሰራዊቱም በቁጥር ደረጃ በአብዛኛው የትግርኛ ተናጋሪ አለመሆኑ ነው።

ስለዚህ ኢህአዴግ ውስጥ ገብቶ ወዲያው ሳይሆን ከስ ብሎ ልውጥ ማምጣት ካልሆነም የለውጥ አጋር መሆን እንደሚቻል ግልፅ ነው። ህዝቡ ይግባ፤ ይሳተፍ፤ ሲያስፈልግ አንገቱን ደፍቶ እሺ ይበል፤ ቀስ ብሎ በስልጥ አብዛኛነትን ያረጋግጥና ጊዘው ሲደርስ ለውጥ ያመጣል።

ከፑቲን የምንማረው ትምህርት የህ ነው። ፑቲን ለዬልትሲን መንግስት ሲያገለግል ብቸኛ የውስጥ ተቃዋሚ አልነበሩም ሊሆኑም አይችሉም ነበር። ፕሪዚደንት ፑቲን ሲሾሙ እንድርሱ አንገታቸውን ደፍተው የመትፎ አገዛዙን ውስጥ ለውስጥ የሚሸረሽሩ ሀገር ወዳድ ይሆኑ ትናንሽ ፑቲኖች አብረው ተነሱና ፑቲንን ደግፈው አላማቸውን አራመዱ። ፑቲን ብቻቸውን ቢሆኑና የሳቸውን አላማ የሚደግፍ ከሥርዓቱ ውስጥ ባይኖሩ የትም አይደርስም ነበር።

በተዘዋዋሪ በሰሞኑ በአማራ ክልል በተካሄደው ተቃውሞ ሰልፎች ምክንያት አንዳንድ የህወሓት ተንታኒዎች ብአዴን በሰላይዎችና በከሃዲውች የተሞላ ነውና ጽዳት (በሌላ ቃል እስራና ግድያ) ያስፈልገዋል ብለው ይተቻሉ! ውነት ነው ህወሓት ለ26 ዓመት በመግዛቱ በፖሊቲካ ስልጥ ከሌላው ልቋልና እንደዚህ አይነት ነገር ቶሎ ነው የሚገባው። ሌላውም ሊገባው ይገባል።

መጀመርያ የታተመው ከዚህ