Showing posts with label policy. Show all posts
Showing posts with label policy. Show all posts

Wednesday, 30 June 2021

የቶክስ ማቆም ውሳኔውና የጎሳ ብሔርተኝነት አደጋ

ስሜታዊና በፖለቲካ ያልበሰልን ስለሆንን የትግራይ ህዝብ ከህወሓት ጋር ወግኗል እንላለን። ይህ አመለካከት እጅግ simplistic ነው። በሕብረ ብሔሪዊ ሀገራት የህዝቡ ታማኝነት ከፊል ለሀገሩ ከፍል ለጎሳው/ብሔሩ ነው። ሀገሪቷ ጤናማ (ሰላማዊ) የምትሆነው የህዝቡ ታማኝነት ከጎሳው ይልቅ ወደ ሀገሩ ቢያደላ ነው። ለምን ሲባል የሀገርና የጎሳ ፍላጎትና ጥቅም አልፎ አልፎ ሊለያዩ ይችላሉ። ጎበዝ ፖለቲካኞች ካሉ እነዚህን ልዩነቶች የሳንሳሉና ወደ ሁሉንም የሚጠቅም መንገድ ያመራሉ። ምንም ቢጥሩ ግን አለመስማማት አይቀርም። ስለዚህ ህዝቡ ከጎሳው ይልቅ ሀገሩን የሚያስቀድም ከሆነ፤ ማለት የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜት እናሳ ከሆነ፤ በጎሰና በሀገር ያሉት ልዩነቶች በቀላሉ ይፋታሉ። ካልሆነ ግን ሀገሪቷ የግጭት ስፍራ ትሆናለች።

አሁን በትግራይ የምናየው ይህ ነው። ለ57 አመት ለትገራይ ህዝብ የተሰበክለት የጎሳ ብሔርተኝነት ዋጋ እያስከፈለ ነው። ከ 57 አመት በፊት የትግራይ ህዝብ የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜት አልነበረውም ማለት አይደለም። ግን ስሜቱ በየጊዜው እየጨመረ ሄደና አሁን ከመጠን በላይ ትግራዊ ጎሳውን ከሀገሩ በደምብ የስቀድማል።

የጎስንነት ስሜት ተቀያያሪ ነው። 69 ዓመት በፊት ኤርትራዊያን ከኢትዮጵያ ጋር እንቀላቀል አሉ። 41 ዓመት በሗላ ከ90% በላይ እንገንጠል አሉ! ፖለቲካ፤ ኤኮኖሚ፤ ግጭት ወዘተ የሰውን ስሜት ይቀይራል። የጎስኝነት ስሜቹን መመለሱ ቀላል አይደለም። ብዙ ጊዜ አይቻልም። 

ሰባት ወር በፊት መንግስት አብዛኛው የትግራይ ህዝብ ልብ የት እንደሆነ መገመት ብቻ ነበር የሚችለው። የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜቱ ምን ደረጃ ላይ ነው? ሰላም፤ ፍትህና የኤኮኖሚ እርዳታ ከሰጠነው የሀገሩ ስሜት ከጎሰኝነቱ እንዲያይል ማድረግ ይቻላል ወይ? መሞከሩ ነው የሚያዋጣው ብሎ ወስነ መንግስት። ሞክረና አልቻለም። ወደ ሁለተኛው አማራጭ ዞረ። ብዙ ሰዎች፣ ቤተሰቦች፣ መንዶሮች ዋጋ ይከፈላሉ ልክ እንደ የኤርትራ መገንጠል።

በዚህ ምክንያት በሕብረ ብሔራዊ ሀገራት የጎሳ ብሔርተኝነት እንዳይበዛ መንግስት ሁልጊዜ መጠንቀቅ አለበት። ያለውን የገንዘብ፣ የፖሊሲ፣ የኃይል አቅም በሙሉ ተጠቅም የጎሳ ስሜትና ፍላጎት እንዲከበርና ሀገራዊነት እዲያይል መደረግ አለበት።

Friday, 16 November 2018

ስለ የዩኒቨርሲቲ ምደባ …

የታወቀ ችግር አለ…

ልጁ በ18 ዓመቱ ከወላጆቹ ቤት ለመጀመርያ ጊዜ ወጥቶ ወደ ሩቅ ሀገር ዩኒቨርሲቲ ይላካል። ከዛ ታላቅ ፈተናዎች እና አደጋዎች ይጠብቁታል። ብቸኝነት፤ ጥካት፤ ጭንቅ፤ ውጥረት፤ ስጋዊ ፈተኖች፤ ወዘተ። ዩኒቨርሲቲ እያለ በቀለ የለመደውን የቤተሰብ፤ ዘመድ እና በጠቅላላ የአካባቢ ድጋፍ የለውም። የሚደርሱበት ችግሮችን ከሞላ ጎደል ብቻውን መውጣት ይኖርበታል። አንዳንዱ ልጅ ፈተናውን ይወጠዋል አንዳንዱ ደግሞ ፈተናው ይውጠዋል።

መሰረታዊው ችግር ይህ ነው፤ «ለሰው ልጅ ከትውልድ ሀገሩ ተነቅሎ ብቻውን ሌላ ሩቅ ቦታ መሄድ ኢ-ተፈጥሮአዊ ነው»። ይህ «ስደት» ጎጊ ብቻ አይሆን «ኢ-ተፈጥሮአዊ» ነው። የሰው ልጅ በተፈጥሮ ወላጅ እና እህት ወንድሞች ብቻ ሳይሆን ዘመድ አዝማድ እና መንዳር አለው። ከነዚህ መሃል ሆኖ ነው ጤናማ ኑሮ መኖ የሚችለው።

ለዚህም ነው በሰው ልጅ ታሪክ የትውልድ ቦታን ትቶ ብቻውን ተሰዶ ሌላ ቦታ መሄድ የሌለው። ሰው ከተሰደድም 1) በታላቅ ችግር ምክንያት ነው የሚሰደደው እና 2) ብቻውን ሳይሆን ከመላ ቤተሰቡ እና መንደሩ ጋር ነው አብሮ የሚሰደደው። እንጂ የሰው ልጅ ብቻውን ቤቱን ትቶ አይሄድም።

ሁለተኛው ችግር ደግሞ ቤታቸውን ትተው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚሄዱት ገና ልጆች ናቸው። ቤተሰብ የመሰረቱ ጎልማሶች አይደሉም። ብዙዎቹ ሃላፊነትም አለመዱም። «ተማሩ እና እራሳችሁን ቻሉ» እየተባሉ ከሌላ ሃላፊነት ነፃ ሆነው ያደጉ ናቸው። እንደ ድሮ ልጆች የበሰሉ አይደሉም። ሽፋናቸው የበሰለ ይመስላል ግን ጥሬ ናቸው።

ሶስተኛ ችግር… በተፈጥሮ የሰው ልጅ ላቅማዳም ካለፈ የትወሰነ ዓመት በኋላ ቤተሰብ ይመሰርታል። እንደገና ይህ ጠፈጥሮ ነው ነአ ተፈጥሮን መታገል አጉል ነው። እነዚህ ልጆች ኃይለኛ የስጋዊ ፈተና አለባቸው። ብቻቸውን ዩኒቨርሲቲ ሲሄዱ ፈተናው ይበልጣል። ገቤተሰቦቻቸው ጋር ቢሆኑ እና በሃላፊነት እና ድጋፍ በከበቡ ይሻላል። ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ ፈተናውን ተቆጣጥረውት ትምሕርታቸውን ሲጨሩሱ ወደ ቤተሰብ ምስረታ መሄድ ይችላሉ።

በነዚህ ምክንያቶች ልጆችን ከቤተሰብ ነቅሎ ወደ ሩቅ ዩኒቨርሲቲዎች መላክ አይመረጥም። እነ ልጆቼ ከቤት ሆኖ ተምረው እንዲዳሩ ነው ፍላጎቴ። ይህ ትክክለኛው ተፈጥሮአዊ መንገድ ነው ብዬ አምናለሁ።

ይህን ሁሉኡ ስል የፖሊሲ አውጪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ እንደ ህዝብን ማስተዋወቅ እና ማቀላቀል መንገድ እንደሚያዩት ይገባኛል። ጥሩ አላማ ቢሆንም ጉዳቱ ከጥቅሙ የሚበልጥ ይመስለኛል። ቢያንስ አስተማሪዎችን የመመደብ እድል መስጠት ነው። እድሜአቸው ትልቅ በመሆኑ ምናልባትም ቤተሰብ ስላላቸው ከባድ ቢሆን ይሻላል።

Wednesday, 19 September 2018

«የእሽሩሩ ፖለቲካ»

በርካታ ሰዎች የጎሳ ብሄርተኖችን «እሽሩሩ» (appease) ማድረግ የለበንም ይላሉ። ልክ ልካቸውን መንገር አለብን። የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት እና እልቂት ምንጭ በመሆኑ መጥፋት እንዳለበት መናገር አለብን። ገና ለገና እናስቀይማቸዋለን ብለን ትክክለኛ ሃሳቦቻችንንም እውናተንም ከመናገር መቆጠብ የለብንም። ይባላል።

በመጀመርያ «እሽሩሩ» ግልጽ ያልሆነ የጅምላ አባባል ነው። ጉዳዩን በትክክል ለመተንተን precise መሆን አለብን። «እሽሩሩ»፤ «ዲፕሎማሲ»፤ «የአገላለጥ ስልት»፤ «ብልህነት» ምን ማለት ናቸው? ተግባሩን ካልወደድነው ወይንም ትክክል ካልመሰለን «እሽሩሩ» እንለዋለን፤ ትክክል ከመሰለን «ዲፕሎማሲ» ወይንም «የአገላለጽ ስልት» እንለዋለን። ስለዚህ «እሹሩሩ» አይነቱን ቃል ከመለጠፍ በፊት ጉዳዩን በትክክል እንየው።

ዓለም ዙርያም በኢትዮጵያም እንደምናየው በተግባርም በጽንሰ ሃሳብ እንደሚታወቀው የጎሳ ብሄርተኖች ከለዘብተኛ እስከ ጸንፈኛ እና በነዚህ መከከል አሉ። ባጭሩ ጸንፈኛው የጎሳ ብሄርተኝነቱ ከማንነቱ ጋር እጅግ ስለተቆራኘ ሃሳቡን መለወት ከባድ ነው ለመሞከርም ብዙ አያዋጣም። ግን ከዛ ለዘብተኛ የሆኑት እስከ ጥቂት የጎሳ ብሄርተኝነት ያላቸው ሰዎች ወደ ሀገራዊ ብሄርተኝነት ማምጣት ይቻላል። ይቻላል ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ግድ ደው። ኢትዮጵያዊነት የሚዘልቀው ለዘብተኞቹን ወደሱ በማምጣት ነው።

እንዴት ነው ትንሽ እና ለዘብተኛ የጎሳ ብሄርተኝነት ስሜት ያላቸውን ወደ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ማምጣት የሚቻለው? እንዴት ነው ይህ ህዝብን በዜጋ የተመሰረተ ህገ መንግስትን እንዲደግፍ ማድረግ የሚቻለው?

የሚቻለው በአውንታዊ መንገድ ነው። ኦሮሞነት በኢትዮጵያዊነት ይንጸባረቃል በማለት ነው። ቋንቋቸው የኢትዮጵያ ቋንቋ ነው በማለት ነው። ባህላቸው የኢትዮጵያ ባሕል ነው በማለት ነው። አልፎ ተርፎ ጥያቄዎቹን (demands) ሰምቶ ተገቢ የሆኑትን ማለትም በህብረ ባህላዊ እና ህብረቋንቋዊ (ህብረ ብሄራዊ ሳይሆን ማለት ነው) ሀገር መስተናገድ የሚችሉትን ማስተናገድ እና ማስፈጸም። እንዲህ ነው ትንሽ እስከ ለዘብተኛ የጎሳ ብሄርተኝነት ወደ «ኢትዮጵያዊነት» ማምጣት የሚቻለው እና በሀገራችን ያለው ጣቅላላ የጎሳ ብሄርተኝነት ስሜትን መቀነስ እና ቀስ ብሎ ማጥፋት የሚቻለው።

ግን መልእክቶአቻችን አሉታዊ ከሆኑ ለዘብተኞችን ወደ ጸንፈኖቹ እንገፋቸዋለን! ማስተወስ ያለብን የጸንፈኞቹ ትግል ከኛ ይቀላል። ሰውን በጎሳ ማንነቱ ማስተባበር ቀላል ነው በሰው ልጅ ተፈጥሮ ምክንያት። ጸንፈኛው ጎሰኛ «ማንነትህ እየተደፈረ ነው» በማለት ብቻ በስሜታዊ መንገድ ለዘብተኞቹን መሳብ ይችላል። ስለዚህ እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ለዚህ አይነት ቅስቀሳ ጥይት እንዳናቀብል መጠንቀቅ አለብን። ጥይቱ ምን ይመስላል? በጅምላ ኦሮሞነት ዘረኝነት ነው ማለት። የጎሳ አስተዳደር አሁኑኑ ሙሉ በሙሉ ይጥፋ ማለት። በጎሳዎች ልዩነቶች የሉም አንድ ቋንቋ አንድ ባህል ነው ያለን ማለት። ወዘተ። እንደዚህ አይነት መልዕክቶች ለዘተኞቹን ወደ ጸንፈኖች ይገፈትርዋቸዋል።

አንድ ጽሁፌ ላይ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/understanding-ethnic-soft-nationalism.html) ስለ ካናዳ ያለው የኬቤክ ጠቅላይ ግዛት የጎሳ ብሄርተኝነት። የጎሳ ብሄርተኛ ፖለቲከኞች አንድ ካናዳ ብሄርተኛ ጠንካራ ወይንም እንደ ስድብ ሊቆጠር የሚችል ንግግር እስኪያደርግ አድፍጠው ይጠብቃሉ። ልክ የሚፈልጉትን ስያገኙ ለሁለት ሶስት ቀን ሚዲያቸውን በሙሉ በዚህ ክስተት ያጥለቀልቃሉ። በፊት ለዘብተኛ የነበረው ወደ አክራሪነት ሲንሳፈፍ በድምጽ ቆጠራ (poll) እናያለን። ዓለም ዙርያ የታወቀ የተለመደ ስልት እና ክስተት ነው።

አንዱ የፖለቲካ ሙያ ስራ ለተላያዩ ሰዎች አቋምን በተለያዩ መንገዶች መግለጽ ነው። መዋሸት ሳይሆን የአገላለጽ ዘዴን በሚያስፈልገው መንገድ ማስተካከል ነው። ለኢትዮጵያ ፕሬዚደንት የሚወዳደር ሰው ግንደር ሲሄድ ስለ ጎንዳር ላይ የሚያቅደው ልማት ይናገራል። አፋር ሲሄድ ስለ አፋር ላይ የሚሰራው መስኖ ይናገራል። ይህ የታወቀ ነገር ነው። የጎሳ ብሄርተኝነትን manage ለማድረግ እንዲሁ ነው የሚደረገው። ምንም ልዩነት የለውም ምናልባት ይበልጥ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል እንጂ።

ባጭሩ በኢትዮጵያ የጎሳ ብሄርተኝነትን መቀነሻ እና የጎሳ ፌደራሊዝምን ማጥፍያ መንገድ ይህ ነው፤

1. ትንሽ እና ለዘብተኛ የጎሳ ብሄርተኝነት የሚሰማቸውን በስልት እና ተባር (እንደ ቋንቋ ፖሊሲን መቀየር) ወደ ኢትዮጵያዊነት ማምጣት እና ከጸንፈኞቹ መለየት።

2. ቋንቋ እና ባህል እንዲቀላቀል አስፈላጊ ፖሊሲዎችን ማስፈጸም። የ«ቅይጥ» ህዝቡን ቁጥር የሚጨምር ፖሊሲዎችን ማራመድ። በየ ክልሉ በርካታ ህዝብ ሶስት አራት ቋንቋ እንዲችል ማድረግ። (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/towards-integrated-ethiopia.html)

3. አንዴ በህዝባችን መካከል የጎሳ ብሄርተኝነት ስሜት በቂ ከቀነሰ ብኋላ እና ህዝቡ ፖለቲካዊ ፈቃዱ ሲሆን ይህንን ጸንፈኛ ህገ መንግስታችንን ወደ ዜጋ ፖለቲካ መቀየር።

አዋጪ እቅዱ ባጭሩ ይህ ነው። ዝርዝሩ ልየያይ ይችላል። ምናላባት ህገ መንግስቱ ላይ አሁኑኑ ትናንሽ ለውጦች ማድረግ በቂ ፈቃደኝነት ሊኖር ይችላል። «ፕሬዚደንታዊ» አሰራር በህገ መንግስቱ በቅርብም ማካተት ይቻል ይሆናል። ግን ከሞላ ጎደል መንገዱ እላይ እንደዘረዘርኩት ነው።

ስለዚህ «እሽሩሩ» የሚለው እውነታን አይገልጽምም አሳሳችም ነው። ይህ ጉዳይ እንደማንም የፖለቲካ ጉዳይ ስልት እና ዘዴ ያስፈልገዋል። ዲፕሎማሲም ብልህነትም ያስፈልጉታል።